AddisAbaba

በህገወጥ መንገድ ኢትዮጵያዊያንን ወደ ዱባይ ሲልክ የነበረው ሰው በ20 ዓመት እስራት ተቀጣ

በህገወጥ መንገድ ኢትዮጵያዊያንን ወደ ዱባይ ሲልክ የነበረው ሰው በ20 ዓመት እስራት ተቀጣ

በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ አርሲ ዞን ዶዶላ ወረዳ  ቢቂላ ከተማ ውስጥ ነዋሪ የሆነው ግለሠብ ከሚመለከተው አካል እውቅና ፈቃድ ሣያገኝ ሰዎችን ወደ ዱባይ የሚልከው ግለሠብ በእስራት መቀጣቱን ፖሊስ አስታዉቋል። የምዕራብ አርሲ ዞን ፖሊስ ዋና መምርያ የወንጀል ምርመራ ክፍል ሐላፊ ዋና ኢንስፔክተር ከድር ጅቦ እንደተናገሩት ተከሣሽ ገመቹ  ሰይድ የተባለው ግለሠብ ከሚመለከተው አካል እውቅና ፈቃድ ሣይኖረው  በዶዶላ ወረዳ ቢቂላ ከተማ ነዋሪ የሆኑ ሁለት ግለሠቦችን ከፍተኛ የስራ ልምድና ችሎታ  ስላላችሁ ስራ የማግኘት እድላችሁ ሰፊ ነው በማለት የማታለያ ቃል በመጠቀም ወደ ዱባይ እንደላካቸው ገልፀዋል። ተከሣሹ የተለያዩ  አሣማኝና  ማታለያ ቃላቶችን በመጠቀም ከሁለቱ ግለሠቦች 250 ብር በአጠቃላይ 500 ሺህ ብር በመቀበል ወደ ተባበሩት አረብ ኢምሬት ዱባይ ከተማ የላካቸው መሆኑ…
Read More
ኢትዮጵያ ከጤፍ የተሰራ የወተት ምርትን ለዓለም ገበያ አስተዋወቀች

ኢትዮጵያ ከጤፍ የተሰራ የወተት ምርትን ለዓለም ገበያ አስተዋወቀች

ኦሪጅናል ቴፍ-ሊ የተባለው ከጤፍ የተሰራ የወተት ምርት ዛሬ በለንደን በሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ እና በአምራቾቹ ትብብር በተዘጋጀ የማስተዋወቂያ መድረክ ላይ ይፋ ተደርጓል፡፡ በዝግጅቱ ላይ ከንግድ ማህበረሰቡ፣ ከሚዲያ፣ ከእንስሳት ተዋጽኦዎች ነፃ በሆኑ ምግቦች ምርት እና ግብይት ውስጥ የሚሳተፉ ኢንዱስትሪዎች አባላት እና የማህበራዊ ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪዎች ተገኝተዋል፡፡ በአሁኑ ጊዜ ከእፅዋት የተዘጋጁ የምግብ አማራጮች ፍላጎት እየጨመረ መምጣቱ የሚታወቅ ሲሆን ዝግጅቱ ጤፍን ለአለም አቀፍ ታዳሚዎች የበለጠ ለማስተዋወቅ እድል ፈጥሯል። በብሪታንያ የኢትዮጵያ አምባሳደር ብሩክ መኮንን በመክፈቻ ንግግራቸው ጤፍ በኢትዮጵያዊያን የአመጋገብ ዘይቤ ውስጥ ያለውን ሰፊ ቦታ እንዲሁም የአየር ንብረት ለውጥን መቋቋም በሚችሉ የምግብ ስርዓቶች ጥናቶች ላይ ሊያበረክት ስለሚችለው አዎንታዊ አስተዋጽኦ አብራርተዋል፡፡ የኦሪጅናል ቴፍ-ሊ (The Original Teff-ly) መስራቾች…
Read More
አይሾው ስፒድ የተሰኘው ተጽዕኖ ፈጣሪ በኢትዮጵያ በነበረው ቆይታ ከ240 ሺህ በላይ ሰብስክራይበር ማግኘቱ ተገለጸ

አይሾው ስፒድ የተሰኘው ተጽዕኖ ፈጣሪ በኢትዮጵያ በነበረው ቆይታ ከ240 ሺህ በላይ ሰብስክራይበር ማግኘቱ ተገለጸ

አሜሪካዊው ተጽዕኖ ፈጣሪ ዩቲዩበሩ I show speed በትናንትናው ዕለት በአዲስ አበባ የአንድ ቀን ቆይታ አድርጓል። ግለሰቡ በኢትዮጵያ በነበረው ቆይታ ሳይንስ ሙዚየም፣ አድዋ ሙዚየም፣ ስላሴ ካቴደራል ቤተ ክርስቲያን ፣ በመስቀል አደባባይ እና ሌሎችም ቦታዎችን በመጎብኘት የዓለም ትኩረት ስቧል። ዩቲዩበሩ በአዲስአበባ ጥሩ የሚባል አቀባበል ተደርጎለት እሱም እያመሰገነ ይገኛል። በኢትዮጵያ ቆይታዉ ብቻ ከ 250 ሺህ በላይ አዳዲስ ሰብስክራይበሮችን ማግኘቱንም በመገረም ሲናገር ታይቷል። ስፒድ በአዲስ አበባ ቆይታዉ በጥሩ መልኩ የኢትዮጵያን መልክ ለማሳየት የተደረጉ ጥረቶች መልካም የሚባሉ ነበሩ። የኢትዮጵያ ቱሪዝም ሚኒስቴርም አጋጣሚዉን በጥሩ የተጠቀመበት ሲሆን የወርቅ ብራስሌት፣ ጥሬ ስጋ፣ የኢትዮጵያ አየር መንገድ አቪዬሽን ማሰልጠኛ እና ሌሎች ታሪካዊ ሁነቶችን ተከታትሏል። የቱሪዝም ሚንስትር ሰላማዊት እና በሚስወርልድ ውድድር…
Read More
በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ሁለት የውጭ ዜጎችን ጨምሮ ሶስት ሰዎች ተገደሉ

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ሁለት የውጭ ዜጎችን ጨምሮ ሶስት ሰዎች ተገደሉ

የክልሉ ኮሙንኬሽን ቢሮ ባወጣው መግለጫ በደቡብ ኦሞ ሱሪ ወረዳ በጉብኝት ላይ የነበሩ ሁለት የውጭ ዜጎችን ጨምሮ ሶስት ሰዎች ተገድለዋል። የተገደሉት ሰዎች ሁለቱ የቱርክ ዜግነት አላቸው የተባለ ሲሆን ሾፌራቸው ደግሞ ኢትዮጵያዊ እንደሆነ ተገልጿል። ግድያው ትናንት ጠዋት 2:20 ላይ እንደተፈጸመ የተገለጸ ሲሆን የገዳዮቹ ማንነት የአርብቶ አደር ሽፍቶች መሆናቸውን የክልሉ መንግሥት አስታውቋል። ገዳዮቹን በህግ ቁጥጥር ስር ለማዋል የክልሉ ጸጥታ ሀይል እርምጃ መውሰድ ጀምሯልም ተብሏል። ሽፍቶቹ ግድያውን የፈጸሙት ለዝርፊያ በሚል እንደሆነም የክልሉ ኮሙንኬሽን ቢሮ ባወጣው መግለጫ ላይ ጠቅሷል። በርካታ ሀገራት ዜጎቻቸው በኢትዮጵያ ጉብኝት እንዳያደርጉ የጉዞ እገዳ እና ማስጠንቀቂያዎችን ማውጣታቸው ይታወሳል። ለአብነትም ካናዳ እና ብሪታንያ ከወራት በፊት ዜጎቻቸውን ወደ ኢትዮጵያ እንዳይጓዙ አልያም ከተጓዙ በሚል ልዩ…
Read More
በኢትዮጵያ ከተሞች ቢስፋፉም የኑሮ ውድነቱ ፈተና መሆኑ ተገለጸ

በኢትዮጵያ ከተሞች ቢስፋፉም የኑሮ ውድነቱ ፈተና መሆኑ ተገለጸ

ኢትዮጵያ በያዝነው የ2026 ዓመት የ6.3 በመቶ የኢኮኖሚ ዕድገት እንደምታስመዘግብ ቢተነበይም፣ በአገሪቱ እየታየ ያለው ፈጣን የከተሞች መስፋፋት በመኖሪያ ቤት፣ በመሠረተ ልማትና በመሠረታዊ አገልግሎቶች ላይ ከፍተኛ ጫና እያሳደረ መሆኑ ተገልጿል። ይህ ሁኔታ በተለይ ዝቅተኛ ገቢ ባላቸው የከተማ ነዋሪዎች ላይ የኑሮ ውድነትን እያባባሰ እንደሚገኝ ተጠቁሟል። አፍሪካ በዓለም አቀፍ ደረጃ በከፍተኛ ፍጥነት የከተሞች መስፋፋት የሚታይባት አህጉር ስትሆን፣ የከተማ ነዋሪዎቿ ቁጥር በየዓመቱ ከ3.5 በመቶ በላይ እያደገ ይገኛል። ኢትዮጵያም ለዚህ ፈጣን ዕድገት በምክንያትነት የሚጠቀሱት ከፍተኛ የውልደት መጠን እና ከገጠር ወደ ከተማ የሚደረግ ፍልሰት ዋነኛ ተዋናይ ናት። ይህ ፍልሰት በመኖሪያ ቤት፣ በመሠረተ ልማትና በመሠረታዊ አገልግሎቶች ላይ ያለውን ፍላጎት በእጅጉ እንዲጨምር አድርጎታል። የፍላጎትና የአቅርቦት አለመመጣጠን ደግሞ የቤት ኪራይንና…
Read More
ባለፉት 6 ወራት ከ704 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰቡ ተገለጸ

ባለፉት 6 ወራት ከ704 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰቡ ተገለጸ

ኢትዮጵያዊ ባለፉት ስድስት ወራት እንደ ሀገር ከ704 ነጥብ 4 ቢሊዮን ብር ገቢ መሰብሰብ እንደተቻለ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት አስታውቋል።  አፈጻጸሙ በገቢዎች ሚኒስቴር በግማሽ ዓመቱ ለመሰብሰብ ከታቀደው 640 ነጥብ 4 ቢሊዮን ብር ውስጥ 704 ነጥብ 4 ቢሊዮን ብር በመሰብሰብ የዕቅዱን 110 በመቶ ተሳክቷል ተብሏል። ይህ ገቢ ባለፉት ጊዜያት ለዓመታት ሲሰበሰብ ከነበረው ገቢ ጋር የሚመሳሰል እንደሆነ ተገልጿል። የተሰበሰበው ገቢ ከባለፈው ዓመት ስድስት ወራት አፈፃፀም ጋር ሲነፃፀር የ63 ነጥብ 7 ቢሊዮን ብር ብልጫ ያለው ሲሆን ስኬቱ ኢትዮጵያ የውስጥ አቅሟን በማጎልበት እያንሰራራች ለመሆኑ ሁነኛ ማሳያ ተድርጎ የሚወሰድ ነው ሲል መንግሥት አስታውቋል። በግማሽ ዓመቱ ከሀገር ውስጥ ታክስ 362 ነጥብ 4 ቢሊዮን ብር የተሰበሰበ ሲሆን ከውጪ ንግድ…
Read More
ወ/ሮ ሃይማኖት ዘለቀ የመገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣንን እንዲመሩ ተሾሙ

ወ/ሮ ሃይማኖት ዘለቀ የመገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣንን እንዲመሩ ተሾሙ

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው 5ኛው ዓመት የሥራ ዘመን 8ኛው መደበኛ ስብሰባ ወ/ሮ ሃይማኖት ዘለቀ የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ሆነው እንዲሾሙ የቀረበለትን ረቂቅ መርምሮ በሙሉ ድምፅ አፅድቋል። ምክር ቤቱ ይህንን ውሳኔ ያሳለፈው የተሿሚዋን የረዥም ዘመን የሙያ ልምድና የሥራ ብቃት ከግምት ውስጥ በማስገባት መሆኑ ተመልክቷል። ወ/ሮ ሃይማኖት ዘለቀ በመገናኛ ብዙኃንና በኮሙኒኬሽን ዘርፍ ሰፊ ልምድ ያላቸው ባለሙያ ሲሆኑ በተለይም በኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ውስጥ ከሪፖርተርነት እስከ አርታኢነት በመሥራት ውጤታማ የሥራ ዘመን አሳልፈዋል። በተጨማሪም በኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን (ኢቢሲ) ውስጥ በሙያቸው ያገለገሉ ሲሆን በቀድሞው የመንግሥት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽሕፈት ቤትም በተለያዩ የኃላፊነት ደረጃዎች አገራቸውን አገልግለዋል። ወደ አሁኑ ከፍተኛ የኃላፊነት ቦታ ከመምጣታቸው በፊት በአዲስ…
Read More
ኢትዮጵያ የሰው ሠራሽ አስተውሎት (AI) ዩኒቨርሲቲ ልትገነባ መሆኑ ተገለጸ

ኢትዮጵያ የሰው ሠራሽ አስተውሎት (AI) ዩኒቨርሲቲ ልትገነባ መሆኑ ተገለጸ

ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ የሰው ሠራሽ አስተውሎት (AI) ዩኒቨርሲቲ ልትገነባ መሆኑንና ለዚህም የሚረዱ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች በሚቀጥሉት ስድስት ወራት ውስጥ እንደሚጠናቀቁ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ 75ኛ ዓመት የምሥረታ በዓልን ምክንያት በማድረግ ''የምሁራን ሚና ለሀገር ብልፅግና'' በሚል መሪ ሃሳብ በተካሄደ ውይይት ላይ እንደተናገሩት፤ በቴክኖሎጂው ዘርፍ መሽቀዳደም የግድ ይላል ብለዋል። አሁን ላይ በዓለማችን አንድ የሰው ሠራሽ አስተውሎት ዩኒቨርሲቲ ብቻ የሚገኝ ሲሆን፤ በኢትዮጵያ የሚገነባው ደግሞ የዓለማችን ሁለተኛው ይሆናል ማለታቸውንም ጋዜጣ ፕላስ ዘግቧል። ዩኒቨርሲቲው በቁጥር ጥቂት ነገር ግን ከፍተኛ ብቃት ያላቸውን 1 ሺህ ተመራቂዎች ለማፍራት ያለመ መሆኑን ዐቢይ (ዶ/ር) አስረድተዋል። እንደ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ገለጻ፤ ለሁሉም…
Read More
የቡና ግብይት ከኢትዮጵያ ምርት ገበያ ውጭ በስፋት እንደሚካሄድ ተገለጸ

የቡና ግብይት ከኢትዮጵያ ምርት ገበያ ውጭ በስፋት እንደሚካሄድ ተገለጸ

ለውጭ ገበያ የማይውሉ ና የተመለሱ ምርቶች ግብይት በኢትዮጵያ ምርት ገበያ ብቻ በኩል እንዲሸጡ አስገዳጅ አሰራር ቢዘረጋም ምርቶቹ መዳረሻቸዉ እየታወቀ አይደለም ተብሏል። ከዉጪ ገበያ የሚመለሱት ምርቶች ግብይት በኢትዮጵያ ምርት ገበያ አማካኝነት መሆን እንዳለበት ቢቀመጥም ይህ ተግባራዊ እየተደረገ እንዳልሆነ ተገልጿል። የፌደራል ዋና ኦዲተር እንዳስታወቀው ቡናን ጨምሮ ሁሉም ምርቶች መዳረሻቸዉ እየታወቀ አለመሆኑን ተናግሯል። በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት ወጪ አስተዳደር እና ቁጥጥር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በኢትዮጵያ ምርት ገበያ የምርት ቅበላ፣ ክምችት እና የግብይት ሥርዓት አፈፃፀምን በተመለከተ የተከናወነ የክዋኔ ኦዲት ሪፖርት ላይ ማብራሪያ ጠይቋል። ከዉጪ ገበያዉ የሚመለሰዉን እና የማይወለዉን ምርት የኢትዮጵያ ምርት ገበያ ሻጭ እና ገዥን የማገናኘት ሀላፊነት በግብይቱ ላይ እየታየ አይደለም ሲሉ የፌደራል ዋና ኦዲተር…
Read More
ህንጻዎች እና ቤቶች በጣሪያቸው ላይ የፀሀይ ሀይል ማመንጫ እንዲገጥሙ ሊገደዱ ነው

ህንጻዎች እና ቤቶች በጣሪያቸው ላይ የፀሀይ ሀይል ማመንጫ እንዲገጥሙ ሊገደዱ ነው

በሕንፃዎችና በቤቶች ውስጥ የፀሐይ ኃይል መጠቀምን አስገዳጅ የሚያደርግ የፖሊሲ ማዕቀፍ እየተዘጋጀ መሆኑ ተገልጿል። ኢትዮጵያ ያላትን የፀሐይ ኃይል በሙሉ አቅሟ ለመጠቀም የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን የውኃና ኢነርጂ ሚኒስቴር አስታውቋል። በሚኒስቴሩ የኢነርጂ ልማትና መረጃ መሪ ሥራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን ዳቢ፣ በሁሉም ሕንፃዎችና ቤቶች ውስጥ የፀሐይ ኃይል አጠቃቀምን በሒደት አስገዳጅ ለማድረግ የሚያስችል የፖሊሲ ማዕቀፍ እየተዘጋጀ መሆኑን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ያላትን የፀሐይ ኃይል አቅም የመለየትና በምን መልኩ ጥቅም ላይ መዋል እንደሚቻል የሚያሳዩ ጥናቶች መጠናቀቃቸውንም አስረድተዋል። ከሌሎች የዓለም ሀገራት ልምድ በመውሰድ፣ በተለይም በከተሞች ረዣዥም ሕንፃዎች ባሉባቸው አካባቢዎች በእያንዳንዱ ቤትና ሕንፃ ጣሪያ ላይ የፀሐይ ኃይል ቴክኖሎጂን በመግጠም፣ ኃይል የመሰብሰብና ጥቅም ላይ ለማዋል የሚያስችል የፖሊሲ ማዕቀፍ እየተዘጋጀ መሆኑን…
Read More