Italy

የአፍሪካ-ጣሊያን መሪዎች ጉባኤ ለመጀመሪያ ጊዜ በአዲስ አበባ መካሄድ ጀመረ

የአፍሪካ-ጣሊያን መሪዎች ጉባኤ ለመጀመሪያ ጊዜ በአዲስ አበባ መካሄድ ጀመረ

ሁለተኛው የአፍሪካ-ጣሊያን መሪዎች ጉባኤ ለመጀመሪያ ጊዜ ከጣሊያን ዋና ከተማ ሮም ውጭ በአፍሪካ ምድር በአዲስ አበባ አዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል ዛሬ መካሄድ ጀምሯል። ይህ ጉባኤ የጣሊያንና አፍሪካ ግንኙነት በአህጉራዊና በዓለም አቀፋዊ ትብብሮች ይበልጥ እንዲጠናከር የሚያደርግ ሲሆን፣ ኢትዮጵያም አህጉሪቱን ከተቀረው ዓለም ጋር ለማስተሳሰር ያላትን የዲፕሎማሲ አቅም በተግባር ያሳየችበት መድረክ ሆኗል። በጉባኤው ላይ የሀገራት መሪዎች እና የተባበሩት መንግሥታት ዋና ጸሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝን ጨምሮ የዓለም አቀፍ ተቋማት ኃላፊዎች ተገኝተዋል። ታሪካዊው ስብሰባ በፈረንጆቹ 2024 በሮም የቀረበውን የጣሊያን "የማቲ ዕቅድ" (Mattei Plan) አፈጻጸም የሚገመግም ሲሆን፣ በተለይም በሀይል ልማት፣ በግብርና፣ በትምህርት እና በጤና ዘርፎች ላይ ያተኮረ ሰፊ ምክክር ያደርጋል። የመንግሥት ኮምኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ደኤታ አቶ ተስፋሁን…
Read More
ጣልያን በኢትዮጵያ የባቡር መስመር ግንባታ ለማድረግ ተስማማች

ጣልያን በኢትዮጵያ የባቡር መስመር ግንባታ ለማድረግ ተስማማች

የጣልያን ባቡር ኮርፖሬሽን ከኢትዮጵያ ምድር ባቡር ኮርፖሬሽን ጋር የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርሟል። መንግሥት በሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት ምክንያት የተቋረጠውን የአዋሽ- ኮምቦልቻ እና ሐራ ገበያ የባቡር መስመርን ለማጠናቀቅ ከፍተኛ ቁርጠኝነት አለኝ ብሏል። የአዋሽ- ኮምቦልቻ እና ሐራ ገበያ  የባቡር መስመርን ለማጠናቀቅ ከፍተኛ የመንግስት ቁርጠኝነት ምኖሩን የኢትዮጵያ ምድር ባቡር ኮርፖሬሽን አስታወቀ። የኮርፖሬሽኑ የህግ አገልግሎት ሃላፊ አቶ ካሳሁን ሙላቱ እንደገልፁት ኮርፖሬሽኑ የባቡር ትራንስፖርት አገልግሎትን ለማጠናከር ከኮይፓ ኢጣሊያ ጋር ስምምነት አድርጓል። ስምምነቱ አዳዲስ የባቡር መስመሮችን መዘርጋትን እንዲሁም እየተገነቡ ያሉ የባቡር መስመሮችን በፍጥነት አጠናቆ ወደ ስራ ማስገባትን የሚያካትት ነው ብለዋል። ከዛም ባለፈ በጋራ ድርጅቶችን ማቋቋም እንዲሁም ትላልቅ ዎርክ ሾፖሽን ማሻሻል ጨምሮ በርካታ ስትራቴጂካዊ ስራዎች የሚሰራበት የጋራ ስምምነት መሆኑን…
Read More
ጣልያን ከኢትዮጵያ የዘረፈቻትን “ፀሀይ” የተሰኘች አውሮፕላንን መለሰች

ጣልያን ከኢትዮጵያ የዘረፈቻትን “ፀሀይ” የተሰኘች አውሮፕላንን መለሰች

በጣልያን-አፍሪካ መሪዎች ጉባኤ ላይ እየተሳተፉ ያሉት ጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ ይህችን አውሮፕላን መረከባቸውን ገልጸዋል። ጠቅላይ ሚንስትሩ እንዳሉት  "ፀሐይ" አውሮፕላንን ከጣልያን መንግሥት በይፋ መረከባቸውን አስታውቀዋል። የጣልያን ጠቅላይ ሚኒስትር ጂኦርጂያ ሜሎኔ ላለፈው አንድ አመት የአውሮፕላኑን መመለስ ስራ እንዳገዙም ተገልጿል። "ፀሐይ" እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር በ1935 ዓ.ም በጀርመናዊው ኢንጂነር እና የንጉሱ ፓይለት ሄር ሉድዊግ ዌበር ብሎም በወቅቱ በነበሩ ኢትዮጵያዊያን ባለሙያዎች ትብብር በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ መሰራቷ ይታወሳል። ጣልያን ኢትዮጵያ ቅኝ ለመግዛት ሁለት ጊዜ የሞከረች ቢሆንም የመጀመሪያው ሙከራ በ1880ዎቹ በኢትዮጵያዊያን አርበኞች ጥረት ሳይሳካ ቀርቷል፡፡  በኢትዮጵያዊያን አርበኞች የተባረረችው ጣልያን ሁለተኛውን የቅኝ ግዛት ሙከራዋን በ1927 ያደረገች ሲሆን ኢትዮጵያዊያን አርበኞች ከአምስት ዓመታት ብርቱ ትግል በኋላ ድል ተቀዳጅተዋል፡፡ ጣልየን በኢትዮጵያ…
Read More
ጣልያናዊው ጂያንሉጂ ቡፎን ጓንቱን ሰቀለ

ጣልያናዊው ጂያንሉጂ ቡፎን ጓንቱን ሰቀለ

ጣልያናዊው ጂያንሉጂ ቡፎን ጓንቱን ሰቀለ የጣልያን ብሔራዊ ቡድን እና ጁቬንቱስ ታሪካዊ ግብ ጠባቂ ጂያንሉጂ ቡፎን በ 45 ዓመቱ ከውድድር ራሱን እንዳገለለ አስታውቋል። ጂያንሉጂ ቡፎን በጣልያኑ ክለብ ጁቬንቱስ ቤት አስራ ሰባት አመታትን ያሳለፈ ሲሆን በክለቡ 685 ጨዋታዎች በማድረግ በክለቡ ታሪክ ብዙ ጨዋታ ያደረገ ሁለተኛው ተጨዋች ነው። ሀያ ስምንት አመታትን በተጨዋችነት ያሳለፈው የ45 ዓመቱ ጂያንሉጂ ቡፎን ከጣልያን ብሔራዊ ቡድን ጋር በ2006 የዓለም ዋንጫን አሸንፏል። ለጣልያን ብሔራዊ ቡድን 176 ጨዋታዎችን ያደረገው ቡፎን ለብሔራዊ ቡድኑ ብዙ ጨዋታዎችን በማድረግ ታሪካዊ ተጫዋች ነው። ተጫዋቹ ከጁቬንቱስ በተጨማሪ ወደ ፓሪስ በማቅናት በፒኤስጂ እግር ኳስ ክለብ ውስጥ ለአንድ ዓመት በግብ ጠባቂነት አገልግሏል።
Read More