Italy

ጣልያን ከኢትዮጵያ የዘረፈቻትን “ፀሀይ” የተሰኘች አውሮፕላንን መለሰች

ጣልያን ከኢትዮጵያ የዘረፈቻትን “ፀሀይ” የተሰኘች አውሮፕላንን መለሰች

በጣልያን-አፍሪካ መሪዎች ጉባኤ ላይ እየተሳተፉ ያሉት ጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ ይህችን አውሮፕላን መረከባቸውን ገልጸዋል። ጠቅላይ ሚንስትሩ እንዳሉት  "ፀሐይ" አውሮፕላንን ከጣልያን መንግሥት በይፋ መረከባቸውን አስታውቀዋል። የጣልያን ጠቅላይ ሚኒስትር ጂኦርጂያ ሜሎኔ ላለፈው አንድ አመት የአውሮፕላኑን መመለስ ስራ እንዳገዙም ተገልጿል። "ፀሐይ" እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር በ1935 ዓ.ም በጀርመናዊው ኢንጂነር እና የንጉሱ ፓይለት ሄር ሉድዊግ ዌበር ብሎም በወቅቱ በነበሩ ኢትዮጵያዊያን ባለሙያዎች ትብብር በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ መሰራቷ ይታወሳል። ጣልያን ኢትዮጵያ ቅኝ ለመግዛት ሁለት ጊዜ የሞከረች ቢሆንም የመጀመሪያው ሙከራ በ1880ዎቹ በኢትዮጵያዊያን አርበኞች ጥረት ሳይሳካ ቀርቷል፡፡  በኢትዮጵያዊያን አርበኞች የተባረረችው ጣልያን ሁለተኛውን የቅኝ ግዛት ሙከራዋን በ1927 ያደረገች ሲሆን ኢትዮጵያዊያን አርበኞች ከአምስት ዓመታት ብርቱ ትግል በኋላ ድል ተቀዳጅተዋል፡፡ ጣልየን በኢትዮጵያ…
Read More
ጣልያናዊው ጂያንሉጂ ቡፎን ጓንቱን ሰቀለ

ጣልያናዊው ጂያንሉጂ ቡፎን ጓንቱን ሰቀለ

ጣልያናዊው ጂያንሉጂ ቡፎን ጓንቱን ሰቀለ የጣልያን ብሔራዊ ቡድን እና ጁቬንቱስ ታሪካዊ ግብ ጠባቂ ጂያንሉጂ ቡፎን በ 45 ዓመቱ ከውድድር ራሱን እንዳገለለ አስታውቋል። ጂያንሉጂ ቡፎን በጣልያኑ ክለብ ጁቬንቱስ ቤት አስራ ሰባት አመታትን ያሳለፈ ሲሆን በክለቡ 685 ጨዋታዎች በማድረግ በክለቡ ታሪክ ብዙ ጨዋታ ያደረገ ሁለተኛው ተጨዋች ነው። ሀያ ስምንት አመታትን በተጨዋችነት ያሳለፈው የ45 ዓመቱ ጂያንሉጂ ቡፎን ከጣልያን ብሔራዊ ቡድን ጋር በ2006 የዓለም ዋንጫን አሸንፏል። ለጣልያን ብሔራዊ ቡድን 176 ጨዋታዎችን ያደረገው ቡፎን ለብሔራዊ ቡድኑ ብዙ ጨዋታዎችን በማድረግ ታሪካዊ ተጫዋች ነው። ተጫዋቹ ከጁቬንቱስ በተጨማሪ ወደ ፓሪስ በማቅናት በፒኤስጂ እግር ኳስ ክለብ ውስጥ ለአንድ ዓመት በግብ ጠባቂነት አገልግሏል።
Read More