ዜና

ኢትዮጵያ እና የተባበሩት አረብ ኤሜሬትስ በራሳቸው ገንዘብ ለመገበያየት ተስማሙ

ኢትዮጵያ እና የተባበሩት አረብ ኤሜሬትስ በራሳቸው ገንዘብ ለመገበያየት ተስማሙ

የሁለቱ ሀገራት ማእከላዊ ባንኮች ገንዘባቸው አሁን ባለው የመግዛት አቅም ልክ 46 ቢሊዮን ብር እና 3 ቢሊየን ድርሀም ለመቀያየር ተስማምተዋል፡፡ ኢትዮጵያ እና የተባበሩት አረብ ኤሜሬትስ በራሳቸው ገንዘብ ለመገበያየት የሚያስችላቸውን የመግባብያ ስምምነት በአዲስ አበባ ተፈራርመዋል፡፡ ሀገራቱ ከአሜሪካን ዶላር ባለፈ እርስ በእርስ በሚያደርጓቸው ግብይቶች ብር እና ድርሀምን ለመጠቀም ነው የተስማሙት፡፡ ስምምነቱን የኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ ገዢ ማሞ ምህረቱ እና የተባበሩት አረብ ኤሜሬትስ ማዕከላዊ ባንክ ገዢ ካሊድ ሞሃመድ ባላማ ተፈራርመዋል፡፡ ሀገራቱ በቀጣይ ዝርዝር አሰራሮች እና መመሪያዎች ላይ በጥልቀት የሚወያዩ ሲሆን ግብይቱን ለማሳለጥ ገንዘባቸው አሁን ባለው የመግዛት አቅም ልክ 46 ቢሊየን የኢትዮጵያ ብር እና 3 ቢሊየን የዩኤኢ ድርሀም በማከላዊ ባንኮቹ በኩል ለመቀያየር ተስማምተዋል፡፡ ስምምነቱ አዲስ አበባ…
Read More
ኢትዮጵያ የሶማሊላድ ወታደሮችን ማሰልጠን ጀመረች

ኢትዮጵያ የሶማሊላድ ወታደሮችን ማሰልጠን ጀመረች

በሺዎች የሚቆጠሩ የሶማሊላንድ ወታደሮች ለሥልጠና ወደ ኢትዮጵያ መግባታቸውን የራስ ገዟ መንግስታዊ ቴሌቪዥን ዘግቧል፡፡ የሶማሊያ ወጣቶችን የጫኑ በርካታ ታታ መኪኖች ሲያልፉ መመልከታቸውን የድሬዳዋ ነዋሪዎች ተናግረዋል። በሺዎች የሚቆጠሩ የሶማሊላንድ ወታደሮች ወታደራዊ ሥልጠና ለመውሰድ ከትናንት ማክሰኞ ሐምሌ 2 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ ወደ ኢትዮጵያ በመግባት ላይ መሆናቸውን ቢቢሲ ዘግቧል፡፡ በመንግሥት የሚተዳደረው የሶማሊላንድ ቴሌቪዥን ጣቢያ ለወታደራዊ ሥልጠና ወደ ኢትዮጵያ የሚጓዙ ናቸው ያላቸውን በሺዎች የሚቆጠሩ የሠራዊት አባላት በተሽከርካሪዎች ጉዞ ሲጀምሩ አሳይቷል። “የሶማሊላንድ ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ሜጀር ጄኔራል ኑህ እስማኢል ለሥልጠና የሚጓዙትን ሠልጣኞች ሸኝተዋል” ብሏል መንግሥታዊው የሶማሊላንድ ቴሌቪዥን ጣቢያ በዘገባው። ወታደራዊ ሥልጠናውን በተመለከተ ከኢትዮጵያ መንግሥት በኩል እስካሁን የተባለ ነገር የለም። ከራስ ገዟ ሶማሊላንድ በኩልም እንዲሁም የሠራዊት…
Read More
በኢትዮጵያ ፓስፖርት ቤት ለቤት ማደል ሊጀመር ነው ተባለ

በኢትዮጵያ ፓስፖርት ቤት ለቤት ማደል ሊጀመር ነው ተባለ

በኢትዮጵያ ባለፉት 12 ወራት ውስጥ ከአንድ ሚሊዮን በላይ ለሆኑ ሰዎች ፓስፖርት ተሰጥቷል ተብሏል የኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት ዓመታዊ አፈጻጸሙን አስመልክቶ መግለጫ ሰጥቷል፡፡ የኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ ሰላማዊት ዳዊት እንዳሉት በ2016 አመት 1 ነጥብ 1 ሚሊዮን ፓስፖርት ለአመልካቾ መሰጠቱን ተናግረዋል፡፡ ተቋሙ በታሪኩ ይህን መጠን ያለዉ ፓስፖርት ለአገልግሎት ፈላጊዎች ሲሰጥ የመጀመሪያዉ መሆኑን ዳይሬክተሯ ጠቅሰዋል። ይህ በዚህ እንዳለም ተቋሙ ከፓስፖርት እና ሌሎች አገልግሎት ክፍያዎች 14 ነጥብ 7 ቢሊዮን ብር ገቢ ማግኘቱንም ተናግረዋል። የኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት በህዝብ ተወካዮች ም/ቤት አባላት ጭምር ቅሬታ ሲቀርብበት ቢሰማም እንዲሁም ተገልጋዮች አሁንም ቅሬታ ማቅረባቸዉን ቢቀጥሉም ፤ ተቋሙ አሰራሮቼን እያስተካከልኩ እገኛለሁ ብሏል። ዋና ዳይሬክተሯ ፤ ከዚህ…
Read More
ኢትዮጵያ ስደተኞች ስራ እንዲቀጠሩ እና እንዲነግዱ ፈቀደች፡፡

ኢትዮጵያ ስደተኞች ስራ እንዲቀጠሩ እና እንዲነግዱ ፈቀደች፡፡

አንድ ሚሊዮን ገደማ ስደተኞችን እና ጥገኝነት ጠያቂዎችን ያስጠለለችው ኢትዮጵያ እውቅና ያገኙ ስደተኞች ስራ መቀጠር የሚያስችላቸውን መመሪያ ማዘጋጀቷን አስታውቃለች፡፡ የኢትዮጵያ ስደተኞች እና ተመላሾች አገልግሎት እንዳስታወቀው በ2011 ዓ/ም ወደ ኢትዮጵያ የገቡ ስደተኞች እና ጥገኝነት ጠያቂዎች ስራ መቀጠርን ጨምሮ ሌሎች ጥቅሞችን እንዲያገኙ የሚያደርገው ህግ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መጽደቁን አስታውቋል፡፡ ይህ አዋጅ የተደነገገውን ዕውቅና ያገኙ ስደተኞችንና ጥገኝነት ጠያቂዎችን እንዲሁም የተቀባይ ማህበረሰቦችን የኑሮ ሁኔታን ለማሻሻል እና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በሚል የተዘጋጀ ነውም ተብሏል፡፡ የስደተኞችና ተመላሾች አገልግሎትም የስደተኞችን የመስራት መብት ለማስፈፀም “ስደተኞች በስራ ላይ የሚሰማሩበትን ሁኔታ ለመወሰን መመሪያ አዘጋጅቶ እንደነበር አስታውቋል፡፡ መመሪያ ቁጥር 02/2012 በሚል የተዘጋጀው ይህ ሰነድም የስደተኞች ጉዳይ አዋጅ ቁጥር 1110/2010 የያዛቸውን መብቶች…
Read More
የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን በነዳጅ የሚሰሩ መኪኖች ላይ የተጣለውን እገዳ ተቃወመ

የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን በነዳጅ የሚሰሩ መኪኖች ላይ የተጣለውን እገዳ ተቃወመ

የኢንቨስትመንት ኮሚሽን፣ በነዳጅ የሚሠሩ ተሽከርካሪዎች ወደ አገር ውስጥ እንዳይገቡ መከልከል ባለሃብቶችንና የውጭ ኢንቨስትመንቶችን ይጎዳል በማለት ተቃውሟል፡፡ ኮሚሽኑ ለትራንስፖርት ሚንስቴር በጻፈው ደብዳቤ፣ የሕግ ድንጋጌ ሳይኖርና ግልጽ ሕግ ሳይወጣለት ከበላይ አካል በተሰጠ ትዕዛዝ ብቻ ነዳጅ የሚጠቀሙ ተሽከርካሪዎች እንዳይገቡ ማገድ አግባብነት የለውም በማለት ቅሬታውን እንደገለጠ ሪፖርተር ጋዜጣ ዘግቧል። በነዳጅ የሚሰሩ ተሽከርካሪዎች ወደ ሀገር ውስጥ እንዳይገቡ የተላለፈው ውሳኔ በግብርና፣ በግብርና ምርት ማቀነባበር፣ በአበባ እርሻ ልማት፣ በቱሪዝም፣ በማኑፋክቸሪንግና ግንባታ እና ሌሎች ስራዎች በተሠማሩ ባለሃብቶች እና ኩባንያዎች ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ መፍጠሩን ኮሚሽኑ አስታውቋል። ኮሚሽኑ አክሎም ለአንዳንድ ኢንቨስትመንት ስራዎች ከባሕሪያቸው አንጻር በነዳጅ የሚሠሩ ተሽከርካሪዎች እንዲያስገቡ እንዲፈቀድላቸው ሲል እንደጠየቀም ተገልጿል። ኢትዮጵያ ካሳለፍነው መጋቢት ወር ጀምሮ በነዳጅ የሚሰሩ መኪኖች…
Read More
ኢትዮጵያን ጨምሮ ከሶስት ሀገራት የተውጣጡ የጠፈር ሳይንስ ተማሪዎች ተመረቁ

ኢትዮጵያን ጨምሮ ከሶስት ሀገራት የተውጣጡ የጠፈር ሳይንስ ተማሪዎች ተመረቁ

ቦይንግ እና የወደፊቶቹ የአፍሪካ ጠፈር ተመራማሪዎች የሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ፣ ምህንድስና እና ሒሳብ አካዳሚ ወይም ፋሲሳ ከሶስት የአፍሪካ ሀገራ የተውጣጡ 300 ታዳጊዎችን በጠፈር ሳይንስ አሰልጥነው አስመርቀዋል፡፡ ለአምስት ወራት የተካሄደው ይህ ስልጠና ከኢትዮጵያ፣ ናይጀሪያ  እና ታንዛኒያ ከሚገኙ 63 ትምህርት ቤቶች የተውጣጡ ናቸው ተብሏል፡፡ በወደፊቶቹ የአፍሪካ ጠፈር ተመራማሪዎች የሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ፣ ምህንድስና እና ሒሳብ አካዳሚ (Future African Space Explorers STEM Academy፣ FASESA) እና Boeing [NYSE:BA] የተዘጋጀ አዲስ የትምህርት ንቅናቄ የሆነው የመጀመሪያው ወደ ጠፈር የሚወስዱ መንገዶች ፕሮግራም ስብስብ ሐምሌ 3 ቀን 2016 ዓ.ም በኢትዮጵያ ተመርቀዋል፡፡ ከአምስት ወራት መማር በኋላ በመላው ኢትዮጵያ፣ ናይጄሪያ እና ታንዛኒያ ከሚገኙ 63 ትምህርት ቤቶች የተውጣጡ 50% ሴት ልጆችን ጨምሮ 312 ተማሪዎች ለጠፈር…
Read More
ኢትዮጵያዊያኑ በሞሮኮ በተካሄደ የቴክኖሎጂ ውድድርን በአንደኝነት አጠናቀቁ

ኢትዮጵያዊያኑ በሞሮኮ በተካሄደ የቴክኖሎጂ ውድድርን በአንደኝነት አጠናቀቁ

የኢትዮጵያ ቡድን በሞሮኮ በተካሄደው የሁዋዌ ቴክ ፎር ጉድ ክፍለ አህጉራዊ ውድድርን በአንደኝነት አጠናቋል፡፡ የሁዋዌ ሲድስ ፎር ዘ ፊውቸር “Huawie Seeds for the Future 2024” የቴክኖሎጂ ስልጠና መርሃ ግብር በሞሮኮ (ኢሳዉራ) ከሰኔ 26 እስከ ሐምሌ 2 ቀን 2016 ዓ.ም ተካሂዷል። ይህ ስልጠና ከምስራቅ፣ ሰሜን፣ ምዕራብ እና መካከለኛው አፍሪካ የተውጣጡ 17 አገራትን አሳትፏል። ኢትዮጵያም ከስምንት ዩኒቨርሲቲዎች የተውጣጡ 10 ተማሪዎችን በስልጠናው ያሳተፈች ሲሆን ከእነዚህ ተማሪዎች መካከል 5 ተማሪዎችን የያዘው የኢትዮጵያ አንድ ቡድን በሁዋዌ ቴክፎርጉድ ክፍለ አህጉራዊ ውድድር አንደኛ በመሆን አሸንፏል፡፡ ተማሪዎቹ በቴክ ፎር ጉድ ክፍለ አህጉራዊ (ግሎባል) ፕሮጀክት ከመወዳደራቸው በፊት የተለያዩ የቴክኖሎጂ ስልጠናዎችን ወስደዋል። ተሳታፊ ተማሪዎቹ በ28 ቡድኖች ተከፋፍለው ለውድድር የሚሆኑ ፕሮጀክቶችን ያዘጋጁ…
Read More
ኢትዮ ቴሌኮም 94 ቢሊየን ብር ገቢ አገኘ

ኢትዮ ቴሌኮም 94 ቢሊየን ብር ገቢ አገኘ

የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ሥራ አስፈጻሚ ፍሬህይወት ታምሩ የበጀት ዓመቱን የሥራ አፈጻጸም በተመለከተ መግለጫ ሰጥተዋል። ኢትዮ ቴሌኮም በ2016 በጀት ዓመት 93 ነጥብ 7 ቢሊየን ብር ገቢ ማግኘቱን አስታውቋል። ከተገኘው ገቢ 39.9 በመቶ የድምጽ ፣ 21.7 የኢንተርኔት ፣10.2 የዓለም አቀፍ አገልግሎቶች ፣ 2.5 ከቴሌብር እና 1.5 ከኢንፍራስትራክቸር እንዲሁም 5 በመቶ የሚሆነው  ደግሞ ከዲቫይስ የተገኘ ገቢ መሆነም ተገልጿል ። በበጀት ዓመቱ የኩባንያው የደንበኞች ቁጥር 78 ነጥብ 3 ሚሊየን መድረሱን ገልጸው፤ በበጀት ዓመቱ 21 ነጥብ 79 ቢሊየን ብር የተጣራ ትርፍ ማግኘቱንም ተናግረዋል። ኩባንያው በውጭ ምንዛሬ ገቢ ከሚያገኝባቸው ምንጮች 198 ሚሊየን ዶላር ገቢ ማግኘቱን ገልጸዋል። ዋና ስራ አስፈጻሚዋ አክለውም በ2016 በጀት ዓመት ኢትዮ ቴሌኮም 30…
Read More
ኢትዮጵያ ከቡና ንግድ ከ1 ነጥብ 4 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ አገኘች

ኢትዮጵያ ከቡና ንግድ ከ1 ነጥብ 4 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ አገኘች

ኢትዮጵያ ወደ ውጭ ሀገራት ከተላከ የቡና ንግድ በታሪክ ከፍተኛ የተባለዉን ገቢ ማግኘቷን አስታውቃለች፡፡ ኢትዮጵያ ከቡና ወጪ ንግድ በዘንድሮው በጀት አመት ከአንድ ነጥብ 4 ቢሊዮን  ዶላር በላይ ገቢ ማግኘቷን የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታውቋል። የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ዶክተር አዱኛ ደበላ እንደገለፁት ኢትዮጵያ በ2016 በጀት አመት ከቡና ሽያጭ በመጠንም ሆነ በገቢ ከፍተኛ የሆነ ውጤት አስመዝግባለች ብለዋል። ኢትዮጵያ በተያዘው በጀት ዓመት 298 ሺህ 500  ቶን ቡና ለውጪ ገበያ አቅርባ 1 ነጥብ 43 ቢሊዮን ዶላር ገቢ አግኝታለች። ይህም ካለፈው አመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር በመጠንም ሆነ በገቢ ደረጃ ከፍተኛ ውጤት የተመዘገበበት እንደሆነ ዋና ዳይሬክተሩ  ጨምረው ገልፀዋል። የተላከው የቡና መጠን በ20 በመቶ እንዲሁም በዋጋ ደረጃም…
Read More
አሜሪካ በአማራ እና ኦሮሚያ ተማሪዎችን እና ንጹሃን ዜጎችን ማገት እንዲቆም ጠየቀች

አሜሪካ በአማራ እና ኦሮሚያ ተማሪዎችን እና ንጹሃን ዜጎችን ማገት እንዲቆም ጠየቀች

ባሳለፍነው ሳምንት ከደባርቅ ዩንቨርሲቲ ተነስተው ወደ ቤተሰቦቻቸው በመጓዝ ላይ የነበሩ ተማሪዎች መታገታቸው ይታወሳል፡፡ እገታው የተፈጸመው ለአዲስ አበባ ከተማ ትንሽ ሲቀራቸው በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ገብረ ጉራቻ ከተማ አቅራቢያ በታጣቂዎች እንደሆነ በወቅቱ ተገልጾም ነበር፡፡ የፌደራል መንግስትም ሆነ የኦሮሚያ ክልል መንግስት እስካሁን ስለ ጉዳዩ በይፋ እስካሁን ያሉት ነገር ባይኖርም የታጋች ተማሪዎች ቤተሰቦች ግን ልጆቻቸው በታጣቂዎች እንደታገቱባቸው ለተለያዩ ብዙሃን መገናኛዎች ተናግረዋል፡፡ በኢትዮጵያ የአሜሪካ ኢምባሲ በጉዳዩ ዙሪያ በወጣው መግለጫ በአማራ እና ኦሮሚያ ክልሎች የተራዘሙ ግጭቶች የህግ የበላይነት እንዳይከበር ምክንያት ሆነዋል ሲል በማህበራዊ ትስስር ገጾቹ ላይ ገልጿል፡፡ ባሳለፍነው ሳምንት እና ከዚህ በፊት የተፈጸሙ ተከታታይ እገታዎች ወንጀለኞችን እንዳይጠየቁ ማድረጉን በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር አረቪን ማሲንጋ መናገራቸውን…
Read More