11
Jul
አንድ ሚሊዮን ገደማ ስደተኞችን እና ጥገኝነት ጠያቂዎችን ያስጠለለችው ኢትዮጵያ እውቅና ያገኙ ስደተኞች ስራ መቀጠር የሚያስችላቸውን መመሪያ ማዘጋጀቷን አስታውቃለች፡፡ የኢትዮጵያ ስደተኞች እና ተመላሾች አገልግሎት እንዳስታወቀው በ2011 ዓ/ም ወደ ኢትዮጵያ የገቡ ስደተኞች እና ጥገኝነት ጠያቂዎች ስራ መቀጠርን ጨምሮ ሌሎች ጥቅሞችን እንዲያገኙ የሚያደርገው ህግ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መጽደቁን አስታውቋል፡፡ ይህ አዋጅ የተደነገገውን ዕውቅና ያገኙ ስደተኞችንና ጥገኝነት ጠያቂዎችን እንዲሁም የተቀባይ ማህበረሰቦችን የኑሮ ሁኔታን ለማሻሻል እና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በሚል የተዘጋጀ ነውም ተብሏል፡፡ የስደተኞችና ተመላሾች አገልግሎትም የስደተኞችን የመስራት መብት ለማስፈፀም “ስደተኞች በስራ ላይ የሚሰማሩበትን ሁኔታ ለመወሰን መመሪያ አዘጋጅቶ እንደነበር አስታውቋል፡፡ መመሪያ ቁጥር 02/2012 በሚል የተዘጋጀው ይህ ሰነድም የስደተኞች ጉዳይ አዋጅ ቁጥር 1110/2010 የያዛቸውን መብቶች…