ዜና

ኢትዮጲያ ከ34 አመት በኋላ ያለ ወርቅ ሻምፒወናዉን አጠናቀቀች

ኢትዮጲያ ከ34 አመት በኋላ ያለ ወርቅ ሻምፒወናዉን አጠናቀቀች

በጃፖን ቶኪዮ አስተናጋጅነት ሲካሄድ  የቆየዉ  የአለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ኢትዮጲያ በታሪክ ለሁለተኛ ጊዜ ያለ ምንም ወርቅ አጠናቃለች። ኢትዮጲያ በዚህ መድረክ በታሪክ ከ34 አመት በኅላ አንድም ወርቅ ሳታገኝ ያጠናቀቀችበት የአለም ሻምፒዮና ሆኖ ተመዝግቧል። በውድድሩ የመጨረሻ ቀናት በተደረገዉ የ5000 ሜትር የወንዶች ፍፃሜ ዉድድር ምን አልባት ወርቅ ይገኝበታል ተብሎ ቢጠበቅም ኢትዮጵያ ሜዳሊያ  ዉስጥ መግባት ሳትችል ቀርታለች። ኢትዮጲያን የወከሉት አትሌት ሀጎስ ገብረ ሂወት እና አትሌት ቢኒያም መሀሪ ዉድድራቸዉን 5ኛ እና 13ኛ  ደረጃን ይዘዉ አጠናቀዋል። ኢትዮጲያ እስካሁን ባደረገቻቸዉ ስምንት የፍፃሜ ዉድድሮች ሁለት ብር እና ሁለት ነሀስ ስታገኝ በድምሩ አራት ሜዳሊያዎችን ብቻ ሰብስባ በታሪኳ በእጅጉ ደካማ የሆነዉን የቶኪዮ አለም ሻምፒዮና ቆይታዋን ደምድማለች። አሜሪካ በውድድሩ 16 የወርቅ ሜዳሊያ…
Read More
አምስት የፖለቲካ ፓርቲዎች ብልጽግና ፓርቲን ለማሸነፍ ህብረት ፈጠሩ

አምስት የፖለቲካ ፓርቲዎች ብልጽግና ፓርቲን ለማሸነፍ ህብረት ፈጠሩ

ፓርቲዎቹ "ትብብር ለኢትዮጵያ አንድነት" የተሰኘ የቅንጅት ፖርቲ መመስረታቸውን ገልጸዋል። ላለፉት ሥስት ዓመታት በትብብር በጋራ ሲሠሩ የቆዩት አምስት የፖለቲካ ድርጅቶች ቅንጅት መመሥረታቸውን በዛሬው ዕለት አስታውቀዋል። የቅንጅቱ ስያሜም "ትብብር ለኢትዮጵያ አንድነት" መሆኑን በዛሬው የመስራች ጉባኤ ላይ ተገልጿል። የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ)፣ እናት ፖርቲ ፣የኢትዮጵያ ሕዝቦች አብዮታዊ ፖርቲ (ኢሕአፓ)፣ አንድ ኢትዮጵያ ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ እና አማራ ግዮናዊ ንቅናቄ ናቸው ቅንጅት መመሥረታቸውን አስታውቀዋል። ቅንጅቱንም እንዲመሩ የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ) ፕሬዝዳንት አቶ አብርሀም ጌጡ ተመርጠዋል። "ለእናት ፖርቲ ትልቅ ቀን ነው" ያሉት የፖርቲው ፕሬዝዳንት ሰይፈስላሴ አያሌው (ዶ/ር)፤ "ኢትዮጵያ 50 ዓመታት የተበታተነ የፖለቲካ ጎራ መከራ እየወረደበት ላለው ፖለቲካ መፍትሄ የሚሰጥ ቅንጅት ነው" ሲሉ ተናግረዋል። በተናጥል የሚመጣ…
Read More
ከተሽከርካሪዎች የሚወጣ በካይ ጋዝ የሚቆጣጠር መመሪያ ተዘጋጀ

ከተሽከርካሪዎች የሚወጣ በካይ ጋዝ የሚቆጣጠር መመሪያ ተዘጋጀ

‎በኢትዮጵያ ደረጃዎች ኢኒስቲትዩት የተዘጋጀው፤ ከተሽከርካሪዎች የሚወጣን ጎጂ የካይ ጋዝ ልቀት ለመቆጣጠር የሚያገለግለው አስገዳጅ መመሪያ ከመስከረም 30 ቀን 2018 ጀምሮ ተግባራዊ እንደሚደረግ የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ አስታውቋል። ዋነኛ ዓላማው የትራንስፖርት ዘርፉ ለበካይ ጋዝ ልቀት የሁለት ሦስተኛ ድርሻ ያለው በመሆኑ በጎጂ በካይ ጋዞች ምክንያት የሚከሰትን የአየር ብክለት መቀነስ ሲሆን፤ አዲሱ መመሪያ ሙሉ ለሙሉ ሲተገበር ተሽከርካሪዎች ወደ አየር የሚለቁትን የበካይ ጋዝ መጠን የሚቆጣጠር መሳሪያ እንዲገጥሙ ይገደዳሉ ተብሏል። የተቋሙ የትራንስፖርት ዘርፍ የአየር ንብረት ክትትል እና ቁጥጥር ቡድን መሪ አቶ ግርማ ሳሙኤል፤ የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ መመሪያው ከጸደቀበት መጋቢት 2017 ጀምሮ ውይይቶች ሲካሄዱበት እንደነበርም ተናግረዋል። በዚህም አስገዳጅ መመሪያው ከጸደቀ በኋላ ከታክሲ ማኅበራት፣ ከክልል ከተማ አስተዳደሮች…
Read More
ኢትዮጵያ ኢንተርኔትን በመዝጋት ከአፍሪካ ቀዳሚዋ ሀገር ተባለች

ኢትዮጵያ ኢንተርኔትን በመዝጋት ከአፍሪካ ቀዳሚዋ ሀገር ተባለች

ኢትዮጵያ ኢንተርኔትን በተደጋጋሚ በመዝጋትና የኢንተርኔትን ነጸነት በመገደብ ከአፍሪካ በአንደኛ ደረጃ ላይ መቀመጧን በብሉምስበሪ አሳታሚ ላይ የታተመ አንድ የጥናት መጽሐፍ አመላከተ። “የኢንተርኔት መዘጋት በአፍሪካ” በሚል ርእስ በፊሊሽያ አንቶኒዮ እና ቶኒ ሮበርትስ የተጠናውና መቀመጫውን በብሪታንያ ባደረገው ብሉምስበሪ አሳታሚ ድርጅት ላይ በመጸሐፍ መልክ ታትሞ የወጣው ጥናት በአውሮፓውያኑ አቆጣጠር ከ2016 እስከ 2024 በአህጉረ አፍሪካ በሀገራት የተፈጸመውን የኢንተርኔት መዘጋት ገምግሟል። በዚህም በአውሮፓውያኑ አቆጣጠር ከ2016 እስከ 2024 ባሉት በለፉት ዘጠኝ ዓመታት 193 የኢንተርኔት መዘጋት በአፍሪካ አህጉር መመዝገቡን ገልጿል። በተጠቀሱት ዘጠኝ ዓመታት ውስጥ በተፈጸሙ የኢንተርኔት መዘጋት ድግግሞሽ መጠኖች ሀገራትን በደረጃ ያስቀመጠው ጥናቱ ኢትዮጵያን በእነዚህ ዓመታት ውስጥ ሰላሳ ጊዜ ኢንትርኔት የዘጋች በሚል ከ55ቱ የአፍሪካ ሀገራት በአንደኛ ደረጃ አስቀምጧታል።…
Read More
ጣልያን በኢትዮጵያ የባቡር መስመር ግንባታ ለማድረግ ተስማማች

ጣልያን በኢትዮጵያ የባቡር መስመር ግንባታ ለማድረግ ተስማማች

የጣልያን ባቡር ኮርፖሬሽን ከኢትዮጵያ ምድር ባቡር ኮርፖሬሽን ጋር የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርሟል። መንግሥት በሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት ምክንያት የተቋረጠውን የአዋሽ- ኮምቦልቻ እና ሐራ ገበያ የባቡር መስመርን ለማጠናቀቅ ከፍተኛ ቁርጠኝነት አለኝ ብሏል። የአዋሽ- ኮምቦልቻ እና ሐራ ገበያ  የባቡር መስመርን ለማጠናቀቅ ከፍተኛ የመንግስት ቁርጠኝነት ምኖሩን የኢትዮጵያ ምድር ባቡር ኮርፖሬሽን አስታወቀ። የኮርፖሬሽኑ የህግ አገልግሎት ሃላፊ አቶ ካሳሁን ሙላቱ እንደገልፁት ኮርፖሬሽኑ የባቡር ትራንስፖርት አገልግሎትን ለማጠናከር ከኮይፓ ኢጣሊያ ጋር ስምምነት አድርጓል። ስምምነቱ አዳዲስ የባቡር መስመሮችን መዘርጋትን እንዲሁም እየተገነቡ ያሉ የባቡር መስመሮችን በፍጥነት አጠናቆ ወደ ስራ ማስገባትን የሚያካትት ነው ብለዋል። ከዛም ባለፈ በጋራ ድርጅቶችን ማቋቋም እንዲሁም ትላልቅ ዎርክ ሾፖሽን ማሻሻል ጨምሮ በርካታ ስትራቴጂካዊ ስራዎች የሚሰራበት የጋራ ስምምነት መሆኑን…
Read More
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ተጫዋቹ ከነዓን ማርክነህ የኦማን ክለብን ተቀላቀለ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ተጫዋቹ ከነዓን ማርክነህ የኦማን ክለብን ተቀላቀለ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ወይም (ዋልያዎቹ) የፊት መስመር እና የመሐል ሜዳ ተጫዋች ከንአን ማርክነህ ወደ አዲስ ክለብ ለማምራት መስማማቱ ተገልጿ። ከንአን ማርከነ በአዲሱ የውድድር ዘመን ወደ ኦማን ሊግ በማቅናት አል ሸባብ ክለብ ለመጫወት ከስምምነት መድረሱ ታውቋል። ከብሔራዊ ቡድን ጨዋታ መልስ ወደ ኦማን ያቀናው ከንአን ማርክነህ በትላንትናው ዕለት የህክምና ምርመራውን በተሳካ ሁኔታ አልፏል። ከንአን ከህክምና ምርመራ በኃላ በክለቡ የሚያቆየውን የአንድ አመት ኮንትራት ሲፈራረም ክለቡ በዛሬው ዕለት ይፋ አድርጎታል። ከንአን ያለፈውን የውድድር ዓመት በሊቢያ ሊግ ስኬታማ ጊዜን ሲያሳልፍ ለአል መዲና እና ሸባብ አል ጋሂር እግር ኳስ ክለቦች መጫወቱ ይታወሳል። ከንአን ማርከነ በሊቢያ ቆይታው በ14 ጨዋታዎች ስድስት ጎሎችን አስቆጥሯል። የከንአን አዲሱ ክለብ አል ሸባብ…
Read More
ከዘንድሮው የ12ኛ ክፍል ተፈታኞች ውስጥ 91 በመቶዎቹ መውደቃቸው ተገለጸ

ከዘንድሮው የ12ኛ ክፍል ተፈታኞች ውስጥ 91 በመቶዎቹ መውደቃቸው ተገለጸ

በ2017 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ከተፈተኑ 586 ሺህ ተማሪዎች ውስጥ ያለፉት 49 ሺህ ገደማ ህሉ ብቻ ናቸው ተብሏል። በ2017 የትምህርት ዘመን የተሰጠው የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና ከወሰዱ 585 ሺህ 882 ተማሪዎች መካከል 48 ሺህ 929 ማለፋቸውን የትምህርት ሚኒስትር አስታውቋል። የትምህርት ሚኒስትር ፕሮፌሰር ብርሀኑ ነጋ የፈተና ውጤቱን አስመልክተው በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ እንደገለፁት ፈተና ከወሰዱ 585 ሺህ 882 ተማሪዎች መካከል 48 ሺህ 929 ከ50 በመቶ በላይ ያስመዘገቡ በመሆናቸው ወደ ዩንቨርስቲ ይገባሉ ብለዋል። ፈተናቸውን ከወሰዱ አጠቃላይ ተማሪዎች መካከል 50 በመቶ እና ከዚያ በላይ ውጤት ካስመዘገቡ የማኅበራዊ ሳይንስ ተፈታኞች 5.2 በመቶ፣ ተፈጥሮ ሳይንስ ተፈታኞች ደግሞ 11.4 በመቶ መሆናቸውንም ሚኒስትሩ ጠቅሰዋል። እንደ ፕሮፌሰሩ ገለፃ በዘንድሮው ዓመት…
Read More
ኢትዮጵያዊቷ እመቤት መሀባው ለምርምር ወደሕዋ እንድትጓዝ ተመረጠች

ኢትዮጵያዊቷ እመቤት መሀባው ለምርምር ወደሕዋ እንድትጓዝ ተመረጠች

በአሜሪካ ሀገር የሚገነውና በሕዋ ሳይንስ ምርምር ላይ የሚሰራው 'ታይታንስ ስፔስ ኢንዱስትሪ' በ2029 ወደጠፈር ለሚያደርገው ጉዞ ኢትዮጵያዊቷን እመቤት መሀባውን ከተጓዥ ተመራማሪዎች መካከል አንዷ እንድትሆን መርጧታል፡፡ እመቤት መሀባው ከልጅነቷ አንስቶ ለሕዋ ሳይንስ ፍቅር እንደነበራት የተገለጸች ሲሆን፤ በአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ትምህርቷን እየተከታተለች ሳለ በሕዋ ሳይንስ የትምህርት ዘርፍ ስኮላርሺፕ አግኝታ ወደሕንድ አቅንታለች። በኋላም አሜሪካ ውስጥ በሕዋ ሳይንስ ምርምር ላይ የሚሰራውን ታይታንስ ስፔስ ኢንዱስትሪን መቀላቀሏን ተከትሎ፤ በተቋሙ በኤሮስፔስ ኢንጂነርነት ሙያዋ የተለያዩ የምርምር ሥራዎችን እያከናወነች ይገኛል። የምትሰራበት የሕዋ ምርምር ተቋም በእ.አ.አ. በ2029 ወደጠፈር ለሚያደርገው ጉዞ እመቤት መሀባውን ከተጓዥ ተመራማሪዎች መካከል አንዷ እንድትሆን መርጧታል። ለዚህ ምርጫ የተለያዩ መስፈርቶች ቢኖሩትም፤ ግዳጁን ለመፈፀም በአካል፣ በስነልቦናም ሆነ በምርምር…
Read More
ኢትዮጵያ ታላቁ የህዳሴ ግድብን አስመረቀች

ኢትዮጵያ ታላቁ የህዳሴ ግድብን አስመረቀች

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የኬንያው ፕሬዚዳንት ውሊያም ሩቶ፣ የሶማሊያው ፕሬዚዳንት ሀሰን ሼክ መሀመድ፣ የጅቡቲው ፕሬዚዳንት እስማኢል ኦማር ጊሌ፣ የደቡብ ሱዳኑ ፕሬዚዳንት ሳልቫኪር በተገኙበት የዓባይ ግድብ መርቀዋል። የኢትዮጵያ የዓባይ ግድብ የምረቃ ሥነስርዓት ዛሬ ጳጉሜ 4 ቀን 2017 ዓም ሲካሄድ የክልል ርዕሰ መስተዳድሮች፣ ሚኒስትሮችና ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት፣ ከፍተኛ የጦር መኮንኖችና የክብር እንግዶች ተገኝተዋል። የዓባይ ግድብ ተገንብቶ እስከሚጠናቀቅ 233 ቢሊዮን ብር ወጪ የተደገ ሲሆን፤ ቦንድ በመግዛት፤ ስጦታ በመስጠት እና በሌሎች መንገዶች ህዝብ ትልቅ ተሳትፎ እንዳደረገ በስፋት ተግልጿል፡፡ ከአምስት ቢሊዮን ዶላር በላይ ወጪ የተደረገበት የህዳሴ ግድቡ መጠናቀቅም የኢትዮጵያን አቅም በሁሉም ዘርፍ የሚያሳግ እንደሆነም የተለያዩ ባለሙያዎች ይናገራሉ፡፡ ዓባይ ግድብ የሚገኘው በቤኔሻንጉል ጉሙዝ ክልል ጉባ…
Read More
በሕገ ወጥ የወርቅ እና የገንዘብ ዝውውር 76 ተጠርጣሪዎች መያዛቸው ተገለጸ

በሕገ ወጥ የወርቅ እና የገንዘብ ዝውውር 76 ተጠርጣሪዎች መያዛቸው ተገለጸ

በሕገ ወጥ የወርቅ፣ የገንዘብና የጦር መሣሪያ ዝውውር ተሳትፈዋል የተባሉ 76 ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር ማዋሉን የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት አስታውቋል፡፡ ፋና እንደዘገበው ከሆነ በተጠቀሱት የወንጀል ድርጊቶች ተሰማርተው በነበሩ የውጭ ሀገር ዜጎችና ኢትዮጵያውያን ላይ አዲስ አበባ ከተማን ጨምሮ በቤንሻንጉል ጉሙዝ፣ ጋምቤላ፣ ኦሮሚያ፣ አማራ፣ ሲዳማ እና ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልሎች ክትትል ሲደረግ ቆይቷል ተብሏል፡፡ ተጠርጣሪዎቹ የወርቅ ማዕድን በሕገ ወጥ መንገድ በማምረት፣ በመሰወርና በማዘዋወር፣ የሀገራችንን ጨምሮ የተለያዩ ሀገራት ገንዘቦችን እንዲሁም ሕገወጥ የጦር መሣሪያዎችን በማዘዋወር ወንጀሎች ላይ ተሳታፊ እንደነበሩ መግለጫው ጠቁሟል፡፡ አገልግሎት መሥሪያ ቤቱ ከኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስና ከየክልሎቹ የፀጥታ አካላት ጋር በመቀናጀት ባካሄደው ልዩ ኦፕሬሽን እስካሁን 45 የውጪ ሀገር ዜጎች እና 31 የሀገር ውስጥ በድምሩ…
Read More