Spacescience

ኢትዮጵያዊቷ እመቤት መሀባው ለምርምር ወደሕዋ እንድትጓዝ ተመረጠች

ኢትዮጵያዊቷ እመቤት መሀባው ለምርምር ወደሕዋ እንድትጓዝ ተመረጠች

በአሜሪካ ሀገር የሚገነውና በሕዋ ሳይንስ ምርምር ላይ የሚሰራው 'ታይታንስ ስፔስ ኢንዱስትሪ' በ2029 ወደጠፈር ለሚያደርገው ጉዞ ኢትዮጵያዊቷን እመቤት መሀባውን ከተጓዥ ተመራማሪዎች መካከል አንዷ እንድትሆን መርጧታል፡፡ እመቤት መሀባው ከልጅነቷ አንስቶ ለሕዋ ሳይንስ ፍቅር እንደነበራት የተገለጸች ሲሆን፤ በአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ትምህርቷን እየተከታተለች ሳለ በሕዋ ሳይንስ የትምህርት ዘርፍ ስኮላርሺፕ አግኝታ ወደሕንድ አቅንታለች። በኋላም አሜሪካ ውስጥ በሕዋ ሳይንስ ምርምር ላይ የሚሰራውን ታይታንስ ስፔስ ኢንዱስትሪን መቀላቀሏን ተከትሎ፤ በተቋሙ በኤሮስፔስ ኢንጂነርነት ሙያዋ የተለያዩ የምርምር ሥራዎችን እያከናወነች ይገኛል። የምትሰራበት የሕዋ ምርምር ተቋም በእ.አ.አ. በ2029 ወደጠፈር ለሚያደርገው ጉዞ እመቤት መሀባውን ከተጓዥ ተመራማሪዎች መካከል አንዷ እንድትሆን መርጧታል። ለዚህ ምርጫ የተለያዩ መስፈርቶች ቢኖሩትም፤ ግዳጁን ለመፈፀም በአካል፣ በስነልቦናም ሆነ በምርምር…
Read More
በጉና ተራራ ላይ የህዋ ማዕከል የመገንባት እቅድ እንዳለ ተገለጸ

በጉና ተራራ ላይ የህዋ ማዕከል የመገንባት እቅድ እንዳለ ተገለጸ

የደብረታቦር ዩኒቨርሲቲ በአፄ ቴውድሮስ የተሰየመች ሮኬት ለኹለተኛ ጊዜ ማስወንጨፉ ይታወሳል። ዩንቨርሲቲው በከተማዋ አቅራቢ በሚገኘው የጉና ተራራ ላይ የህዋ ምርምር ማዕከል ለመገንባት እቅድ መያዙን ገልጿል። 154ኛውን የአፄ ቴዎድሮስ ዝክረ-ሰማዕት መታሰቢያ በዓል አስመልክቶ የደብረታቦር ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂ ትምህርት ዘርፍ በአካባቢያቸው ባለ ቁሳቁስ ከ 2 ኪ.ሜትር በላይ መወንጨፍ የቻለች ሮኬት ለመጀመሪያ ጊዜ ከአንድ ዓመት በፊት አስወንጭፏል። ዩንቨርሲቲው በዚህ ዓመትም በተሻለ መልኩ ማስወንጨፍ መቻላቸውን ዩንቨርሲቲው ገልጿል። የደብረታቦር ዩኒቨርሲቲ ረዳት ፕሮፌሰር አዲሱ ወርቁ እንዳሉት በ2014 የተሰሩት ሮኬትና መድፍ  ዋና አላማ የአጼ ቴዎድሮስን የመቅደላ መድፍን ለመድገምና ኢትዮጽያ ውስጥ የተሳካለት ሮኬትና መድፍ መስራት መቻል እንደሆነ ተናግረዋል።  ሚያዚያ 2014 በሮኬት ሳይንስ ማዕከል አሞራ ገደል ተብሎ በሚጠራ አካባቢ የተወነጨፈችው ሮኬት የት…
Read More