06
Sep
ለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ 233 ቢልዮን ብር ወጪ መደረጉን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አስታወቀ። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ምርቃትን አስመልክቶ ለመገናኛ ብዙሃን ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቷል። የተቋሙ የኮርፖሬት የኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ሞገስ መኮንን እንደተናገሩት ለህዳሴ ግድብ ግንባታ በአጠቃለይ 233 ቢልዮን ብር ወጪ ተደርጓል። ከዚህ ውስጥ 223 ቢልዮን ወይም 91 በመቶ የሚሆነው ወጪ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የተገኘ ነው ብለዋል። ከመላው ኢትዮጵያዊያን በቦንድ ግዢ 18 ነጥብ 9 ቢልዮን ብር የተሰበሰበ ሲሆን፤ በውጭ ከሚኖሩ ኢትዮጵያዊያንና ትውልደ ኢትዮጵያዊያን 1 ነጥብ 6 ቢልዮን ብር መሰብሰቡንም አቶ ሞገስ አብራርተዋል። እንዲሁም 3 ነጥብ 2 ቢልዮን ብር በስጦታ የተገኘ መሆኑን አንስተዋል። ላለፉት 14 ዓመት በግንባታ ላይ…