ኢኮኖሚ

ኢትዮጵያ አዲስ የክሪፕቶ ማይኒንግ የኤሌክትሪክ ኃይል ስምምነት እንደማታፀድቅ ገለጸች

ኢትዮጵያ አዲስ የክሪፕቶ ማይኒንግ የኤሌክትሪክ ኃይል ስምምነት እንደማታፀድቅ ገለጸች

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ አሸብር እንደገለጹት ጥያቄውን ለማስተናግድ የኤሌክትሪክ አቅርቦታችን አቅም ማሳደግ እንደሚጠበቅ ገልፀው ይሄን አሁን ባለው አቅም ማስተናገድ እንደማይቻል ተናግረዋል። በኢትዮጵያ ባለው ዝቅተኛ የታሪፍ ዋጋ እና የኃይል ኃብት በመሳብ 25 ኩባንያዎች የቢትኮይን ማዕድን ቁፋሮ ስራ የጀመሩ ሲሆን፣ 20 የሚሆኑ ኩባንያዎች ደግሞ ፈቃድ ለማግኘት በዝርዝር ተመዝግበው እየጠበቁ ናቸው። ኩባንያው ገቢውን ለማስፋት በማሰብ፣ “ተጨማሪ ኃይል” ብሎ የሰየመውን ጥቅም ላይ ሳይውል የቀረ የኤሌክትሪክ ኃይልን ለክሪፕቶ ማዕድን አውጪ ድርጅቶች በውጭ ምንዛሬ መሸጥ ጀምሮ ነበር። ይህ በዚህ እንዳለ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከኤሌክትሪክ ሽያጭ 75.4 ቢሊየን ብር ገቢ ማግኘቱን አስታውቋል። የተቋሙ ዋና ስራ አስፈጻሚ ኢንጅነር አሸብር ባልቻ  እንደገለጹት በበጀት ዓመቱ 25.18 ቴራ…
Read More
ከአዲስ አበባ ናይሮቢ የአውቶቡስ ትራንስፖርት ተጀመረ

ከአዲስ አበባ ናይሮቢ የአውቶቡስ ትራንስፖርት ተጀመረ

አቢሲኒያ ሌግዠሪ ኮች የተሰኘ የትራንስፖርት አገልግሎት አቅራቢ ድርጅት ከኬንያ ዋና ከተማ ናይሮቢ ወደ አዲስ አበባ በአውቶብስ ተጓዦችን ማመላለስ መጀመሩን አስታውቋል። ድርጅቱ ባለፈው ሳምንት እሁድ በይፋ አገልግሎት መስጠት መጀመሩን የድርጅቱ ዳይሬክተር ሚካኤል ጄምስ ማቺዮ ለቢቢሲ ተናግረዋል። "በአንድ ጉዞ 7 ሺህ 500 የኬንያ ሽልንግ ነው የምናስከፍለው። ለደርሶ መልስ ጉዞ ዋጋ 15 ሺህ የኬንያ ሽልንግ ወይም 16 ሺህ ብር ገደማ ያስከፍላል ተብሏል። ከኛ በፊት 'ሮያል አላይድ' የተሰኘ ከናይሮቢ ሞያሌ እና ሞምባሳ የሕዝብ ማመላለሻ ትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የተሰማራ ድርጅት አለ። ከአራት ዓመታት በፊት የተመሠረተው 'ሮያል አላይድ' እስከ ሞያሌ ከተማ ብቻ ይሠራ ነበር። በአውሮፕላን ቲኬት መወደድ ሳቢያ የአውቶብስ ትራንስፖርት ፍላጎት መኖሩን እና ይህንን ፍላጎት ሊያሟላ…
Read More
ኢትዮጵያ ለጎረቤት ሀገራት ከሸጠችው ኤሌክትሪክ ከ118 ሚሊየን ዶላር በላይ ገቢ ማግኘቷ ተገለጸ

ኢትዮጵያ ለጎረቤት ሀገራት ከሸጠችው ኤሌክትሪክ ከ118 ሚሊየን ዶላር በላይ ገቢ ማግኘቷ ተገለጸ

በተጠናቀቀው 2017 በጀት ዓመት ኢትዮጵያ ለጎረቤት ሀገራት ካቀረበችው የኤሌክትሪክ ኃይል ሽያጭ 118 ነጥብ 1 ሚሊየን ዶላር ገቢ ማግኘቷን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አስታውቋል፡፡ የተቋሙ የኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር ሞገስ መኮንን፤ ኢትዮጵያ በቀጣናው ያላትን የኤሌክትሪክ ሃይል ትስስር ይበልጥ ለማጠናከር በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ አሁን ላይም ኢትዮጵያ ለኬንያ፣ ጅቡቲ፣ ሱዳንና ታንዛኒያ የኤሌክትሪክ ኃይል እየሸጠች እንደምትገኝ አብራርተዋል፡፡ በ2017 በጀት ዓመት 25 ሺሕ በላይ ጊጋ ዋት ሰዓት የኤሌክትሪክ ኃይል ለማመንጨት ታቅዶ 29 ሺሕ በላይ ጊጋ ዋት ሰዓት ማመንጨት መቻሉን ተናግረዋል፡፡ ከተመረተው ኃይል ውስጥም ለኬንያ 85 ነጥብ 2 ሚሊየን ዶላር የኤሌክትሪክ ሃይል ሽያጭ ለማከናወን ታቅዶ 86 ነጥብ 3 ሚሊየን ዶላር መገኘቱን ጠቅሰዋል፡፡ እንዲሁም ለጅቡቲና ሱዳን ከቀረበ የኤሌክትሪክ ሃይል…
Read More
የኢትዮጵያ አየር መንገድ የ28 ሚሊዮን ዶላር ኪሳራ እንደደረሰበት ገለጸ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ የ28 ሚሊዮን ዶላር ኪሳራ እንደደረሰበት ገለጸ

ኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን ጣሰው በተቋሙ የበጀት አመት አፈጻጸም ዙሪያ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል። ዋና ስራ አስፈጻሚው ሪፖርቱን ባቀረቡበት ወቅት ጥያቄዎች ተነስተውላቸው ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል። ከነዚህም ጥያቄዎች መካከል ከበረራ ትኬቶች ውድነት ጋር እና አየር መንገዱ በኤርትራ ከተያዘበት ገንዘብ ጋር የተያያዙ ጥያቄዎች ሲሆን ዋና ስራ አስፈጻሚው ምላሽ ሰጥተውበታል። ከሀገር ውስጥ በረራ ጋር በተያያዘ የ28 ሚሊዮን ዶላር ኪሳራ እንዳጋጠማቸው ስራ አስፈጻሚው ተናግረዋል። "የዓለም አቀፍ በረራዎች ትኬት ኮምፒውተር ውስጥ በዶላር ነው የተጻፈው ሰው ትኬት ሲገዛ በእለታዊ የዶላር ምንዛሬ ተመን ነው ይህንን ምንም ልናደርግ አንችልም። የሃገር ውስጥ በረራ ግን በብር ነው የተጻፈው ባለፈው አመት የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው ወቅት አልጨመርንም የዶላር…
Read More
አሜሪካ በኢትዮጵያ ላይ የጣለችውን የ10 በመቶ ታሪፍ አጸናች

አሜሪካ በኢትዮጵያ ላይ የጣለችውን የ10 በመቶ ታሪፍ አጸናች

በተሻሻለው የትራምፕ ታሪፍ ኢትዮጵያ  ቀድሞ በተጣለባት ዝቅተኛው 10 ፐርሰንት ታሪፍ እንድትቀጥል ተደርጓል የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ለአሥርተ ዓመታት የቆዩትን የዓለም ንግድ አሠራሮች ለመለወጥ በሚያደርጉት ጥረት ከሰባ በላይ አገራት ላይ አዲስና የተቀየረ የንግድ ቀረጥ ተግባራዊ ሊያደርጉ መሆኑን አስታወቀዋል። ኢትዮጵያ በአሜሪካ የተጣለባትን የ10 በመቶ ታሪፍ የተቀበለች ሲሆን ታሪፉ የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት እንደሚያሳድግላት አስታውቃለች። ትናንት በተፈረመው የአስፈጻሚ ትዕዛዝ መሰረት፣ ፕሬዝዳንት ትራምፕ የአገሪቱን የንግድ ጉድለት ከዋነኛ አጋሮች ጋር ለመቀነስ ታስቦ የተደረገ ነው በማለት የገለፁ ሲሆን፣ በዚህም እስከ 41 በመቶ የሚደርስ አዲስ የገቢ ምርቶች ላይ የሚጣል ታሪፍን ተፈፃሚ አድርገዋል። በካናዳ ምርቶች ላይ የተጣለው የንግድ ቀረጥ ወደ 35 በመቶ ከፍ ማለቱ ቀድሞውንም የተወጠረው የንግድ ግንኙነት ይበልጥ…
Read More
ቱርክ የኢትዮጵያ ሁለተኛዋ የንግድ እና ኢንቨስትመንት አጋር ሆነች

ቱርክ የኢትዮጵያ ሁለተኛዋ የንግድ እና ኢንቨስትመንት አጋር ሆነች

የኢትዮጵያና የቱርክ የንግድና የኢንቨስትመንት ግንኙነትን የሚያጠናከር የቢዝነስ ኮንፈረንስ እና ኤግዚቢሽን በአዲስ አበባ እየተካሄደ ነው። በቱርኩ የአለም አቀፍ የኢንዱስትሪ ትብብር ፎረም/ World Cooperation of Industries Forum-WCI Forum/ / እና በአዲስ አበባ ንግድና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት አማካኝነት የተሰናዳው ስምንተኛው የ ደብሊው ሲአይ / WCI የቢዝነስ ፎረም ዛሬ ተጀምሯል፡ ፡ በንግድ ፎረሙ ላይ የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር  ዘለቀ ተመስገን፤ የአዲስ አበባ ንግድና የዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት/ አዲስ ቻምበር/ ፕሬዚዳንት  ዘሀራ መሀመድ፤ የዲፕሎማቲክ እና የንግዱ ማህበረሰብ እና  ሌሎች ጥሪ ተደረገላቸው እንግዶች ታድመዋል፡ ፡ በመድረኩ ላይ መልእክታቸውን ያስተላለፉት የአዲስ ቻምበር ዋና ፀሀፊ መሰረት ሞላ የኢትዮጵያ እና የቱርክ አመታዊ የንግድ ልውውጥ መጠን እ.አ.አ በ2023 ከ…
Read More
ኢትዮጵያ በአሜሪካ ታሪፍ ምክንያት አማራጭ የቡና መዳረሻ እየፈለገች መሆኗን ገለጸች

ኢትዮጵያ በአሜሪካ ታሪፍ ምክንያት አማራጭ የቡና መዳረሻ እየፈለገች መሆኗን ገለጸች

የፕሬዝዳንት ትራምፕ አስተዳድር ኢትዮጵያን ጨምሮ በብዙ የዓለማችን ሀገራት ላይ አዲስ ታሪፍ መጣላቸው ይታወሳል። አዲሱ ታሪፍ ኢትዮጵያ ወደ ውጭ ከምትልከው ጠቅላላ ምርት ላይ የ35 በመቶ ገቢ እንዲቀንስ የሚያደርግ እንደሆነ ተገልጿል። የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለሥልጣን ምክትል ዳይሬክተር ሻፊ ዑመር የአሜሪካ አስተዳደር ፖሊሲ ከሀገሪቱ የወጪ ንግድ ገቢ 35 በመቶ የሚሆነውን የሚነካ ነው ብለዋል። በዚህ ምክንያትም ከአሜሪካ ባለፈ አማራጭ የውጭ ገበያዎችን በመመልከት ላይ መሆናቸውንም ሻፊ ተናግረዋል። ይህንን ተከትሎም የኢትዮጵያን ቡና ወደ ሩቅ ምስራቅ እና መካከለኛው ምስራቅ ሀገራት የማስፋት እቅድ ተይዟል ተብሏል። በተያዘው በጀት ዓመት ውስጥም 20 አዳዲስ የቡና ወጪ ንግድ መዳረሻዎችን የመክፈት እቅድ እንደተያዘም ተገልጿል። እንዲሁም ዋነኛ የኢትዮጵያ ቡና ገዢ ወደ ሆኑት ቻይና፣ ጃፓን፣…
Read More
መንግስት ከግምጃ ሰነድ ግዢዎች 173 ቢሊዮን ብር እንደሚሰበስብ ገለጸ

መንግስት ከግምጃ ሰነድ ግዢዎች 173 ቢሊዮን ብር እንደሚሰበስብ ገለጸ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ፣ የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለስልጣን፣ የሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ማዕከላዊ ግምጃ ቤት ሰነዶች ሽያጭን በይፋ አስጀምረዋል። የገንዘብ ሚንስቴር ሚኒስትር አህመድ ሽዴ በዚህ ጊዜ እንዳሉት መንግስት ለመጀመሪያ ጊዜ የግምጃ ቤት ሰነዶችን ለገበያ ማቅረቡን ተናግረዋል፡፡ በ2018 በጀት ዓመት ውስጥ መንግስት ከበጀተው 1.9 ትርሊዮን ብር ውስጥ 188 ቢሊዮን ብር የበጀት ጉድለት እንዳለበት ሚኒስትሩ ገልጸዋል፡፡ ከገጠመው የበጀት ጉድለት ውስጥም 173 ቢሊዮን ብሩን ግምጃ ቤት ሰነድ ለሽያጭ በማቅረብ ለመሰብሰብ መታቀዱንም አቶ አህመድ ተናግረዋል፡፡ የሀገር ውስጥ ብድሩ ከሰነድ ገዢዎች የሚሰበሰበው የዋጋ ግሽበትን በማያባብስና የማክሮ ኢኮኖሚውን በማያናጋ መልኩ እንደሚሆንም ገልጸው ነባር የግምጃ ሰነዶችን ወደ ኤሌክትሮኒክስ መንገድ ስራዎች እየተቀየሩ መሆኑን፣ አዳዲስ ግምጃ ሰነዶችም በዚህ መልኩ ለገበያ ይቀርባሉም…
Read More
ቻይና የኢትዮጵያን አኩሪ አተር ወደ ሀገሯ እንዲገባ ፈቀደች

ቻይና የኢትዮጵያን አኩሪ አተር ወደ ሀገሯ እንዲገባ ፈቀደች

የቻይና ጉምሩክ ባወጣው መግለጫ መሠረት፣ ቻይና ከአሜሪካ ጋር እየተካረረ የመጣውን የንግድ ውጥረት ተከትሎ የፕሮቲን አቅርቦቶቿን ለማስፋት ባላት ፍላጎት ከኢትዮጵያ የሚገቡ የአኩሪ አተር ምርቶችን እንዲገቡ ፈቃድ መስጠቷን ኒውስ ሴንትራል ዘግቧል። የኢትዮጵያ አኩሪ አተር ከባለፈው ሳምንት ጀምሮ ወደ ቻይና እንዲገቡ ተፈቅደዋል። ቻይና ለአገር ውስጥ የአኩሪ አተር ምርት በአብዛኛው በአኩሪ አተር ምርቶች ከብራዚል እና ከአሜሪካ ታስመጣለች። ቻይና በሰኔ ወር ከኡራጓይ የሚገቡ የአኩሪ አተር ምርቶች እንዲገቡ ፈቅዳለች፤ ኢትዮጵያ ደግሞ አሁን  ሩሲያ፣ ቤላሩስ፣ አርጀንቲና እና ብራዚልን ጨምሮ እውቅና የተሰጣቸውን የአቅራቢዎች ዝርዝርን  ተቀላቅላለች። ቻይና የኢትዮጵያ ቁጥር አንድ የንግድና ኢንቨስትመንት አጋር ስትሆን ዓመታዊ የንግድ ልውውጥ መጠን ከአራት ቢሊዮን ዶላር በላይ ደርሷል። ኢትዮጵያ በተለይም ባለፉት ሶስት ዓመታት ውስጥ…
Read More
ብሔራዊ ባንክ በባንኮች ላይ የጣለውን አስገዳጅ የቦንድ ግዥ አነሳ

ብሔራዊ ባንክ በባንኮች ላይ የጣለውን አስገዳጅ የቦንድ ግዥ አነሳ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የገንዘብ ፖሊሲ ኮሚቴ በሁሉም ንግድ ባንኮች ላይ የተጣለው አስገዳጅ የቦንድ ግዥ እንዲነሳ መወሰኑን ገልጿል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ባወጣው መግለጫ እንዳስታወቀው የገንዘብ ፖሊሲ ኮሚቴው ባደረገው ውይይት የተለያዩ ውሳኔዎችን አሳልፏል። ከእነዚህም ውስጥ አንዱ ሁሉም ንግድ ባንኮች የረጅም ጊዜ የግምጃ ቤት ቦንድ (Treasury Bond) እንዲገዙ የሚያስገድደው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ መመሪያ (MFAD/TRBO/001/2022) እንዲነሳ ያሳለፈው ወሳኔ ተጠቃሽ ነው። "አሁን ላይ የመንግሥት ገቢ የማሰባሰብ አቅም በእጅጉ በመሻሻሉ፣ እንዲሁም መንግሥት የበጀት ጉድለቱን ለሟሟላት የውጭና ገበያ መር የሆኑ የሀገር ውስጥ የመበደሪያ አማራጮችን እየተጠቀመ በመሆኑ በባንኮች ላይ ተጥሎ የቆየውን ይህ አስገዳጅ መመሪያ አሁን ላይ ማንሣቱ ተገቢ መሆኑን ኮሚቴው አምኖበታል" ሲል መግለጫው ጠቅሷል። ኮሚቴው ያመነበት ይህ የገንዘብ…
Read More