wto

ኢትዮጵያ ከ18 ሀገራት ጋር የንግድ ድርድር ጀመረች

ኢትዮጵያ ከ18 ሀገራት ጋር የንግድ ድርድር ጀመረች

ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት (WTO) አባልነት ድርድር ሂደት 6ኛው የሥራ ቡድን ስብሰባ ላይ፤ በሁለትዮሽ ንግድ ድርድር ዙሪያ 18 ሀገራት ጋር ድርድር ማድረግ መጀመሯን ንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡ የዓለም ንግድ ድርጅት 6ኛ የሥራ ቡድን ስብሰባ ባለፈው ሳምንት በስዊዘርላንድ ጄኔቫ መካሄዱ ይታወሳል። ይህ ስብሰባ ኢትዮጵያ የድርጅቱን አባልነት ጥያቄ ባቀረበች ከ20 ዓመታት በላይ ሂደት ውስጥ ወሳኝ ምዕራፍ የተመዘገበበት እንደነበር ሚኒስቴሩ ገልጿል። የድርድሩ ቡድን መሪ፣ ዋና ተደራዳሪ እና የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) የድርድር ሂደቱን አስመልክቶ፤ ለጋዜጠኞች መግለጫ ሰጥተዋል። በመግለጫቸውም ኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባል እንድትሆን እና ከተለያዩ ሀገራት ጋር ያለው የንግድ ትስስር እንድታጎለብት ለማድረግ ብርቱ ሥራ ሲሰራ መቆየቱን አስታውሰዋል፡፡ ከዚህ…
Read More
ኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅትን ለመቀላቀል አዲስ ተደራዳሪ ቡድን አዋቀረች

ኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅትን ለመቀላቀል አዲስ ተደራዳሪ ቡድን አዋቀረች

የዓለም ንግድ ድርጅት የአባልነት ድርድርን እና ቀጣናዊ የንግድ ትስስሮችን የሚመራ ብሔራዊ ኮሚቴ በአዲስ መልክ መቋቋሙን የንግድ እና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡ ኮሚቴው ከሚመለከታቸው የመንግስት ተቋማት ከፍተኛ አመራሮችን እንዲሁም ባለሙያዎችን ያካተተ ነው ተብሏል። ኢትዮጵያ የአለም ንግድ ድርጅት አባል ለመሆን በተለያዩ ጊዜያት ፍላጎቷን ብታሳይም ከአባል አገራት ለሚነሱ አንዳንድ የንግድ ዘርፍ አካታችነት አዎንታዊ ምላሽ መስጠት ባለመቻሏ ድርጅቱን መቀላቀል ሳትችል ቆይታለች። የጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ መንግስት ከአምስት ዓመት በፊት ወደ ስልጣን ሲመጣ የዓለም ንግድን በአባልነት መቀላቀል እንደሚፈልግ በይፋ ጥያቄ አቅርቧል፡፡ መንግስት ከወሰዳቸው ስር ነቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያዎች እና አዳዲስ ለውጦች መካከል አገሪቱን በ2021 የአለም ንግድ ድርጅት አባል ማድረግ ይገኝበታል። በዚህም ከ2020 አንስቶ ድርድር እንደ አዲስ…
Read More