ኢኮኖሚ

ኢትዮጵያ የኦጋዴን የተፈጥሮ ጋዝ ወደ ውጭ የመላክ እቅዷን ሰረዘች

ኢትዮጵያ የኦጋዴን የተፈጥሮ ጋዝ ወደ ውጭ የመላክ እቅዷን ሰረዘች

መንግስት  ከኦጋዴን ተፋሰስ የተፈጥሮ ጋዝ በጅቡቲ በኩል በቧንቧ መስመር ወደ ውጭ የመላክ እቅዱን የገንዘብ እጥረትና የትግበራ መጓተትን በመጥቀስ በይፋ ሰርዟል። በኢትዮጵያ ኢነርጂ አውትሉክ 2025 የተረጋገጠው ይህ ስረዛ፣ በሀገራዊ የኢነርጂ ፖሊሲ ውስጥ ትልቅ ለውጥ የሚያሳይ ሲሆን፣ ከውጭ የመላክ ፍላጎት ወደ ሀገር ውስጥ አጠቃቀም እየተሸጋገረ መሆኑን ያመለክታል ሲል ሪፖርተር ጋዜጣ ዘግቧል። “የኢትዮጵያ መንግስት በኦጋዴን ክልል የታቀደውን የተፈጥሮ ጋዝ ማውጣት እና የተፈጥሮ ጋዝ ወደ ውጭ ለመላክ ወደ ጅቡቲ የሚዘረጋውን የቧንቧ መስመር ፕሮጀክት ሰርዟል” ሲል ሪፖርቱ ይገልጻል። በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር፣ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ፣ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት እና በነዳጅና ኢነርጂ ባለስልጣን በጋራ የተዘጋጀው የኢነርጂ አውትሉክ “የፕሮጀክት ፋይናንስን በማግኘት ረገድ ያሉ ችግሮች እና የፕሮጀክት ትግበራ…
Read More
ኢትዮጵያ ፕሬዝዳንት ትራምፕ በህዳሴው ግድብ ዙሪያ የሰጡትን አስተያየት ውድቅ አደረገች

ኢትዮጵያ ፕሬዝዳንት ትራምፕ በህዳሴው ግድብ ዙሪያ የሰጡትን አስተያየት ውድቅ አደረገች

ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ባሳለፍነው ሳምንት ሀገራቸው አሜሪካ ለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የገንዘብ ድጋፍ ማድረጓን ተናግረዋል። የታላቁ ህዳሴ ግድብ ህዝባዊ ማስተባበሪያ ጽህፈት ቤት የፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕን አስተያየት ውድቅ አድርጓል። የጽህፈት ቤቱ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አረጋዊ በርሔ ፕሬዝዳንቱ ቱርዝ ሶሻል ተብሎ በሚጠራው የማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ዩናይትድ ስቴትስ የህዳሴ ግድብን በገንዘብ ደግፋለች ማለታቸውን "መሠረተ ቢስ" ብለውታል። ኃላፊው "ህዳሴ ግድብ ከ20ዐ3 ዓ.ም ጀምሮ በኢትዮጵያ ሕዝብ ሀብት፣ ጉልበት፣ እውቀትና በኢትዮጵያ መንግሥት የገንዘብ ድጋፍ እየተገነባ ያለ ነው” ሲሉ አፅዕኖት ሰጥተዋል። አክለውም የአሜሪካው መሪ ንግግር ከዓለም አቀፋ ፖለቲካ ጋር የተያያዘ እንደሆነም ተናግረዋል። ከ15 ዓመት በፊት ለግንባታው መሰረት ድንጋይ ሲጣል 80 ቢሊዮን ብር ያስፈልገዋል ተብሎ የተጀመረው የታላቁ ህዳሴ…
Read More
በኢትዮጵያ የውጭ ባንኮች እንዲሰሩ ተፈቀደ

በኢትዮጵያ የውጭ ባንኮች እንዲሰሩ ተፈቀደ

የኢትዮጵያ የባንክ ዘርፍ ከዛሬ ጀምሮ ለውጭ ባለሀብቶች ክፍት ሆነ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የሀገሪቱን የባንክ ዘርፍ ለውጭ ተሳትፎ ክፍት የሚያደርግ አዲስ መመሪያን ዛሬ ይፋ አድርጓል። ይህ እርምጃ የኢትዮጵያን የፋይናንስ ዘርፍ ለውጭ ኢንቨስትመንት ክፍት ለማድረግ ሲደረግ የቆየው ጥረት የመጨረሻው ምዕራፍ ተደርጎ እንደሚወሰዱ ተገልጿል። መመሪያ ቁጥር SBB/94/2025 ባለፉት አንድ ዓመት በተለያዩ ባለድርሻ አካላት በተደረጉ ሰፊ ውይይቶች እና ምክክሮች ግብዓት ተደርጎበት የተዘጋጀ መሆኑ ታውቋል። ይህ መመሪያ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በፀደቀው የባንክ ሥራ አዋጅ መሰረት የወጣ ሲሆን፣ የሚያስፈልገውን የሕግ ማዕቀፍ ማሟላቱ ተገልጿል። ይህ አዲሱ የፈቃድ አሰጣጥ መመሪያ ለመጀመሪያ ጊዜ የውጭ ባለሀብቶች፣ ባንኮችን እና ሌሎች ስትራቴጂካዊ ባለሀብቶችን ጨምሮ፣ በኢትዮጵያ የባንክ ሥርዓት ውስጥ እንዲሳተፉ ያስችላል ተብሏል። ብሔራዊ…
Read More
የመንግስት ተቋማት ስራ ለለቀቁና ለሞቱ ሰራተኞች ከ400 ሺህ በላይ ብር ደመወዝ ከፍለዋል ተባለ

የመንግስት ተቋማት ስራ ለለቀቁና ለሞቱ ሰራተኞች ከ400 ሺህ በላይ ብር ደመወዝ ከፍለዋል ተባለ

የፌደራል ዋና ኦዲተር የመንግስት ተቋማት የ2016 በጀት ዓመት የበጀት ኦዲት አፈጻጸም ሪፖርት ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አቅርቧል፡፡ ዋና ኦዲተር በሪፖርቱ ላይ እንደጠቀሰው 17 የመንግስት ተቋማት በጡረታ፣ በሞትና በሌሎች ምክንያት ከሥራ ለለቀቁ ሰራተኞች 408,462 ብር ያላግባብ ደመወዝ ከፍለው ተገኝተዋል ተብሏል፡፡ የሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ከግንቦት 30 ቀን 2014 ዓ.ም ጀምሮ በልዩ ሁኔታ ካልተፈቀደ  በስተቀር የሰራተኞች ቅጥር፣ የደረጃ ዕድገትና ዝውውር እንዳይፈጸም ቢከለክልም በስምንት መስሪያ ቤቶችና በአንድ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት በጠቅላላው 24,073,003 ብር የሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽንን ሳያስፈቅዱ በቋሚ የሥራ መደቦች ላይ ሰራተኞችን በኮንትራት በመቅጠር ክፍያ ፈጽመዋልም ተብሏል፡፡ ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽንን ሳያስፈቅዱ የኮንትራት ቅጥር ከፈጸሙት ተቋማት መካከል የቅደስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሊኒየም ህክምና ኮሌጅ፣ ሃሮማያ ዩኒቨርሲቲ፣…
Read More
ኢትዮጵያ ከሁለት ወር በኋላ ነዳጅ ለገበያ እንደምታቀርብ ተገለጸ

ኢትዮጵያ ከሁለት ወር በኋላ ነዳጅ ለገበያ እንደምታቀርብ ተገለጸ

ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ከቀጣዩ መስከረም ወር ጀምሮ በታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ ነዳጅ ለገበያ እንደምታቀርብ መናገራቸውን ኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 ዘግቧል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በኢትዮጵያ ካሉ የሚዲያ ባለሙያዎች ጋር ውይይት አድርገዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዚህ ጊዜ እንዳሉት ከመስከረም ወር ጀምሮ ነዳጇን ለገበያ ማቅረብ እንደምትጀምር ገልጸዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከሰባት ዓመት በፊት ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ በታሪክ ነዳጅ ማውጣት ጀመረች በሚል ለኢትዮጵያዊያን የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት ማስተላለፋቸው ይታወሳል፡፡ ይሁንና ይህ ከሆነ ከሰባት ዓመት በኋላ ኢትዮጵያ ነዳጅ ለገበያ እንደምታቀርብ ተናግረዋል፡፡ ኢትዮጵያ በሶማሊ ክልል ኦጋዴን አካባቢ ከፍተኛ መጠን ያለው ነዳጅ እንዳላት በተደጋጋሚ ሲገለጽ የቆየ ሲሆን የቻይና ፖሊሲጂኤል ኩባንያ ነዳጅ ለማውጣት በሂደት ላይ ነበር፡፡ ኢትዮጵያ የነዳጅ ፍላጎቷን ሙሉ ለሙሉ…
Read More
ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ የማህበራዊ ትስስር ኩባንያዎች ቢሯቸውን በአዲስ አበባ እንዲከፍቱ ጠየቀች

ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ የማህበራዊ ትስስር ኩባንያዎች ቢሯቸውን በአዲስ አበባ እንዲከፍቱ ጠየቀች

የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን እንደ ሜታ (ፌሰቡክ) ያሉ የማኅበራዊ ትስስር አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ቅርጫንፍ ቢሮዎቻቸውን በኢትዮጵያ እንዲከፍቱ ጠይቋል፡፡ ባለሥልጣኑ በበይነ መረብ የሚካሄዱ የጥላቻ ንግግችን የሚመለከት የአንድ ዓመት ሪፖርቱን የተመለከተ መግለጫ ለመገናኛ ብዙኃን ሰጥቷል። የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን "እንደ ፌስቡክ ያሉ ድርጅቶች ከፍተኛ ተጠቃሚ ባለው ኢትዮጵያ ለማስታወቂያ ገቢ እያስገኙ አይደለም" ብሏል። ኢትዮጵያ ከ44 ሚሊዮን በላይ የበይነ ተጠቃሚዎች ያሉባት ሀገር ብትሆንም፤ እስካሁን ድረስ የማኅበራዊ ሚዲያ ፖለሲም ሆነ አዋጅ የላትም። ባለሥልጣኑ ለሦስተኛ ግዜ እንዳዘጋጀው በተገለጸው ሪፖርት ላይ፤ የጥላቻ ንግግር ከምንጊዜውም በላይ በበይነ መረብ አማካኝነት መስፋፋቱን ያሳያል ብሏል። ከጥር 2016 ዓ.ም. እስከ ጥር 2017 ዓ.ም. ያለውን የአንድ ዓመት ሪፖርት መቅረቡን ለመገናኛ ብዙኃን የገለጹት መግለጫውን…
Read More
ኢትዮጵያ ለእዳ ክፍያ 463 ቢሊዮን ብር መመደቧ ተገለጸ

ኢትዮጵያ ለእዳ ክፍያ 463 ቢሊዮን ብር መመደቧ ተገለጸ

የገንዘብ ሚንስትር አሕመድ ሽዴ፣ ለ2018 በጀት ዓመት 1 ነጥብ 93 ትሪሊዮን ብር ወይም 14 ቢሊዮን ዶላር ረቂቅ የፌደራል በጀት ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አቅርበዋል። ረቂቅ በጀቱ እየተጠናቀቀ ካለው በጀት ዓመት ጋር ሲነጻጸር የ31 በመቶ ብልጫ ያለው ነው። ከቀረበው ረቂቅ በጀቱ ውስጥ 1 ነጥብ 2 ትሪሊዮኑ ለመደበኛ ወጪ፣ 415 ቢሊዮኑ ለካፒታል ወጪ፣ 315 ቢሊዮኑ ለክልሎች ድጎማና 14 ቢሊዮኑ ለክልሎች የዘላቂ ልማት ግቦች ማስፈጸሚያ እንዲውል መመደቡን ሚንስትሩ አብራርተዋል። ከጥቅል አገራዊ ምርት አንጻር 2 ነጥብ 2 በመቶ ያልተጣራ የበጀት ጉድለት ያጋጥማል ተብሎ እንደሚጠበቅና ኾኖም መንግሥት ጉድለቱን ለመሙላት ከብሄራዊ ባንክ ብድር እንደማይበደር ተገልጧል። ይህ በዚህ እንዳለ መንግስት ከያዘው በጀት አንድ ሶስተኛውን ለእዳ ክፍያ መያዙ…
Read More
በኢትዮጵያ በቡና ላኪነት ለመሰማራት 15 ሚሊዮን ብር ካፒታል ማስያዝ ግዴታ ሆነ

በኢትዮጵያ በቡና ላኪነት ለመሰማራት 15 ሚሊዮን ብር ካፒታል ማስያዝ ግዴታ ሆነ

ከዚህ ቀደም የቡና ላኪነትን የብቃት ማረጋገጫ ለማግኘት ይጠየቅ የነረበው የ1.5 ሚሊዮን ብር በ10 እጥፍ እንዲያድግ የተደረገው ዘርፉ በእውቀትና የተሻለ አቅም ባላቸው ሰዎች እንዲያዝ በማስፈለጉ ነው ተብሏል፡፡ ከዚህ ቀደም በቡና ላኪነት የብቃት ማረጋገጫ ለማግኘት ይጠየቅ የነበረው ካፒታል 1.5 ሚሊየን ብር ነበር፤ ይህ ገንዘብ አሁን በአስር እጥፍ እንዲያግ በኢትዮጵያ ቡና ሻይ ባለስልጣን ማሻሻያ መቅረቡ ተሰምቷል። የሚጠየቀው ካፒታል አነስተኛ ሆኖ በመቆየቱ አትራፊ ነው በሚል ብቻ ብዙዎች የሚገቡበት ዘርፍ ሆኖ ቆይቷል የሚሉት የኢትዮጵያ ቡና ማህበር ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ግዛት ወርቁ ናቸው። ይሄ ደግሞ እዚሁ ሀገር ቤት በአቅራቢ እና ላኪዎች እንዲሁም ላኪዎች እና የውጭ ገዥዎች መካከል ችግሮች እንዲፈጠሩ ሲያደርግ መቆየቱን ተናግረዋል።  የቡና_ንግድ ሰዎች የተወሰነ…
Read More
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከ14 ሚሊዮን በላይ መንገደኞች ማጓጓዙን ገለጸ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከ14 ሚሊዮን በላይ መንገደኞች ማጓጓዙን ገለጸ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ባለፉት 9 ወራት 14.5 ሚሊዮን መንገደኞችን ማጓጓዙን አስታውቋል፡፡ ይህም ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲመሳከር የ13 በመቶ እድገት እንዳለው ዋና ስራ አስፈፃሚው መስፍን ጣሰው ተናግረዋል፡፡ አየር መንገዱ በዘጠኝ ወር ውስጥ ያገኘው ገቢ 5.6 ቢሊዮን ዶላር መሆኑንን የተናገሩት አቶ መስፍን ጣሰው ገቢውም ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲተያይ የ8 በመቶ ብልጫ አሳይቷል ብለዋል፡፡ በጊዜ ማዕቀፍ 10 አዳዲስ አውሮፕላኖች የኢትዮጵያ አየር መንገድን መቀላቀላቸው የተጠቀሰ ሲሆን ከዚህ ውስጥ ሶስቱ ኤርባስ A350-1000 መሆናቸው ተሰምቷል፡፡ በዘጠኝ ወሩ ውስጥ አራት አዳዲስ የበረራ መዳረሻዎችንም የኢትዮጵያ አየር መንገድ መክፈቱን ጠቅሷል፡፡ አየር መንገዱ የፊታችን እሁድ ጁን 1, 2025 ከአዲስ አበባ ወደ ተባበሩት አረብ ኢምሬት ሻርጃህ ከተማ…
Read More
የአፍሪካ ኢንሹራንስ ጉባኤ በአዲስ አበባ መካሄድ ጀመረ

የአፍሪካ ኢንሹራንስ ጉባኤ በአዲስ አበባ መካሄድ ጀመረ

57 በመቶ የሚሆኑት የአፍሪካ ሀገራት ለከፍተኛ የእዳ ችግር መጋለጣቸው ተገልጿል። እነዚሁ ታዳጊ ሀገራት በተያዘው ዓመት ብቻ ከ 80 ቢሊዮን ዶላር በላይ የዉጪ እዳ እንዲከፍሉ ይጠበቃል በአፍሪካ የሕዝብ ዕዳ ሁኔታ እጅግ አሳሳቢ ደረጃ ላይ መድረሱን የአፍሪካ ኢንሹራንስ ድርጅት አስታውቋል ። እንደ ድርጅቱ መረጃ ከሆነ በአህጉሪቱ ከሚገኙ ዝቅተኛ ገቢ ካላቸው ሀገራት መካከል 57% የሚሆኑት በዕዳ ችግር ውስጥ ገብተዋል ወይም ከፍተኛ የዕዳ ስጋት ላይ ይገኛሉ። ይህንን አኃዝ የገለጹት የድርጅቱ ፕሬዝዳንት ወ/ሮ ፓቲ ማርቲን በአዳስ አበባ እየተካሄደ በሚገኘዉ 51ኛዉ የአፍሪካ ኢንሹራንስ ድርጅት ዓመታዊ ኮንፍረንስ እና ጠቅላላ ጉባኤ መድረክ ላይ ሲሆን :- በዚህ ንግግራቸው የዕዳው ጫና መጨመር ዋና ዋና መንስኤዎች የዓለም አቀፍ የገበያ መዋዠቅ እና…
Read More