20
Aug
ብሔራዊ ባንክ ባሳለፍነው ሰኔ ወር ላይ የውጭ ባንኮች ወደ ኢትዮጵያ ገብተው እንዲሰሩ የሚፈቅድ ህግ ይፋ ማድረጉ ይታወሳል፡፡ ይህንን ተከትሎም የኬንያው ኬሲቢ ግሩፕ በኢትዮጵያ ባንክ ኢንቨስትመንት ለመስራት በንግግር ላይ መሆኑን ቢዝነስ ዴይሊ ዘግቧል፡፡ ባንኩ በሚቀጥሉት 18 ወራት ውስጥ በኢትዮጵያ የሚገኝን አንድ ባንክ 40 ከመቶ ድርሻን ለመግዛት ንግግር በማድረግ ላይ እንደሆነ ተገልጿል። ይሁንና ኬሲቢ ከየትኛው የኢትዮጵያ ባንክ ጋር ንግግር እንደጀመረ በዘገባው ላይ አልተገለፀም። ያም ሆነ ይህ የኬንያ ባንክ ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ሰፊ የባንክ ስራዎችን በመስራት በኢትዮጵያ ተመራጭ ባንክ ለመሆን እቅድ ይዟል። ብሔራዊ ባንክ ሰኔ 18 ቀን 2017 ዓ.ም. ባወጣዉ መግለጫ መመሪያው የውጭ ተዋናዮች የባንክ ዘርፉን እንዲቀላቀሉባቸው በርካታ መንገዶችን ያቀርባል፤ ከእነዚህም መካከል ቅርንጫፍ…