ኢኮኖሚ

ንግድ ባንክ ለዲያስፖራዎች 50 ቢሊዮን ብር ብድር ለመስጠት ዝግጁ መሆኑን ገለጸ

ንግድ ባንክ ለዲያስፖራዎች 50 ቢሊዮን ብር ብድር ለመስጠት ዝግጁ መሆኑን ገለጸ

ንግድ ባንክ ለዲያስፖራው ማኀበረሰብ 50 ቢሊዮን ብር የብድር አገልግሎት አዘጋጅቼ እየጠበቀ መሆኑን አስታውቋል። የባንኩ የብድር አገልግሎቱ ለኢንቨስትመንት፣ ለመኖሪያ ቤትና አውቶሞቢል ግዥ የቀረበ ነው ተብሏል። የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፕሬዚደንት አቶ አቤ ሳኖ ሰሞኑን በተባበሩት አረብ ኤምሬቶች ከሚኖሩ ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያን  የዲያስፖራ ማህበረሰብ አባላት ጋር ተወያይተዋል፡፡ በውይይቱ ወቅት ፕሬዚደንቱ እንዳስታወቁት ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያን  የዲያስፖራ ማህበረሰብ አባላት በአገር ውስጥ ለሚያካሄዱት የቢዝነስ እንቅስቃሴ፣ ለመኖሪያ ቤትና መሰል ፍላጎቶች የ50 ቢሊዮን ብር የብድር አገልገሎት ተመቻችቷል ብለዋል፡፡ የብድር አገልግሎቱ በተያዘው የ2024/25 በጀት ዓመት ተፈጻሚ እንደሚሆንም ፕሬዝዳንቱ ተናግረዋል፡፡ ባንኩ አገልግሎቱን ለማግኘት ጥያቄ ለሚያቀርቡ የዲያስፖራ ማህበረሰብ አባላት ቀልጣፋና ምቹ አሰራር እንደሚተገብርም አቶ አቤ አስታውቀዋል፡፡ ሙሉ ለሙሉ የመንግስት…
Read More
የካፒታል ገበያ ባለስልጣን በጋራ ኢንቨስትመንት ፈንዶች ላይ አዲስ መመሪያ አወጣ

የካፒታል ገበያ ባለስልጣን በጋራ ኢንቨስትመንት ፈንዶች ላይ አዲስ መመሪያ አወጣ

በአሁኑ ወቅት በካፒታል ገበያ ሥር በተለያዩ ዘርፎች አገልግሎት ለመስጠት 10 ተቋማት የፈቃድ ማመልከቻ አስገብተው እየተጠባበቁ እንደሚገኝ የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለስልጣን አስታውቋል። በባለስልጣን መስሪያ ቤቱ የምዝገባና ፈቃድ አሰጣጥ ኃላፊ አቶ እንድሪስ ሰልማን፤ በኢትዮጵያ ያለው የካፒታል ገበያ ገና በማደግ ላይ የሚገኝ መሆኑን ገልጸዋል። ሆኖም ከጊዜ ወደጊዜ ፍላጎቱ እየጨመረ እንደሚመጣ ገልጸው፤ ያንን ፍላጎት ለመሙላት የሚያስችል ተጨማሪ አገልግሎት ሰጪዎች ገበያውን ሊቀላቀሉ የሚችሉበት ዕድል እንዳለ ተናግረዋል። በዚህም ወደ 10 ተቋማት እንዲሁም በግለሰብ ደረጃ ደግሞ አንድ ሰው የኢንቨስትመንትና የሰነደ መዋዕለ ነዋይ አማካሪነትን ጨምሮ በተለያዩ ዘርፎች የፈቃድ ማመልከቻ በማስገባት እየተጠባበቁ እንደሚገኙ አስታውቀዋል። ያመለከተው አካል በሙሉ ፈቃድ ይሰጠዋል ማለት እንዳልሆነ የገለጹት ኃላፊው፤ "በተቀመጠው የፈቃድ አሰጣጥ መመሪያ መስፈርት መሰረት…
Read More
ቢሊየነሩ አሊኮ ዳንጎቴ በኢትዮጵያ የአፈር ማዳበሪያ ፋብሪካ ለመገንባት ተስማማ

ቢሊየነሩ አሊኮ ዳንጎቴ በኢትዮጵያ የአፈር ማዳበሪያ ፋብሪካ ለመገንባት ተስማማ

የአፈር ማዳበሪያ ማምረቻ ኮምፕሌክስ የድርሻ ስምምነት መፈረሙን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ገልጸዋል፡፡ ፕሮጀክቱ በዓመት እስከ ሦስት ሚሊዮን ሜትሪክ ቶን ማዳበሪያ ማምረት የሚያስችል መሆኑንም ጠቅላይ ሚኒስትሩ ተናግረዋል፡፡ በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግ እና በዳንጎቴ ግሩፕ መካከል የማዳበሪያ ማምረቻ ኮምፕሌክስ የድርሻ ስምምነት መፈረሙን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ አስታውቀዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት፤ "ወደ ምግብ ዋስትና እና የግብርና ሽግግር በምናደርገው ጉዞ አንድ ሌላ እጥፋት ላይ በመድረሳችን ኢትዮጵያውያን ሁሉ እንኳን ደስ አለን!" ብለዋል። 2 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ኢንቨስትመንት የሚፈስበት ይህ ሜጋ ፕሮጀክት በዓመት እስከ ሦስት ሚሊዮን ሜትሪክ ቶን ማዳበሪያ የሚያመርት ሲሆን፤ "ይህም ኢትዮጵያን ከዓለም ግንባር ቀደም አምራቾች አንዷ ያደርጋታል" ብለዋል። "ፕሮጀክቱ በሀገር…
Read More
ልማት ባንክ ከ24 ቢሊዮን ብር በላይ ብድር መሰብሰቡን አስታወቀ

ልማት ባንክ ከ24 ቢሊዮን ብር በላይ ብድር መሰብሰቡን አስታወቀ

የኢትዮጵያ ልማት ባንክ በ2017 በጀት ዓመት የሥራ አፈጻጸም ግምገማ ወቅት፣ ከ24 ቢሊዮን ብር በላይ የብድር ክምችት ማሰባሰቡን ይፋ አድርጓል። ይህ ባንኩ ለተለያዩ ፕሮጀክቶች አበድሮ የነበረውን ገንዘብ ከባለዕዳዎች መልሶ የሰበሰበው መጠን አፈጻጸም ከታለመለት ግብ በ5 በመቶ ብልጫ ያለው ሲሆን፣ ከባለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር ደግሞ የ51.6 በመቶ ዕድገት ማሳየቱ ተገልጿል። የባንኩ ዋና ትኩረት ለኢንዱስትሪ፣ ለግብርና እና ለሌሎች ቁልፍ የኢኮኖሚ ዘርፎች የፋይናንስ ድጋፍ ማድረግ እንደሆነ ይታወቃል። የኢትዮጵያ ልማት ባንክ በዚሁ በጀት ዓመት 18.0 ቢሊዮን ብር ገቢ በማሰባሰብ ከባለፈው ዓመት ጋር ሲነጻጸር የ30.7 በመቶ ጭማሪ ማሳየቱን ተጠቅሷል፡፡ የኢትዮጵያ ልማት ባንክ በግብርና፣ ማዕድን ማውጣት፣ ማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ ለሚሰማሩ ኢንቨስትመንቶች የገንዘብ አቅርቦት የሚያመቻች መንግስታዊ ተቋም…
Read More
በኢትዮጵያ ከተመዘገቡ 6 ሺህ ቤት አልሚዎች ውስጥ ስራ ላይ ያሉት ከ400 አይበልጥም ተባለ

በኢትዮጵያ ከተመዘገቡ 6 ሺህ ቤት አልሚዎች ውስጥ ስራ ላይ ያሉት ከ400 አይበልጥም ተባለ

ከፌዴራልና ከክልል በአጠቃላይ በሀገር አቀፍ ደረጃ በሪል እስቴት ልማት ዘርፍ ለመሳተፍ ፈቃድ የወሰዱና የተመዘገቡ 6 ሺሕ የሚሆኑ አልሚዎች ያሉ ቢሆኑም፤ በሥራ ላይ የሚገኙት ግን ከ400 እንደማይበልጡ የኢትዮጵያ ሪል እስቴት አልሚዎች ማህበር አስታውቋል። የሪል እስቴት ዘርፉ ከአልሚዎች፣ ከገዢዎችና ከፋይናንስ ተቋማት ጨምሮ፤ በርካታ ችግሮች እና ተነሳሽነት ያልነበረበት እንደነበር የገለጹት፤ የማህበሩ ም/ፕሬዝዳንት ኢንጂነር ጀበል ጀማል ናቸው። ያለውን ችግር ለማስተካከልና በዘርፉ መተጋገዝ ካለና በጋራ መስራት ከተቻለ፤ የተሻለ ለውጥ ሊመጣ እንደሚችል በማመን የሪል እስቴት አልሚዎች ማሕበር መመስረት መቻሉንም አንስተዋል። ማሕበሩ ከመንግሥትና ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን በ29 አባላት መመስረት እንደቻለ አስታውሰው፤ አሁን ላይ ከ100 በላይ አባልትን በውስጡ መያዙን ገልጸዋል። አሁን ላይ እንደሀገር ከተመዘገቡት 6 ሺሕ…
Read More
የኬንያው ኪሲቢ ባንክ የኢትዮጵያን ባንክ 40 በመቶ ድርሻ ለመግዛት ንግግር ጀመረ

የኬንያው ኪሲቢ ባንክ የኢትዮጵያን ባንክ 40 በመቶ ድርሻ ለመግዛት ንግግር ጀመረ

ብሔራዊ ባንክ ባሳለፍነው ሰኔ ወር ላይ የውጭ ባንኮች ወደ ኢትዮጵያ ገብተው እንዲሰሩ የሚፈቅድ ህግ ይፋ ማድረጉ ይታወሳል፡፡ ይህንን ተከትሎም የኬንያው  ኬሲቢ ግሩፕ በኢትዮጵያ ባንክ ኢንቨስትመንት ለመስራት በንግግር ላይ መሆኑን ቢዝነስ ዴይሊ ዘግቧል፡፡ ባንኩ በሚቀጥሉት 18 ወራት ውስጥ በኢትዮጵያ የሚገኝን አንድ ባንክ 40 ከመቶ ድርሻን ለመግዛት ንግግር በማድረግ ላይ እንደሆነ ተገልጿል። ይሁንና ኬሲቢ ከየትኛው የኢትዮጵያ ባንክ ጋር ንግግር እንደጀመረ በዘገባው ላይ አልተገለፀም። ያም ሆነ ይህ የኬንያ ባንክ ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ሰፊ የባንክ ስራዎችን በመስራት በኢትዮጵያ ተመራጭ ባንክ ለመሆን እቅድ ይዟል። ብሔራዊ ባንክ ሰኔ 18 ቀን 2017 ዓ.ም. ባወጣዉ መግለጫ መመሪያው የውጭ ተዋናዮች የባንክ ዘርፉን እንዲቀላቀሉባቸው በርካታ መንገዶችን ያቀርባል፤ ከእነዚህም መካከል ቅርንጫፍ…
Read More
የጉምሩክ ቀረጥ ገቢ ባለፉት 7 ዓመታት በግማሽ መቀነሱ ተነገረ

የጉምሩክ ቀረጥ ገቢ ባለፉት 7 ዓመታት በግማሽ መቀነሱ ተነገረ

ባለፉት ሰባት ዓመታት ውስጥ የጉምሩክ ቀረጥና ተጨማሪ ቀረጥ ከጠቅላላ የሀገር ውስጥ ምርት አንጻር በግማሽ መቀነሱ ተገለጸ። ይህ ቅናሽ በዋናነት ከውጭ የሚገቡ የሸቀጦች መጠን እና ዋጋ በመቀነሱ ምክንያት እንደሆነ ተጠቁሟል። እኤአ 2015/16 ጀምሮ የነበረው የጉምሩክ ቀረጥና ተጨማሪ ቀረጥ ከጠቅላላ የሀገር ውስጥ ምርት 2.1% የነበረ ሲሆን፣ ይህ አሃዝ በ2022/23 ወደ 1.0% ዝቅ ብሏል። የዚህ መቀነስ ዋነኛ ምክንያት፣ ከውጭ የሚገቡ የሸቀጦች መጠን ከጠቅላላ የሀገር ውስጥ ምርት ከ24% ወደ 10% በመውረዱ እንደሆነ የገንዘብ ሚኒስቴር የሰሞኑን ጥናት ያመለክታል። ይህ የገቢ ቅናሽ አጠቃላይ የግብር እና የሀገር ውስጥ ምርት ጥምርታ መውረድ ውስጥ አንድ አራተኛውን ይዟል። ከ2015/16 እስከ 2021/22 ባለው ጊዜ ውስጥ፣ የውጭ ምርቶች መጠን መቀነስ በዋነኝነት በካፒታል…
Read More
ቻይና ሰራሹ ሲኖ ትራክ ተሽከርካሪ ወደ ኢትዮጵያ እንዳይገባ ተከለከለ

ቻይና ሰራሹ ሲኖ ትራክ ተሽከርካሪ ወደ ኢትዮጵያ እንዳይገባ ተከለከለ

የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር ከሲኖትራክ ምርት ተሽከርካሪዎች ጋር ተያይዞ በታየው የጥራትና ቴክኒክ ጉድለት ምክንያት፣ እነዚህ ተሽከርካሪዎች ወደ ኢትዮጵያ እንዳይገቡ እገዳ መጣሉን አሳውቋል። ይህ ውሳኔ በሰዎች ህይወት ላይ በተደጋጋሚ አደጋ እየደረሰ በመሆኑ እንደተወሰነ ኢትዮ ነጋሪ ለጉምሩክ ኮሚሽን በተጻፈ ከሰርኩላር ደብዳቤ ላይ ተመልክቷል። ሚኒስቴሩ በጉምሩክ ኮሚሽን በኩል ለጉምሩክ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤቶች በሙሉ ባስተላለፈው መረጃ መሰረት፣ የሲኖትራክ ካምፓኒው የጥራት ጉድለቶቹን እስኪያስተካክል ድረስ ከግንቦት 27 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ ምንም ዓይነት የሲኖትራክ ተሽከርካሪ ማስገቢያ ፍቃድ እንደማይሰጥ አስታውቋል። ከዚህም ባሻገር፣ ሚኒስቴሩ ፊርማና ማህተም በማስመሰል የሲኖትራክ ማስገቢያ ፍቃድ በማዘጋጀት ተሽከርካሪዎችን ወደ አገር ውስጥ ለማስገባት የሚሞክሩ ሰዎች መኖራቸውን መረጃ እንዳገኘ ገልጿል። ይህን ተከትሎ፣ ከግንቦት 27 ቀን 2017…
Read More
የኢትዮጵያ ሙቀት በየዓመቱ ከአንድ ድግሪ ሴልሺየስ በላይ እየጨመረ መሆኑ ተገለጸ

የኢትዮጵያ ሙቀት በየዓመቱ ከአንድ ድግሪ ሴልሺየስ በላይ እየጨመረ መሆኑ ተገለጸ

በአየር ንብረት ለውጥ ምክንያት በኢትዮጵያ የሙቀት መጠን በየዓመቱ በአማካይ ከ1 ዲግሪ ሴልሺየስ በላይ እየጨመረ ነው ተብሏል ኢትዮጵያ ለአለም ሀገራት የሙቀት መጨመር ያላት የበካይ ጋዝ ልቀት ድርሻ ግን 0.04 በመቶ ነው ተብሏል፡፡ ያደጉት ሀገራት ለአፍሪካ በየጉባኤው ቃል የሚገቡትን የአየር ንብረት ለውጥ መደገፊያ የፋይናንስ ድጋፍ እየሰጡ ስላልሆነ የአየር ንብረት ለውጥ መከላከል የሚሰራው ስራ የሚፈለገውን ያህል መሆን አልቻለም ተብሏል፡፡ ይህ የተነገረው በአየር ንብረት ለውጥ ላይ የሚመክረውና ኢትዮጵያ ከጳጉሜ 3 እስከ 5 ከምታሰናዳው ሁለተኛው የአፍሪካ የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ አስቀድሞ በተሰናዳ ዝግጅት ላይ ነው፡፡ የውሃ እና ኢነርጂ ሚኒስቴር ዛሬ ያሰናዳውና ነገም የሚቀጥለው ጉባኤና ኢግዚብሽን ከዋናው ጉባኤ በፊት የሚደረግ ቅድመ ጉባኤ ስለመሆኑ ተናግሯል፡፡ በዝግጅቱ መክፈቻ…
Read More
የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ ከኖርዌው የማዕድን ኩባንያ የ3 ሚ. ዶላር ድርሻ ገዛ

የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ ከኖርዌው የማዕድን ኩባንያ የ3 ሚ. ዶላር ድርሻ ገዛ

የኢትዮጵያ ሉዓላዊ ሀብት ፈንድ በአኮቦ የማዕድን ድርጅት የመጀመሪያውን ዓለም አቀፍ ኢንቨስትመንት ፈፀመ፡፡ የፈንዱ አካል የሆነው የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ፣ በኢትዮጵያ የወርቅ ማውጣት ሥራ ላይ ከተሠማራው የኖርዌው አኮቦ የማዕድን ኩባንያ  ሦስት ሚሊየን ዶላር ዋጋ ያለው 7.4 በመቶ ድርሻ መግዛቱን አስታውቋል። የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ብሩክ ታዬ፤ “በአኮቦ ማዕድን የምናደርገው ኢንቨስትመንት ለኢትዮጵያ የኢኮኖሚ መስፋፋት ታሪካዊና ስትራቴጂካዊ እመርታ ነው” ብለዋል፡፡ ውሳኔው ኢትዮጵያ ከክፍለ ዘመን በኋላ ወደ ዓለም አቀፍ የአክስዮን ገበያ እንድትመለስ ያደረገና ለቀጣይ የድንበር ተሻጋሪ ኢንቨስትመንቶች በር የከፈተ ነው ሲል የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ ዛሬ ባወጣው መግለጫ አስታውቋል፡፡ ኢንቨስትመንቱ አኮቦ አዲስ ማዕድን ማውጫ ለመገንባት የሚያስፈልገውን ወጪ የሚደግፍ ሲሆን፤ ይህም የድርጅቱን ወርሃዊ የወርቅ…
Read More