መነሻ ገፅ

በሻሸመኔ ከተማ ቆሻሻ ውስጥ የተጣለ ቦምብ ፈንድቶ የ4 ልጆች ህይወት አለፈ

በሻሸመኔ ከተማ ቆሻሻ ውስጥ የተጣለ ቦምብ ፈንድቶ የ4 ልጆች ህይወት አለፈ

በአማራ ክልል ከደብረማርቆስ ወደ ደንበጫ የሚወስደው መንገድ በተቃውሞ ምክንያት መዘጋቱም ተገልጿል፡፡ በኦሮሚያ ክልል ሻሸመኔ ከተማ ቆሻሻ ውስጥ ተጥሎ የነበረ ቦምብ ፈንድቶ በህጻናት ላይ ጉዳት አድርሷል፡፡ እንደ ከተማዋ ፖሊስ መግለጫ ከሆነ ቦምቡ ፈንድቶ ያገለገሉ ፕላስቲኮችን እየለቀሙ የነበሩ አራት ልጆች ህይወት አልፏል፡፡ ልጆቹ ያገለገሉ ፕላስቲኮችን እየለቀሙ ባለበት ሰዓት ከተጠራቀመ ቆሻሻ ውስጥ ቦምቡ መፈንዳቱን ፖሊስ ገልጿል፡፡ በቆሻሻ ውስጥ ተጥሎ የነበረው ቦምብ ባደረሰው ጉዳትም አራት ልጆችን ከመግደሉ በተጨማሪ ሁለት ተጨማሪ ህፃናትም ቆስለው ወደ ሆስፒታል ተወስደዋል፡፡ ህይወታቸው ካለፈ ልጆች ውስጥ ሶስቱ የአንድ ቤተሰብ አባላት መሆናቸውን ፖሊስ አስታውቋል፡፡ በተያያዘ ዜና በአማራ ክልል ከደብረማርቆስ ወደ ደንበጫ የሚወስደው መንገድ በተቃውሞ ምክንያት መዘጋቱ ተገልጿል፡፡ በአማራ ክልል ምስራቅ ጎጃም ዞን…
Read More
ኢትዮጵያ 59 ህገወጥ የሰዎች አዘዋዋሪዎችን በእስራት ቀጣች

ኢትዮጵያ 59 ህገወጥ የሰዎች አዘዋዋሪዎችን በእስራት ቀጣች

ኢትዮጵያ 59 ህገወጥ የሰዎች አዘዋዋሪዎችን በእስራት ቀጣች በኦሮሚያ ክልል በህገወጥ የሰዎች  ዝውውር እና ድንበር በማሻገር የተከሰሱ 161 ደላሎች መካከል 59 ያህሉ ላይ የቅጣት ውሳኔ መተላለፉ ተገልጿል፡፡ የኦሮሚያ ጠቅላይ ዓቃቢ ህግ ቢሮ የህገወጥ የሰዎች ዝውውር እና ድንበር ማሻገር ወንጀሎች ቁጥጥር  ቡድን መሪ አቶ መሀመድ ዝያድ  እንዳሉት ህገወጥ የሰዎች አዘዋዋሪዎች በእስራት ተቀጥተዋል፡፡ የህገወጥ የሰዎች ዝውውር እና ድንበር የማሻገር ወንጀል ሲፈጽሙ የነበሩት ግለሰቦች ኬንያ፣ ሶማሊያ፣ ታንዛኒያ እና ሊቢያ ጠረፎች ካሉ ደላሎች ጋር በቅንጅት ሲሰሩ እንደነበር ተገልጿል፡፡ በህገወጥ የሰዎች አዘዋዋሪዎች ሰለባ የሆኑ 134 ግለሰቦች በህገወጥ መንገድ ከሀገር በመዉጣታቸዉ ለተለያዩ ጥቃቶች መዳረጋቸዉን ገልጸዋል። በነዚህ ህገ ወጥ የሰዎች አዘዋዋሪዎች ምክንያት ሰለባ ከሖኑት ከ134 ግለሰቦች መካከል  112ቱ  የሚሆኑት…
Read More
ኢትዮጵያ ቮልስዋገን የኤሌክትሪክ ተሸከርካሪ ወደ ሀገር ውስጥ እንዳይገባ አገደች

ኢትዮጵያ ቮልስዋገን የኤሌክትሪክ ተሸከርካሪ ወደ ሀገር ውስጥ እንዳይገባ አገደች

በቻይና የሚመረተው የቮልስ ዋገን የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ በጊዜያዊነት ወደ ኢትዮጵያ እንዳይገባ ማገዷን አስታውቃለች፡፡ በቻይና ሀገር የሚመረተው የቮልስ ዋገን የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ በጊዜያዊነት ወደ ሀገር ውስጥ እንዳይገባ መታገዱን የትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ሚኒስቴር ገልጿል፡፡ በቻይና ሀገር ተገጣጥሞ ወደ ኢትዮጵያ እየገባ የሚገኘው ቮልስ ዋገን የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ ሕጋዊ የሆነ ፈቃድ አለመኖሩን የጀርመኑ ኩባንያ በኤንባሲው በኩል በደብዳቤ ለሚኒስቴሩ ማሳወቁ ተገልጿል፡፡ በመሆኑም በቻይና ሀገር የሚመረተው የቮልስ ዋገን የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ ከኩባንያው ሕጋዊ ፈቃድ ያለው መሆኑ እስከሚረጋገጥ ድረስ በጊዜያዊነት ወደ ሀገር ውስጥ እንዳይገባ ታግዷል፡፡ ወደ ሀገር ውስጥ የሚገቡ ተሽከርካሪዎች ላይ ክትትል በማድረግና የሕጋዊነት ማረጋገጫ መረጃዎችን የማጥራት ስራም በከፍተኛ ጥንቃቄ እየተሠራ መሆኑን ሚኒስቴሩ ገልጿል፡፡ መንግስት የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች በስፋት እንዲመረቱ፣ እንዲገጣጠሙና ወደ ሀገር…
Read More
በኢትዮጵያ የጥሬ ገንዘብ እጥረት አጋጥማል መባሉን ብሔራዊ ባንክ አስተባበለ

በኢትዮጵያ የጥሬ ገንዘብ እጥረት አጋጥማል መባሉን ብሔራዊ ባንክ አስተባበለ

በኢትዮጵያ የጥሬ ገንዘብ እጥረት አጋጥማል መባሉን ብሔራዊ ባንክ አስተባብሏል። በኢትዮጵያ በተለይም የግል ባንኮች የጥሬ ገንዘብ እጥረት እንዳጋጠማቸው በተለያየ መልኩ ሲገለጹ ቆይቷል። የባንክ ደንበኞችም ለአገልግሎት ባመሩባቸው የግል ባንኮች የጥሬ ገንዘብ ሲጠይቁ እንዳልሰጧቸው በርካታ ሚዲያዎች ዘግበዋል። በስድስተኛው የምስራቅ አፍሪካ የፋይናንስ ጉባኤ እየተሰተፈ የሚገኘው ብሔራዊ ባንክ በዚህ ጥያቄ ዙሪያ ምላሽ ሰጥቷል። የብሔራዊ ባንክ ምክትል ገዢ አቶ ሰለሞን ደስታ እንዳሉት "በኢትዮጵያ በግል ባንኮች የጥሬ ገንዘብ እጥረት ገጥሟቸዋል እሚባለው መረጃ ሀሰት ነው" ብለዋል። የጥሬ ገንዘብ እጥረት ገጥሟቸዋል የተባሉት አምስት ባንኮች ናቸው መባሉን ሰምተናል ፣ "ነገር ግን በሶስት ባንኮች ላይ የተወሰነ የጥሬ ገንዘብ እጥረት ገጥሞ ነበር፣ ብሔራዊ ባንክ እና ሌሎች ተቋማት በወሰዷቸው ማስተካከያዎች አሁን ላይ ከአንድ…
Read More
አፍሪካ ከዶላር ይልቅ በራሷ ገንዘብ እንድትገበያይ የኬንያ ፕሬዝዳንት ጠየቁ

አፍሪካ ከዶላር ይልቅ በራሷ ገንዘብ እንድትገበያይ የኬንያ ፕሬዝዳንት ጠየቁ

ኬንያ የአፍሪካ ሀገራት የእርስ በርስ ግብይት ሲፈጽሙ እና አገልግሎት ሲለዋወጡ በራሳቸው ገንዘብ ክፍያ  መፈጸም እንዲጀምሩ ጠይቃለች። ለኢጋድ የመሪዎች ስብሰባ ጅቡቲ ያመሩት የኬንያ ፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ አፍሪካ በዶላር ላይ ያላት ጥገኝነት ይብቃ ሲሉ ጥሪ አቅርበዋል። “ከጂቡቲ እቃ ገዝተን በዶላር የምንከፍለው ለምንድን ነው? ለምን? ምንም ምክንያት የለም”  ያሉት ፕሬዝዳንት ሩቶ ጂቡቲም ሆነች ኬንያ የእርስ በርስ ግብይት ሲፈጽሙ የአሜሪካ ዶላር መጠቀም አያስፈልጋቸውም ብለዋል። “እኛ የአሜሪካን ዶላር እየተቃወምን አይደለም፤ በነጻነት ግብይት መፈጸም ስለፈለግን እንጂ” ሲሉም ስለ ዶላር አስፈላጊነት ተናግረዋል። እንደ ኢስት አፍሪካን ጋዜጣ ዘገባ ፕሬዝዳንቱ ሩቶ አክለውም “ዶላር የሚያስፈልገን ከአሜሪካ ጋር ለምናደርገው ግብይት ብቻ ነው” ሲሉ ገልጸዋል፡፡ በፈረንጆቹ 1993 የተቋቋመው የአፍሪ ኤክዚም ባንክ ግብይቱ…
Read More
የአክሱም ሀውልት ከሁለት ዓመት ጦርነት በኋላ ለጎብኚዎች ክፍት ተደረገ

የአክሱም ሀውልት ከሁለት ዓመት ጦርነት በኋላ ለጎብኚዎች ክፍት ተደረገ

የአክሱም ሀውልት ዳግም ለጎብኚዎች ክፍት መደረጉን በትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር የአክሱም ከተማ ባህልና ቱሪዝም ጽሕፈት ቤት አስታውቋል። የጽሕፈት ቤቱ ሀላፊ ገብረመድህን ፍፁም ብርሀን፤ በአክሱም ከተማና አካባቢው የሚገኙ የሚዳሰሱ እና የማይዳሰሱ ጥንታዊ ቅርሶች ለቱሪስቶች ክፍት መደረጋቸውን ተናግረዋል። ቅርሶቹ ዳግም ለጎብኚዎች ክፍት እንዲሆኑ ሕብረተሰቡ በጉልበቱ፣ በገንዘቡና በሙያው ያደረገው ተሳትፎ የላቀ እንደነበርም ገልጸዋል። የቱሪዝሙን ዘርፍ ወደነበረበት ለመመለስና ሕብረተሰቡ ለቱሪስቶች የሚሰጠውን አገልግሎት ለማሳደግ ለፎቶ ግራፍ ባለሙያዎች፣ አስተርጓሚዎች፣ ለባህላዊ ጌጣጌጦችና ቅርፃ ቅርፅ ባለሙያዎች እንዲሁም ለባለ ሆቴሎች ስልጠና መሰጠቱንም አስረድተዋል። በአክሱምና አካባቢው የሚገኙ ቅርሶችና ሙዚየም ለጎብኚዎች ተደራሽ ለማድረግ ከዛሬ ጀምሮ ክፍት መደረጋቸውን ገልጸዋል። በአክሱምና አካባቢው የሚገኙ የሚዳሰሱና የማይዳሰሱ ጥንታዊ ቅርሶች ለመጎብኘትና ለማየት በየዓመቱ ከ30 ሺሕ በላይ…
Read More
የትግራይ እና አማራ ክልል አመራሮች ከሁለት ዓመት ደም አፋሳሽ ጦርነት በኋላ ተገናኙ

የትግራይ እና አማራ ክልል አመራሮች ከሁለት ዓመት ደም አፋሳሽ ጦርነት በኋላ ተገናኙ

የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳድር ፕሬዝዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ ወደ ባህርዳር ያቀኑ ሲሆን ከአማራ ክልል ፕሬዝዳንት ይልቃል ከፋለ ጋር ተወያይተዋል፡፡ አቶ ጌታቸው ረዳ እና ልዑካቸው ከአማራ ክልል ፕሬዝዳንት ዶ/ር ይልቃል ከፋለ ጋር እንዲሁም ከህብረተሰቡ ከተውጣጡ ተወካዮች ጋር ውይይት አድርገዋል። በዚህ ውይይት ላይ አቶ ጌታቸው ረዳ " ዋጋ የማይጠይቅ የሠላም አማራጭ ሳለ በፖለቲከኞች የጠብ ርሃብ ምክንያት በርካታ ጉዳቶች ተከስተዋል " ብለዋል፡፡ "ልዩነቶች ቢኖሩ እንኳን ልዩነቶቹ ከአማራ እና ትግራይ ሕዝብ በታች ናቸው " ያሉ ሲሆን " አሁን የጦርነትን ምዕራፍ ዘግተን የሠላም አማራጮችን የምናይበት ጊዜ ነው " ሲሉም አክለዋል፡፡ "የሁከት እና ግርግር አጀንዳዎች የሚታያቸው ይኖራሉ፤ ነገር ግን ለሕዝብ ካሰብን እና ከሠራን ከሠላም ውጭ የተሻለ…
Read More
ማንችስተር ሲቲ የአውሮፓ ቻምፒዮንስ ሊግ ዋንጫን አነሳ

ማንችስተር ሲቲ የአውሮፓ ቻምፒዮንስ ሊግ ዋንጫን አነሳ

ማንችስተር ሲቲ የአውሮፓ ቻምፒዮንስ ሊግ ዋንጫን አነሳ የጣልያኑ ኢንተርሚላንን እና የእንግሊዙ ማንችስተር ሲቲን ያገናኘው የዘንድሮው የአውሮፓ ቻምፒዮንስ ሊግ ዋንጫ በሲቲ አሸናፊነት ተጠናቋል፡፡ ትናንት ምሽት በቱርክ ኢስታምቡል በተካሄደው የፍጻሜ ጨዋታ ሮድሪጎ በሁለተኛው አጋማሽ ባስቆጠራት ጎል ማንችስተር ሲቲ ዋንጫውን ማሸነፍ ችሏል፡፡ ማንችስተር ሲቲ በስፔናዊው አሰልጣኝ ፔፔ ጋረዲዮላ አሰልጣኝነት ታግዞ በታሪክ የመጀመሪያውን የቻምፒዮንስ ሊግ ዋንጫ ማንሳት ችሏል፡፡ ማንችሰተር ሲቲ በ2022/23 የውድድር ዓመት ከቻምፒዮንስ ሊግ ዋንጫ በተጨማሪ የእንግሊዝን ፕሪሚየር ሊግ እና ኤፍኤካፕ ዋንጫን በማንሳት የሶትዮሽ ዋንጫ መውሰድ ችሏል፡፡ አሰልጣኝ ፔፔ ጋርዲዮላ የቻምፒዮንስ ሊግ ዋንጫን ከባርሴሎና፣ ባየርንሙኒክ እና ማንችስተር ሲቲ ጋር አሸንፏል፡፡ ከቦርሲያ ዶርትሙንድ ማንችስተር ሲቲን ከአንድ ዓመት በፊት የተቀላቀለው ኖረዌያዊው አርሊንግ ሀላንድ በ12 ጎሎች…
Read More
ኢትዮጵያዊያን እና ኬንያዊያን አትሌቶች በፓሪስ ዳይመንድ ሊግ ደምቀው አምሽተዋል

ኢትዮጵያዊያን እና ኬንያዊያን አትሌቶች በፓሪስ ዳይመንድ ሊግ ደምቀው አምሽተዋል

የፓሪስ ዳይመንድ ሊግ ውድድር ትናንት ምሽት የተካሄደ ሲሆን ኢትዮጵያዊያን እና ኬንያዊያን አትሌቶች ድል ቀንያቸዋል። ኢትዮጵያዊው ለሜቻ  ግርማ ለ19 አመት ተይዞ የነበረውን የ3 ሺህ መሰናክል ክብረወሰን በመስበር አሸንፏል። ከውድድሩ አስቀድሞ ሪከርዱን እንደሚሰብር ሲናገር የነበረው ለሜቻ በአንድ ወር ውስጥ ሁለተኛ ክብረወሰኑ ሁኖ ተመዝግቧል ። አትሌቱ 7:51:11 በመግባት ሲያሸንፍ ሌላኛው ኢትዮጵያዊ አብርሃም ስሜ8:10:73 የግሉን ምርጥ  ሰዓት በማስመዝገብ 4ኛ ደረጃን ይዞ አጠናቋል ። ከቀናት በፊት የ1500 ሜትር የአለም ክብረ ወሰን የሰበረችው ኬኒያዊቷ ፌዝ ኪፕዮገን ለመጀመሪያ ጊዜ በተዋዳደረችበት የ5 ሺህ ሜትር ውድድር ለ8 ዓመት ተይዞ የቆየውን ክብረ ወሰን አሻሽላለች። የዚሁ ርቀት ክብረወሰን ባለቤት የሆነችው እና በውድድሩ ላይ የተሳተፈችው ለተሰንበት ግደይ ሁለተኛ ሆና አጠናቃለች። የ5 ኪሎ…
Read More
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ዘጠኝ የአውሮፓ ህብረት ፕሮጀክቶችን አሸነፈ

የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ዘጠኝ የአውሮፓ ህብረት ፕሮጀክቶችን አሸነፈ

የአውሮፓ ህብረት ከሚደግፋቸው አስራ ሰባት (17) የምርምር እና የትምህርት ልህቀት ማዕከላት ፕሮጀክቶች አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በዘጠኙ አሸናፊ ሆነ። ከዚህም በተጨማሪ ሁለት የፕሮጀክት ፕሮፖዛሎች ውጤት በመጪው ጥቂት ወራት የሚታወቅ ይሆናል ተብሏል። በደቡብ አፍሪካ ኬፕታውን በ2022 November የARUA እና Guild የዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንቶች በነበራቸው ስብሰባ በአውሮፓ ህብረት የሚደገፉ የምርምር እና የ ትምህርት ልህቀት ማእከላት ለማቋቋም ወስነው መለያየታቸው ይታወሳል። በዚሁ መሰረት በተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች በርካታ ፕሮፖዛሎች የቀረቡ ሲሆን ባለፉት ሁለት ተከታታይ ቀናት በቤልጂየም ብራስልስ በተካሄደው ግምገማ መሰረት 17 የልህቀት ማእከል ተመስርተዋል። ከነዚህ የልህቀት ማዕከል ፕሮጀክቶች ውስጥም በዘጠኙ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ አሸናፊ ሆኗል። በተጨማሪም ዩኒቨርሲቲው ፕሮጀክቶቹን በማሸነፉ በሚሊዮኖች የሚቆጠር ዩሮ የሚያገኝ ይሆናል፡፡ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚደንት…
Read More