Humantrafficking

ኤርትራዊያንን በኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት መኪና ሲያጓጉዙ የተገኙ ወታደሮች በእስራት ተቀጡ

ኤርትራዊያንን በኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት መኪና ሲያጓጉዙ የተገኙ ወታደሮች በእስራት ተቀጡ

በሰዎች ዝውውር የተከሰሱ የመከላከያ ሠራዊት አባላት በእሥራት ተቀጥተዋል። በህገ ወጥ የሠዎች ዝውውር ተሠማርተዋል የተባሉ አንድ ከፍተኛ የአገር መከላከያ ሠራዊት አዛዥን ጨምሮ ሁለት የሠራዊቱ አባላት በ8 ዓመት ከ5 ወር ፅኑ እስራት ተቀጥተዋል፡፡ አባላቱ ቅጣቱ የተላለፈባቸው ትናንት በአርባምንጭ ከተማ በተሰየመው የጋሞ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ባሳለፈው የፍርድ ውሳኔ ነው  ተብሏል፡፡ ቅጣቱ የተወሰነው በሠራዊቱ የደቡብ ዕዝ 202ኛ ኮር 1ኛ ሬጅመንት አዛዥ ሻምበል መብራቱ ታዴ እና በሬጅመንቱ የኦራል አሽከርካሪ በሆነው ወታደር ጌታቸው ክብረት በተባሉት  ላይ እንደሆነ ዶቸቪሌ ዘግቧል። አዛዡ እና የሰራዊቱ አባል ቅጣቱ የተወሰነባቸው ህዳር 16 2016 ዓ.ም 52 ኤርትራዊያንን በሠራዊቱ የኦራል ተሽከርካሪ በመጫን ወደ ኬኒያ በማሻገር ላይ እንዳሉ በመያዛቸው መሆኑን የጋሞ ዞን ከፍተኛ…
Read More
ኢትዮጵያ 59 ህገወጥ የሰዎች አዘዋዋሪዎችን በእስራት ቀጣች

ኢትዮጵያ 59 ህገወጥ የሰዎች አዘዋዋሪዎችን በእስራት ቀጣች

ኢትዮጵያ 59 ህገወጥ የሰዎች አዘዋዋሪዎችን በእስራት ቀጣች በኦሮሚያ ክልል በህገወጥ የሰዎች  ዝውውር እና ድንበር በማሻገር የተከሰሱ 161 ደላሎች መካከል 59 ያህሉ ላይ የቅጣት ውሳኔ መተላለፉ ተገልጿል፡፡ የኦሮሚያ ጠቅላይ ዓቃቢ ህግ ቢሮ የህገወጥ የሰዎች ዝውውር እና ድንበር ማሻገር ወንጀሎች ቁጥጥር  ቡድን መሪ አቶ መሀመድ ዝያድ  እንዳሉት ህገወጥ የሰዎች አዘዋዋሪዎች በእስራት ተቀጥተዋል፡፡ የህገወጥ የሰዎች ዝውውር እና ድንበር የማሻገር ወንጀል ሲፈጽሙ የነበሩት ግለሰቦች ኬንያ፣ ሶማሊያ፣ ታንዛኒያ እና ሊቢያ ጠረፎች ካሉ ደላሎች ጋር በቅንጅት ሲሰሩ እንደነበር ተገልጿል፡፡ በህገወጥ የሰዎች አዘዋዋሪዎች ሰለባ የሆኑ 134 ግለሰቦች በህገወጥ መንገድ ከሀገር በመዉጣታቸዉ ለተለያዩ ጥቃቶች መዳረጋቸዉን ገልጸዋል። በነዚህ ህገ ወጥ የሰዎች አዘዋዋሪዎች ምክንያት ሰለባ ከሖኑት ከ134 ግለሰቦች መካከል  112ቱ  የሚሆኑት…
Read More