Blog

ኢትዮጵያ 78 በመቶ የሬሚታንስ ገቢዋን እንደምታጣ ተገለጸ

ኢትዮጵያ 78 በመቶ የሬሚታንስ ገቢዋን እንደምታጣ ተገለጸ

ሀገሪቱ ከሬሚታንስ ገቢ 35 ቢሊዮን ዶላር ገቢ የማግኘት አቅም እንዳላት ተገልጿል ኢትዮጵያ ከውጭ ሀገራት በሕጋዊ መንገድ ከሚላክላት ገንዘብ (ሬሚታንስ) የምታገኘው ገቢ የሀገሪቱን አቅም 22 በመቶ ብቻ መሆኑ ተገልጿል። የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፕሬዝዳንት አቶ አቤ ሳኖ በተለያዩ ሀገራት ከሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን ዲያስፖራዎች ጋር በመወያየት ላይ ናቸው፡፡ ከዚህ በፊት በተባበሩት አረብ ኢምሬት እና ሳውዲ አረቢያ ከተሞች ከኢትዮጵያዊያን ዲያስፖራዎች ጋር የተወያዩት ፕሬዝዳንቱ አሁን ደግሞ በደቡብ አፍሪካ ፕሪቶሪያ ከተማ ከሚገኙ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ጋር ተወያይተዋል፡፡ ፕሬዝዳንቱ በዚህ ጊዜ እንዳሉት ኢትዮጵያ ከሬሚታንስ ገቢ እየተገኘች ያለው ገቢ 7.2 ቢሊየን ዶላር ብቻ ነዉ ብለዋል። አቶ አቤ ሳኖ እንዳስረዱት፣ አሁን ካለው የገንዘብ ፍሰት ቀሪው 78 በመቶ የሚሆነው ወደ ሀገር…
Read More
ኢትዮጵያ በዓመት 111 ሚሊዮን ሊትር የሚያመርት የጋዝ ማጣሪያ አስመረቀች

ኢትዮጵያ በዓመት 111 ሚሊዮን ሊትር የሚያመርት የጋዝ ማጣሪያ አስመረቀች

በዓመት 111 ሚሊየን ሊትር የሚያመርተው የኦጋዴን ፈሳሽ የተፈጥሮ ጋዝ ፕሮጀክት ተመርቋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሶማሌ ክልል ካሉብ በዓመት 111 ሚሊየን ሊትር ማምረት የሚችለውን የኦጋዴን ፈሳሽ የተፈጥሮ ጋዝ ፕሮጀክት የመጀመሪያ ዙር መርቀዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በምረቃ ስነ ስርዓቱ ላይ እንዳሉት በሶማሌ ክልል ካሉብ በዓመት 111 ሚሊየን ሊትር ማምረት የሚችለውን የኦጋዴን ፈሳሽ የተፈጥሮ ጋዝ ፕሮጀክት የመጀመሪያ ዙር መርቀናል ብለዋል። በተመሳሳይ በዓመት 1 ነጥብ 33 ቢሊየን ሊትር የማምረት አቅም የሚኖረውን ሁለተኛውን የነዳጅ ማጣሪያ ስራ ማስጀመራቸውንም ገልጸዋል፡፡ ማጣሪያው ከፈሳሽ ተፈጥሮ ጋዝ ምርት ባሻገር በኃይል ማመንጫ ዘርፉም 1 ሺህ ሜጋ ዋት የማመንጨት አቅም በመያዝ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው አስረድተዋል፡፡ ከሁሉም በላይ ፕሮጀክቱ የጋዝ ማምረቻ ብቻ…
Read More
በሶማሊ ክልል ጎዴ የአፈር ማዳበሪያ እና ነዳጅ ማጣሪያ ግንባታ ተጀመረ

በሶማሊ ክልል ጎዴ የአፈር ማዳበሪያ እና ነዳጅ ማጣሪያ ግንባታ ተጀመረ

ጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ የዩሪያ ማዳበሪያ እና ጌዴ ነዳጅ ማጣሪያ ግንባታን አስጀምረዋል። የዩሪያ አፈር ማዳበሪያ ፋብሪካ በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግ እና ዳንጎቴ ግሩፕ ጋር በመተባበር ይገነባል ተብሏል። ጎልደን ኮንኮርድ ግሩፕ ደግሞ የጎዴ ነዳጅ ማጣሪያ ፋብሪካን እንደሚገነባ ጠቅላይ ሚንስትሩ ገልጸዋል። የጎዴ ነዳጅ ማጣሪያ ከሂላል የነዳጅ ስፍራ ድፍድፍ ነዳጅ በማውጣት፣ በማጣራትና በማጠራቀም በአመት 3.5 ሚሊዮን ቶን የማምረት አቅም አለውም ተብሏል። በሌላ በኩልም የማዳበሪያ ፋብሪካው ከካሉብ የጋዝ ስፍራ በማውጣት እና 108 ኪሎሜትር የማጓጓዣ ቱቦ በመጠቀም በአመት 3 ሚሊዮን ቶን አምርቶ ያቀርባል። ከአንድ ወር በፊት አሊኮ ዳንጎቴ ግሩፕ ከኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግ ጋር የአፈር ማዳበሪያ ማምረቻ ኮምፕሌክስ ስምምነት መፈራረማቸው ይታወሳል፡፡ ፕሮጀክቱ በዓመት እስከ ሦስት ሚሊዮን ሜትሪክ…
Read More
አቢሲንያ ባንክ ሰባት ቢሊዮን ብር ማትረፉን ገለጸ

አቢሲንያ ባንክ ሰባት ቢሊዮን ብር ማትረፉን ገለጸ

አቢሲንያ ባንክ አጠቃላይ ሀብቱ ከ286 ቢሊዮን ብር በላይ መድረሱን አስታውቋል። አቢሲንያ ባንክ በዛሬው ዕለት ዓመታዊ የባለአክስዮኖች 29ኛ መደበኛ እና 16ኛ አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤው አካሂዷል። በጉባኤው ላይ እ.ኤ.አ በ2024/25 የሒሳብ ዓመት ሪፖርት የቀረበ ሲሆን፤ የባንኩ አጠቃላይ ሀብት 286 ነጥብ 2 ቢሊዮን ብር መድረሱን አስታውቋል፡፡ ይህም ካለፈው ዓመት አጠቃላይ ሀብት ማለትም ከ222 ነጥብ 3 ቢሊዮን ብር ጋር ሲነጻጸር የ63 ነጥብ 9 ቢሊዮን ወይም የ28 ነጥብ 8 በመቶ ዕድገት ማሳየቱን የአቢሲኒያ ባንክ የዳይሬክተሮች ቦርድ ሊቀመንበር አቶ መኮንን ማንያዘዋል ገልጸዋል። ባለፈው የሒሳብ ዓመት የባንኩ ጠቅላላ ገቢው 39 ነጥብ 1 ቢሊዮን ብር መድረሱን የገለጹ ሲሆን፤ ውጤቱ ካለፈው ተመሳሳይ ዓመት ጋር ሲነጻጸር የ11 ነጥብ 3 ቢሊዮን…
Read More
ኢትዮጵያ በ1 ቢሊዮን ዩሮቦንድ ዕዳ ዙሪያ አዲስ ውይይት ጀመረች

ኢትዮጵያ በ1 ቢሊዮን ዩሮቦንድ ዕዳ ዙሪያ አዲስ ውይይት ጀመረች

ኢትዮጵያ የ1 ቢሊዮን ዶላር ዩሮቦንድ ዕዳዋን እንደገና ለማዋቀር ከግል ባለቤቶች ጋር ሚስጥራዊ ውይይት ጀምራለች። የኢትዮጵያ መንግስት የ1 ቢሊዮን ዶላር የዩሮቦንድ ዕዳን እንደገና ለማዋቀር (restructure) ከዓለም አቀፍ የቦንድ ባለቤቶች ኮሚቴ ጋር ይፋዊ እና ሚስጥራዊነትን ያካተተ ውይይት መጀመሩን ብሉምበርግ ዘግቧል። ይህ እርምጃ ሀገሪቱ በከባድ የዕዳ ጫናዋን ለማቃለል በምታደርገው ጥረት ውስጥ እንደ ወሳኝ ምዕራፍ ተወስዷል። ውይይቱ "restricted" ተብሎ የተገለጸ ሲሆን፣ ይህ ማለት በድርድሩ ላይ የሚሳተፉት አበዳሪዎች (የቦንዱ ባለቤቶች) "የምስጢራዊነት ስምምነት" (NDA) መፈረም ነበረባቸው። ይህ ስምምነት የኢትዮጵያ መንግስት ለስምምነቱ መሳካት ወሳኝ የሆኑ ሚስጥራዊ የኢኮኖሚ መረጃዎችን ለአበዳሪዎቹ እንዲያካፍል ያስችለዋል። ስምምነቱን የፈረሙ ባለቤቶች በውይይቱ ወቅት የኢትዮጵያን ቦንድ መሸጥም ሆነ መግዛት አይችሉም። ይህ የውይይት እርምጃ የመጣው ኢትዮጵያ…
Read More
ኢትዮጵያ ከ18 ሀገራት ጋር የንግድ ድርድር ጀመረች

ኢትዮጵያ ከ18 ሀገራት ጋር የንግድ ድርድር ጀመረች

ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት (WTO) አባልነት ድርድር ሂደት 6ኛው የሥራ ቡድን ስብሰባ ላይ፤ በሁለትዮሽ ንግድ ድርድር ዙሪያ 18 ሀገራት ጋር ድርድር ማድረግ መጀመሯን ንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡ የዓለም ንግድ ድርጅት 6ኛ የሥራ ቡድን ስብሰባ ባለፈው ሳምንት በስዊዘርላንድ ጄኔቫ መካሄዱ ይታወሳል። ይህ ስብሰባ ኢትዮጵያ የድርጅቱን አባልነት ጥያቄ ባቀረበች ከ20 ዓመታት በላይ ሂደት ውስጥ ወሳኝ ምዕራፍ የተመዘገበበት እንደነበር ሚኒስቴሩ ገልጿል። የድርድሩ ቡድን መሪ፣ ዋና ተደራዳሪ እና የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) የድርድር ሂደቱን አስመልክቶ፤ ለጋዜጠኞች መግለጫ ሰጥተዋል። በመግለጫቸውም ኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባል እንድትሆን እና ከተለያዩ ሀገራት ጋር ያለው የንግድ ትስስር እንድታጎለብት ለማድረግ ብርቱ ሥራ ሲሰራ መቆየቱን አስታውሰዋል፡፡ ከዚህ…
Read More
የባንኮች ብድር ዕድገት ጣሪያ ወደ 24 በመቶ አደገ

የባንኮች ብድር ዕድገት ጣሪያ ወደ 24 በመቶ አደገ

ብሔራዊ ባንክ አሁን ያለውን የዋጋ ግሽበት የመርገብ አዝማሚያ ለማስቀጠል እና የፋይናንስ ዘርፉን ጤናማነት ለመጠበቅ በመስከረም ወር ላይ ሊነሣ ይችላል ተብሎ የተገመተዉ የባንኮች ዓመታዊ የብድር ዕድገት ጣሪያን ሙሉ ለሙሉ ከማንሳት ይልቅ ገደቡ ለጊዜው ከ18 በመቶ ወደ 24 በመቶ ከፍ እንዲል ወስኗል፡፡ የባንኮች የብድር ዕድገት ገደብ መነሣት የብሔራዊ ባንክን የገንዘብ ፖሊሲ አቋም ለማመልከትና የገንዘብ ፖሊሲ መዋቅሩን የተሻለ ለማድረግ እንደሚረዳ ይታመናል ሲል ኮሚቴው አስረድቷል፡፡ ኮሚቴው  በጉዳዩ ላይ በወደፊት ስብሰባዎቹ ገምግሞ የውሳኔ ሐሳብ አንደሚያቀርብም ጠቅሷል፡፡ የብሔራዊ ባንክ የፖሊሲ ተመን አሁን ባለበት 15 በመቶ እንዲቆይም ወስኗል፡፡ ብሔራዊ ባንክ ለሚሰጣቸው የተቀማጭ ሂሳብ አገልግሎት እና የብድር አገልግሎት የሚከፈሉ የወለድ ተመኖች ባሉበት እንዲቀጥሉ፤ እንዲሁም ባንኮች በብሔራዊ ባንክ የሚያስቀምጡት…
Read More
ኢትዮጵያ እና ኬንያ ወታደራዊ ስምምነት ተፈራረሙ

ኢትዮጵያ እና ኬንያ ወታደራዊ ስምምነት ተፈራረሙ

ኢትዮጵያ እና ኬንያ ከ62 ዓመታት በኋላ ለሁለተኛ ጊዜ ታሪካዊ የሚባል ወታደራዊ ስምምነት ተፈራርመዋል። ስምምነቱ ከሁለቱ ሀገራት ባለፈ ለቀጠናው ሰላምና መረጋጋትም የጎላ ፋይዳ ያለው መሆኑም ተገልጿል። ስምምነቱን የኢትዮጵያ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ እና የኬንያ መከላከያ ኢታማዦር ሹም ጄነራል ቻርልስ ሙሪዩ ካሃሪሪ ፈርመዋል። ስምምነቱ ከሃገራቱ በተጨማሪ ለቀጠናው ሰላምና ደህንነት የጎላ አስተዋጽኦ ያለው መሆኑን ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ እና የኬንያ መከላከያ ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ጄኔራል ቻርልስ ሙሪዩ ካሃሪሪ ተናግረዋል። በቀጣይም ከኢትዮጵያ መከላከያ ጋር በትብብር በሚሰሩ ስራዎች ዙሪያ የኬንያ መከላከያ በቁርጠኝነት ለመስራት ፍላጎት ያለው መሆኑን ኢታማዦር ሹም ጄኔራል ቻርልስ ሙሪዩ ካሃሪሪ መናገራቸውንም ከኢኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት የተገኘው መረጃ ያመላክታል። ኢትዮጵያና…
Read More
ኢትዮጵያ የ6 መርከቦች ግዥ መፈፅሟ ተገለ

ኢትዮጵያ የ6 መርከቦች ግዥ መፈፅሟ ተገለ

የመርከቦቹ መገዛት በባህር ትራንስፖርት ላይ ያላትን አቅም የበለጠ ያሳድጋል ተብሎ ታምኖበታል፡፡ የባህር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ የሚያስተዳድራቸው 10 መርከቦች ባለቤት የሆነችው ኢትዮጵያ የማዳበሪያ ምርትን ጨምሮ የሚበዛውን ምርት የምታጓጉዘው እነዚህኑ መርከቦች ተጠቅማ ነው። አሁን ደግሞ የተጨማሪ ስድስት ትላልቅ መርከቦች ግዢ ተፈፅሞ ኢትዮጵያ መርከቦቹን ዘንድሮ እንደምትረከብ ተነግሯል። ይህም ኢትዮጵያ በውሃ ትራንስፖርት ላይ ያላትን አቅም የሚያሳድግ ነው ተብሏል። ከስድስቱ መርከቦች ሁለቱ እስከ 62,000 ቶን የመጫን አቅም ያላቸው እንደሆኑም ተነግሯል። ኢትዮጵያ አሁን ካሏት አስር መርከቦች አባይ ሁለት በመባል የምትጠራው እስከ 63,000 ቶን የመጫን አቅም እንዳላት ይነገራል። ባለፈው ዓመት ኢትዮጵያ ወደ ሀገር ውስጥ ካስገባችው 1.9 ሚሊየን ሜትሪክ ቶን የማዳበሪያ ምርት አብዛኛው ተጓጉዞ ጅቡቲ ወደብ የደረሰው በራሷ መርከቦች…
Read More
የመንግሥት አጠቃላይ የአገር ውስጥ የብድር እዳ ክምችት 2.5 ትሪሊዮን ብር ደረሰ

የመንግሥት አጠቃላይ የአገር ውስጥ የብድር እዳ ክምችት 2.5 ትሪሊዮን ብር ደረሰ

የመንግሥት አጠቃላይ የአገር ውስጥ የብድር ክምችት 2.5 ትሪሊዮን ብር መድረሱን፣ ከዚህም ውስጥ የግምጃ ቤት ቦንድ ግዥ ከፍተኛ ድርሻ ይይዛል ተብሏል፡፡ የገንዘብ ሚኒስቴር በዕዳ አስተዳደር ክፍል በኩል ያዘጋጀውን ወርኃዊ የዕዳ ማስታወቂያ የነሐሴ ወር 2017 ዓ.ም. ሪፖርት፣ የመንግሥት አገራዊ ብድር ዝርዝር መረጃ ይፋ አድርጓል፡፡ በዚህም መንግሥት እ.ኤ.አ. ከጁን 30 ቀን 2025 ጀምሮ አጠቃላይ የአገር ውስጥ ብድር 2.5 ትሪሊዮን ብር መድረሱን እንዳስታወቀ የሪፖርተር ዘገባ ያሳያል፡፡ ከአገር ውስጥ ብድር ድርሻ 80 በመቶ የሚይዘው በረዥም ጊዜ የሚከፈል የግምጃ ቤት ሰነድ እ.ኤ.አ. በኦገስት 2025 የግምጃ ቤት ሰነድ ግዥ ከፍተኛ እንደነበርና ከአጠቃላይ ክምችት አንፃርም 39 በመቶ እንደሚሸፍን ገልጿል፡፡ እስከ ኦገስት 2025 ድረስ ባለው የመንግሥት አጠቃላይ የአገር ውስጥ…
Read More