ethiopianews

በጦርነት በተጎዳችው ትግራይ የ6 ቢሊዮን ብር ብረት ማምረቻ ፋብሪካ ሊገነባ እንደሆነ ተገለጸ

በጦርነት በተጎዳችው ትግራይ የ6 ቢሊዮን ብር ብረት ማምረቻ ፋብሪካ ሊገነባ እንደሆነ ተገለጸ

በ6 ቢሊዮን ብር ወጪ በኢትዮጵያ እና ቻይና ባለሃብቶች ትብብር የብረታ-ብረት ማምረቻ ኢንዱስትሪ በመቐሌ ከተማ ሊገነባ ነው። በአስር ወራት ውስጥ የሚገነባው ይህ ኢንዱስትሪ የስራ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ዛሬ ይፋ ተደርጓል። በዚህ ወቅት የትግራይ ክልል ግዜያዊ አስተዳደር ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጌታቸው ረዳ፤ የሌጀንድ ብረታብረት ኢንዱስትሪ ሃላፈነቱ የተወሰነ የግል ማህበር ለበርካታ ወጣቶች የስራ ዕድል የሚፈጥር በመሆኑ አስፈጊው ድጋፍ ይደረግለታል ብለዋል። ሌሎች በግልና በማህበር የተደራጁ ባለሃብቶችም የዚህን የልማት ፕሮጀክት አርአያ ተከትለው በማልማት  ራሳቸውንና ሀገራቸውን እንዲጠቅሙ መልእክት አስተላልፈዋል። የብረታብረት ማምረቻው 75 በመቶ በኢትዮጵያዊው ባለሃብት ኢንጅነር ያሬድ ተስፋይ የተሸፈነ ሲሆን ቀሪው 25 በመቶ ደግሞ በቻይናዊው ባለሃብት ሚስተር ሊ ዮን መሸፈኑን የፕሮጀክቱ አስተባባሪ አቶ ሳምሶም ገብረመድህን ገልጸዋል።…
Read More
ኢትዮጵያ 28 የመስኖ ግድቦችን በመገንባት ላይ መሆኗን ገለጸች

ኢትዮጵያ 28 የመስኖ ግድቦችን በመገንባት ላይ መሆኗን ገለጸች

የመስኖ እና ቆላማ አካባቢ ሚኒስቴር እንደገለጸው ኢትዮጵያ 28 የመስኖ ፕሮጀክቶችን በመገንባት ላይ መሆኑን አስታውቋል፡፡ በግንባታ ላይ ካሉት የመስኖ ግድቦች ውስጥም 13ቱን በተያዘው የ2016 ዓመት በከፊል ለማጠናቀቅ ጥረት እየተደረገ መሆኑንም ሚኒስቴሩ ገልጿል፡፡ በዚህ ዓመት እንዲጠናቀቁ በሚል እየተገነቡ ላሉ ግድቦችም 8 ነጥብ 03 ቢሊዮን ብር መመደቡ ተመልክቷል፡፡ የመስኖ እና ቆላማ አካባቢ ሚኒስቴር የሕዝብ ግንኙነት እና ኮሙኒኬሽን ሥራ አስፈጻሚ አቶ ብዙነህ ቶልቻ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጀት እንደገለጹት በአሁኑ ጊዜ በሀገሪቱ 28 የመስኖ ልማት ፕሮጀክቶች ግንባታቸው በመከናወን ላይ ነው፡፡ 13 የመስኖ ፕሮጀክቶች በከፊል ሲጠናቀቁ 2 ሺህ 450 ሄክታር መሬት ማልማት የሚያስችሉ እንደሆኑም ሃለፊው ተናግረዋል፡፡ እየተገነቡ ካሉት ግድቦች በተጨማሪም 27 አዲስ የመስኖ ግድቦችን ለመገንባት የጥናትና ዲዛይን…
Read More
የኢትዮጵያ ባለሥልጣናት ስለባህር በር አስተያየት ሲሰጡ እንዲጠነቀቁ ተጠየቀ

የኢትዮጵያ ባለሥልጣናት ስለባህር በር አስተያየት ሲሰጡ እንዲጠነቀቁ ተጠየቀ

ባለስልጣናት ስለ ባህር በር ጉዳይ የሚሰጡት መግለጫ የተጠናና ጥንቃቄ የተሞላበት መሆን እንዳለበት ምሁራን አሳስበዋል፡፡ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በኢትዮጵያ የባህር በር ዙሪያ የምሁራን ውይይት መድረክ አዘጋጅቶ ነበር፡፡ በዚህ የምሁራን መድረክ ላይ ጥናት ያቀረቡና ውይይት ያደረጉ ምሁራን፣ መንግሥት ስለባህር በር የሚሰጣቸው መረጃዎች የጎረቤት አገሮችን የማያሠጉና ጥንቃቄ የተሞላባቸው እንዲሆኑ አሳስበዋል፡፡ ‹‹ፍትሐዊ የወደብ አጠቃቀም ለአፍሪካ ቀንድ ዘላቂ ሰላምና ልማት›› በሚል ርዕስ በተስተናገደው በዚህ ዓውደ ጥናት ላይ፣ ኢትዮጵያ በሰላማዊ መንገድ የባህር በር ባለቤት መሆን ስለምትችልባቸው አማራጮች ሰፊ ምሁራዊ ውይይት ተካሂዷል፡፡ በጥናት መድረኩ ላይ ለኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄን በማስመለስ ታሪካዊ ድል ያስመዘገቡ ያለፈው ትውልድ ምርጥ ተሞክሮ ታሪካዊ ድል እንደነበር ተገልጿል፡፡ በሰላማዊ መንገድ ኤርትራን በፌዴሬሽን ከኢትዮጵያ ጋር…
Read More
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ እስራኤል አቋርጦት የነበረውን በረራ እንደሚጀምር ገለጸ፡፡

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ እስራኤል አቋርጦት የነበረውን በረራ እንደሚጀምር ገለጸ፡፡

ሃማስ በእስራኤል ላይ ድንገተኛ እና ያለተጠበቀ ጥቃት መሰንዘሩን ተከትሎ የተቀሰቀሰው ጦርነት ከተጀመረ 47ኛ ቀኑን ይዟል። ከሁለቱም ወገን 15 ሺህ ገደማ ሰዎች የተገደሉበት ይህ ጦርነት እንዲቆም በርካቶች ሲያሳስቡ ቢቆዩም ጊዜያዊ የተኩስ አቁም ለማድረግ ከስምምነት ላይ ደርሰዋል፡፡ በጦርነቱ ምክንያት የኢትዮጵያ አየር መንገድን ጨምሮ በርካታ የዓለማችን አየር መንገዶች ወደ እስራኤል ሲያደርጉት የነበረውን በረራ አቋርጠው ቆይተዋል፡፡ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከህዳር 21 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ በጦርነት ምክንያት ተቋርጦ የነበረውን በረራ ዳግም እንደሚጀምር አስታውቋል፡፡ አየር መንገዱ አክሎም በሳምንት አምስት ቀናት ከአዲስ አበባ-ቴልአቪቭ ከተማ የቀጥታ በረራውን እንደሚያደርግ ገልጿል፡፡ የደርሶ መልስ ትራንስፖርት አገልግሎቱን በበረራ መስመር ኢት 404 እና 405 አውሮፕላኖቹ  እንደሚሰጥ የገለጸው አየር መንገዱ ሁሉንም የሳምንቱ ቀናት…
Read More
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በቡርኪናፋሶ አቻው 3 ለ 0 ተሸነፈ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በቡርኪናፋሶ አቻው 3 ለ 0 ተሸነፈ

ዋልያዎቹ በዓለም ዋንጫ የምድብ ማጣርያ ጨዋታ በቡርኪና ፋሶ አቻቸው 3 ለ 0 ተሸንፈዋል፡፡ የቡርኪናፋሶን የማሸነፊያ ግቦች ብላቲ ቱሬ በ69 ኛው፣ በርትራንድ ትራኦሬ በ78ኛው እንዲሁም ዳንጎ ኦታትራ 90ኛው ደቂቃ አስቆጥረዋል፡፡ ውጤቱን ተከትሎም በ2026 ካናዳ ሜክሲኮ እና አሜሪካ በጥምረት ለሚያዘጋጁት የአለም ዋንጫ ማጣሪያ በምድብ አንድ የተደለደለው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በምድቡ 1 ነጥብ በመያዝ አምስተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል፡፡ ብሔራዊ ቡድኑ በቀጣይ የአለም ዋንጫ የምድቡን ሶስተኛ እና አራተኛ የማጣሪያ ጨዋታዎች ከጊኒ ቢሳኦ እና ጅቡቲ ጋር የሚያደርግ ይሆናል፡፡
Read More
የአሜሪካው ራክሲዮ የቴክኖሎጂ ኩባንያ የዳታ ማዕከሉን በኢትዮጵያ ከፈተ

የአሜሪካው ራክሲዮ የቴክኖሎጂ ኩባንያ የዳታ ማዕከሉን በኢትዮጵያ ከፈተ

የዳታ ማዕከሉ 30 ሚሊዮን ዶላር ወጪ የተደረገበት ሲሆን በአፍሪካ 2ኛዉን የዳታ ማዕከል በአዲስ አበባ ከፍቷል። በአፍሪካ ገለልተኛ የመረጃ ማዕከል የሆነዉ ራክሲዮ ግሩፕ በኢትዮጵያ 2ኛዉን የዳታ ማዕከል በ30 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር ወጪ ኢንቨስትመንት በመገንባት አስጀምሯል። ኩባንያው የዳታ ማዕከሉን በአዲስ አበባ በአይሲቲ ፓርክ ውስጥ መክፈቱን የገለጸ ሲሆን የዳታ ፍሰትን ሙሉ በሙሉ በአገር ዉስጥ በማድረግ የአገልግሎቱ ተጠቃሚ ድርጅቶች ለኢንተርኔት የሚያወጡትን ወጪ ለመቀነስ ይረዳል ተብላል። በኢትዮጵያ የተከፈተዉ አዲሱ የደረጃ III የመረጃ ማዕከል 800 ራኮች እና እስከ 3MW የአይቲ ሃይል አለዉ ተብሏል። በ2018 የተቋቋመዉ ራክሲዮ በአፍሪካ የመጀመሪያውን የዳታ ማዕከል በኡጋንዳ እንደከፈተ ገልጿል። ኩባንያው ሁለተኛውን የዳታ ማዕከል በኢትዮጵያ ዛሬ ያስጀመረ ሲሆን እስከ ሚቀጥለው ዓመት ድረስም በኮንጎ  ፣…
Read More
ኢትዮጵያ ከኢንዱስትሪ ፓርኮች ከ1 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ አገኘች

ኢትዮጵያ ከኢንዱስትሪ ፓርኮች ከ1 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ አገኘች

ከኢንዱስትሪ ፓርኮች ወደ ውጭ ከተላኩ ምርቶች አንድ ነጥብ አንድ ቢሊዮን ዶላር መገኘቱ ተገልጿል፡፡ በኢትዮጵያ ከሚገኙ የኢንዱስትሪ ፓርኮች በአራት ዓመታት ውስጥ ወደ ውጪ ሀገራት ከተላኩ ምርቶች አንድ ነጥብ አንድ ቢሊዮን ዶላር መገኘቱን የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን አስታወቀ። በአዳማ ኢንዱስትሪ ፓርክ በዓመት 17 ሚሊዮን ዶላር ገቢ የሚያስገኙ የተለያዩ የፕላስቲክ ቱቦዎችን የሚያመርት ፋብሪካ ተመርቆ ሥራ ጀምሯል። የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ አክሊሉ ታደሠ፤ ኮርፖሬሽኑ ከሚያስተዳድራቸው 13 የኢንዱስትሪ ፓርኮች የተለያዩ ምርቶች ለውጭ ገበያ እየቀረቡ መሆኑን ተናግረዋል። ኢንዱስትሪ ፓርኮቹ ለተለያዩ ሀገራት ገበያ ከሚያቀርቧቸው ምርቶች በአራት ዓመታት ውስጥ አንድ ነጥብ አንድ ቢሊዮን ዶላር ገቢ መገኘቱን ሀላፊው ተናግረዋል፡፡ ከውጭ ሀገራት ይገቡ የመበሩ ምርቶችን በሀገር…
Read More
የኦሮሚያ ክልል ከአንድ ሺህ በላይ ሃኪሞችን ለመቅጠር ቢፈልግም ተቀጣሪ ማጣቱን ገለጸ

የኦሮሚያ ክልል ከአንድ ሺህ በላይ ሃኪሞችን ለመቅጠር ቢፈልግም ተቀጣሪ ማጣቱን ገለጸ

የኦሮሚያ ክልል ጤና ቢሮ 1ሺህ 1መቶ ሀኪሞችን ለመቅጠር ባለፈዉ ዓመት ሰኔ ወር 2015 ዓ.ም ማስታወቂያ ቢያወጣም ተቀጣሪዎችን ባለማግኘቱ በጀቱን ወደ ሌላ ዘረፍ ማዛወሩን ለኢትዮ ኤፍ ኤም አስታዉቋል፡፡ የቢሮዉ ምክትል ሃላፊ ዶ/ር ጉሻ በለኮ በሰኔ 2015 ላይ 1ሺህ 1መቶ ሀኪሞችን ለመቅጠር ማስታወቂያ የወጣ ቢሆንም ተቀጣሪዎችን ባለማግኘቱ ቢሮዉ በጀቱን ለሌላ ጉዳይ ማዋሉን ለጣቢያችን ተናግረዋል፡፡ ለ 2 ወራት ያክል ማስታወቂያዉን ክፍት ባደርግም ገበያ ላይ ተቀጣሪዎችን አላገኘሁም ብሏል ቢሮዉ፡፡ በየአንዳንዱ ጤና ተቋም ሀኪሞች መኖር ስላለባቸዉ ያንን ለማሟላት ማስታወቂያ ብናወጣም ሀኪሞችን ባለማግኘታችን በምትኩ የጤና ኤክስቴንሽን ባለሙያዎችን፣ አዋላጆችን እና ነርሶችን ለመቅጠር ተገደናል ነዉ ያሉት፡፡ ከዚህ በፊት ለመላዉ ኦሮሚያ አገልግሎት የሚሰጡ የጤና ባለሙያዎች ቁጥር 72ሺህ ነበር ያሉት…
Read More
ኢትዮጵያ ረጅም ዓመት ያገለገሉ ተሽከርካሪዎችን ልታግድ መሆኗን ገለጸች

ኢትዮጵያ ረጅም ዓመት ያገለገሉ ተሽከርካሪዎችን ልታግድ መሆኗን ገለጸች

በአዲስ አበባ ከፍተኛ ጭስ የሚለቅ መኪና ያላቸው አሽከርካሪዎች አስቀድመው መፍትሄ እንዲያዘጋጁ የአዲስ አበባ አካባቢ ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል፡፡ ተሸከርካሪዎች የሚለቁትን ጭስ የሚለካ መሳሪያ እና ጥራት ማስጠበቂያ ወይም ስታንዳርድ በመዘጋጀት ላይ እንደሆነም ተገልጿል፡፡ የአዲስ አበባ አካባቢ ጥበቃ ባለሥልጣን ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ድዳ ድሪባ እንደተናገሩት የመኪና ጭስ ስታንዳርድ እየተዘጋጀ ነው የተባለ ሲሆን እያንዳንዱ መኪና የሚያስወጣው ጪስ ይለካል ተብሏል። መኪናው ከተቀመጠው መለኪያ በላይ ጪስ የሚያመነጭ ከሆነ አገልግሎት እንዳይሰጥ ይደረጋል ብለዋል። አብዛኛውን ጊዜ ከፍተኛ ጭስ የሚለቁ ተሽከርካሪዎች ከተመረቱ 23 ዓመትና ከዚያ በላይ ያገለገሉ ናቸው ያሉት ኃላፊው፤ ስለዚህ አሮጌ መኪና ያላቸው አሽከርካሪዎች ከአሁኑ መፍትሄ ሊያዘጋጁ ይገባል ብለዋል። በመዲናዋ አሮጌና ከፍተኛ ጭስ የሚለቁ በርካታ መኪኖች መኖራቸውን…
Read More
ኖህ ሪል ኢስቴት 754 መኖሪያ ቤቶችን አስመረቀ

ኖህ ሪል ኢስቴት 754 መኖሪያ ቤቶችን አስመረቀ

ኖህ ሪል እስቴት አስረኛ ዓመቱን 754 አዳዲስ መኖሪያ ቤቶችን በማስረከብ አክብሯል ኖህ ሪል ስቴት ኃ/የተ/የግ/ማህበር 10ኛ አመት የምስረታ በአሉን  754 አዳዲስ የመኖሪያ ቤቶችን ገንብቶ በማስረከብ አክብሯል። በኢትዮጵያ የከተማ ልማት ከፍተኛ እድገት አበርክቶ ያለው ኖህ ሪል ኢስቴት ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት፣ ደንበኞቹና የሚዲያ አባላት ጋር አክብሯል። ኖህ ሪል እስቴት ባለፉት አስርት አመታት 8,000 በላይ ለሆኑ ቤተሰቦች በከፍተኛ ጥራት የተገነቡ ቤቶችን በታማኝነት፣ በሰዐቱ እና በቃሉ መሰረት አስረክቧል። ይህ ጉዞ ኩባንያውን በኢትዮጵያ የቤቶች ልማት ዘርፍ ቁልፍ ተዋናይ ሆኖ እንዲቀጥል አስችሎታል።  ለአገራዊ የልማት ግቦች ስኬትም ትልቅ አስተዋፅዖ እያደረገ ይገኛል። የኖህ ሪል ኢስቴት ዋና ስራ አስፈፃሚ ንፁህ አዉግቸዉ “በዛሬው ዕለት በኖህ ግሪን ፓርክ ሳይት አዲስ የተገነባውን …
Read More