ethiopianews

በደብረማርቆስ ከተማ በአራት ቀናት ውስጥ ከ100 በላይ ሰዎች መገደላቸው ተገለጸ

በደብረማርቆስ ከተማ በአራት ቀናት ውስጥ ከ100 በላይ ሰዎች መገደላቸው ተገለጸ

በምስራቅ ጎጃም ዞን ዋና ከተማ ደብረማረቆስ ከአርብ ነሐሴ 19/2015 እስከ ሰኞ ነሐሴ 22/2015 ድረስ በመከላከያ ሠራዊትና እና በፋኖ ታጣቂዎች መካከል በተደረገ ውጊያ፤ ከመቶ በላይ ሰዎች ሳይገደሉ እንዳልቀረ ተገልጿል። ሥማቸውን መጥቀስ ያልፈለጉ የደብረማርቆስ ስፔሻላይዝድ ሆሰፒታል ሐኪም በከተማዋ ቦሌ ተብሎ በሚጠራው ሰፈር ከመቶ በላይ ሰዎች መገደላቸውን ተናግረዋል ። የሟቾቹ አስክሬን ከኹለት ቀን በላይ ሳይነሳ መንገድ ላይ ወድቆ መታየቱንም ነዋሪዎች እና ሀኪሞች ለአዲስ ማለዳ ተናግረዋል። "በቦታው የወደቁትን አስከሬኖች፤ አንዳንድ ሰዎች ሙስሊሙንም ክርስቲያኑንም ኹሉንም እያነሱ ማሪያም ቤተክርስቲያን ውስጥ እና በአካባቢ ቀብረዋቸዋል፡፡ ነገር ግን ሰኞ ድረስ ያልተቀበሩም ነበሩ።" ሲሉ ነዋሪዎቹ ጠቅሰዋል፡፡ በከተማው ለሦስት ቀናት በተደረገው ውጊያ ቆስለው ወደ ሆስፒታል የሄዱ ጥቂት ሰዎች ቢኖሩም፤ የትራንሰፖርት እና…
Read More
በአማራ ክልል ከ50 በላይ ወረዳዎች ከመንግስት ቁጥጥር ውጪ መሆናቸው ተገለጸ

በአማራ ክልል ከ50 በላይ ወረዳዎች ከመንግስት ቁጥጥር ውጪ መሆናቸው ተገለጸ

በአማራ ክልል ባለዉ ጦርነት ምክንያት ክልሉ ከመንግሥት መዋቅር ውጪ ናቸው የተባሉ ወረዳዎች ይፋ ሆነዋል። መንግስት ከቁጥጥር ውጪ የሆኑ ወረዳዎች እና ከተማ አስተዳድር የባንክ ሂሳቦችን እንዳይንቀሳቀሱ እገዳ ጥሏል። ከሰሜን ሸዋ ወረዳዎች ውስጥ ሚዳ ወረሞ፣ መርሃቤቴ፣ አለም ከተማ ፣እነዋሪ፣ መንዝ ቀያ፣ መንዝ ላሎ፣ መንዝ፣ ማማ፣ መንዝ ሞላሌ ከተማ አስተዳድር፣ መንዝ ጌራ፣ ሲያደብር እና ዋዩ፣ እንሳሮ ፣ሞረትና ጅሩ ወረዳዎች ከመንግስት ቁጥጥር ውጪ ናቸው ተብሏል። ከሰሜን ወሎ ወረዳዎች ደግሞ ግዳን ወረዳ ፣እስታይሽ፣ ቡግና እና ሙጃ ወረዳዎች እንዲሁም ከደቡብ ወሎ ደፍሞ ወግዲ ወረዳ፣ ከለላ፣ መካነሰላም ፣ቦረና ፣ አማራ ሳይንት እና ዋድላ ደላንታ ወረዳዎች ከመንግስት ቁጥጥር ውጪ ናቸው የተባለ ሲሆን የመንግስት ተቋማት የባንክ ሂሳብ እንዳይንቀሳቀሱ እገዳ…
Read More
አፍሪካ ህብረት በአማራ ክልል ያለው ሁኔታ እንዳሳሰበው ገለጸ

አፍሪካ ህብረት በአማራ ክልል ያለው ሁኔታ እንዳሳሰበው ገለጸ

የአፍሪካ ህብረት ባወጣው መግለጫ በኢትዮጵያ አማራ ክልል ያለው ሁኔታ እንዳሳሰበው አስታውቋል። ህብረቱ በመገለጫው አክሎም የአፍሪካ ህብረት ሊቀመንበር ሙሳ ፋኪ መሀማት ጉዳቱን እየተከታተሉት እንደሆነም ገልጿል። ሊቀመንበሩ አክለውም በአማራ ክልል ያለውን ወታደራዊ ፍጥጫ በቅርበት እየተከታተሉት መሆኑንም አስታውቋል። አፍሪካ ህብረት ለኢትዮጵያ ህገመንግስታዊ ስርዓት፣ ሉዓላዊነት እና አንድነት ድጋፍ እንደሚያደርግም ህብረቱ በመግለጫው ላይ ጠቅሷል። ሁሉም የግጭቱ ተሳታፊ አካላት ንጹሀንን ከጉዳት እንዲጠብቁ እና ግጭት እንዲያቆሙ ያሳሰቡት ሊቀመንበሩ ወደ ውይይት እንዲመጡ እና ችግራቸውን እንዲፈቱም አስጠንቅቋል። ሙሳ ፋኪ አክለውም አፍሪካ ህብረት በኢትዮጵያ ሰላምና መረጋጋት እንዲመጣ ለሚደረጉ ውይይቶች ድጋፍ እንደሚያደርግ ተናግረዋል። የፌደራል መንግስት ባሳለፍነው ሚያዝያ ወር ላይ የክልል ልዩ ሀይሎችን መልሼ አደራጃለሁ በማለቱ በአማራ ክልል ተቃውሞ ገጥሞታል። ይህን ተከትሎም…
Read More
አሜሪካ እና የአውሮፓ ህብረት በአማራ ክልል ያለው አለመረጋጋት እንዳሳሰባቸው ገለጹ

አሜሪካ እና የአውሮፓ ህብረት በአማራ ክልል ያለው አለመረጋጋት እንዳሳሰባቸው ገለጹ

የተለያዩ አገራት በአማራ ክልል የተቀሰቀሰው ኹከትና የዜጎች ሞት እንዳሳሰባቸው ገለጹ በኢትዮጵያ የአውሮፓ ኅብረት ልዑክን ጨምሮ የተለያዩ አገራት ኤምባሲዎች ሰሞኑን በአማራ ክልል የተቀሰቀሰው ኹከት፣ የዜጎች ሞትና አለመረጋጋት እንዳሳሰባቸው ገልጸዋል። የአውሮፓ ኅብረት ልዑክ በኢትዮጵያን እና የኦስትሪያ፣ የቤልጂየም፣ የቼክ ሪፖብሊክ፣ የዴንማርክ ፣ የፊንላንድ፣ የፈረንሳይ፣ የጀርን፣ የሃንጋሪ፣ የአየርላንድ ፣ የኢጣሊያ፣ የሉክሰምበርግ፣ የማልታ፣ የኔዘርላንድስ፣ የሮማኒያ፣ የፖላንድ፣ የፖርቱጋል፣ የስሎቬንያ፣ የስፔን እና የስዊድን ኤምባሲዎች የአማራ ክልል ወቅታዊ ሁኔታን አስመልክተው የጋራ መግለጫ አውጥተዋል፡፡ በመግለጫቸውም በክልሉ የተቀሰቀሰው ኹከት፣ የዜጎች ሞትና አለመረጋጋት እንዳሳሰባቸው የገለጹ ሲሆን፤ ኹሉም ወገኖች ሲቪሎችን እንዲጠብቁ፣ ጉዳት ለደረሰባቸው ህዝቦች የተሟላ፣ ደህንነቱ የተጠበቀ እና ቀጣይነት ያለው ሰብአዊ ተደራሽነት እንዲረጋገጥ፣ የውጪ ዜጎች ከግጭቱ አካባቢ ለቅቀው እንዲወጡ እና ደህንነቱ በተጠበቀ…
Read More
በጎንደር እና ባህርዳር ያሉ ከአንድ ሺህ በላይ ሱዳናዊያን ችግር ውስጥ መውደቃቸውን ገለጹ

በጎንደር እና ባህርዳር ያሉ ከአንድ ሺህ በላይ ሱዳናዊያን ችግር ውስጥ መውደቃቸውን ገለጹ

በአማራ ክልል በተለይም ከአንድ ሳምንት በፊት አንስቶ በተከሰተው ጦርነት ምክንያት በክልሉ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መታወጁ ይታወሳል፡፡ በሱዳን በተከሰተው የእርስ በርስ ጦርነት ምክንያት የተሻለ ደህንነት ፍለጋ በሚል በተማ አድርገው ወደ ኢትዮጵያ የገቡ ሱዳናዊያን ዜጎች ችግር ውስጥ መግባታቸውን ለአልዐይን ተናግረዋል፡፡ በተለይም በጎንደር እና በባህርዳር ባሉ ሆቴሎች የቆዩ ሱዳናዊያን በምግብ እጥረት፣ ደህንነት እና ትራንስፖርት ችግር  ገጥሞናልም ብለዋል፡፡ ቁጥራቸው ከአንድ ሺህ በላይ እንደሚሆኑ የነገሩን እነዚህ ሱዳናዊያን መንገደኞች ወደ አዲስ አበባ በመምጣት ከዚያም ወደ ሳውዲ አረቢያ እና ሌሎች ሀገራት የመጓዝ አቅድን ይዘው ወደ ኢትዮጵያ እንደገቡ ተናግረዋል፡፡ ሱዳናዊያኑ በተለይም ከጎንደር እና ብህርዳር ከተሞች ውስጥ ባሉ ሆቴሎች ከተጠለሉት በተጨማሪም በመተማ በኩል አድርገው ወደ ኢትዮጵያ ድንበር ከገቡ በኋላ…
Read More
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ አማራ ክልል የሚያደርጋቸውን በረራዎች ሰረዘ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ አማራ ክልል የሚያደርጋቸውን በረራዎች ሰረዘ

አየር መንገዱ በድረገጹ እንዳስታወቀው ወደ ደሴ፣ ጎንደር፣ባህርዳር እና ላሊበላ የሚያደርገውን በረራ ሰርዣለሁ ብሏል፡፡ የተሰረዙት በረራዎች ነገ እና ከነገ በስቲያ ሊያደርጋቸው የነበሩ በረራዎች እንደሆኑ ገልጾ አየር መንገዱ ወደ ተጠቀሱት አካባቢዎች ለመጓዝ ትኬት የቆረጡ ደንበኞች በረራዎቹ እንደተመለሱ አስተናግዳለሁም ብሏል፡፡ ወደሥፍራው ለመጓዝ ትኬት የቆረጡ መንገደኞች ትኬታቸው ለአንድ ዓመት ያህል የሚያገለግል መሆኑን አውቃችሁ ወደፊት በፈለጋችሁት ቀን ያለምንም ተጨማሪ ክፍያ መቀየር ትችላላችሁም ብሏል፡፡ ገንዘቡን መመለስ እንፈልጋለን ለሚሉ ደንበኞችም ገንዘብ መመለስ እንደሚቻል ገልጾ በአቅራቢያችሁ ባሉ የአየር መንገዱ ቲኬት ቢሮዎች በመሄድ አገልግሎቱን ማግኘት እንደሚቻልም አስታውቋል፡፡ ይሁንና አየር መንገዱ በምን በረራዎቹን እንደሰረዘ ያልገለጸ ሲሆን በአማራ ክልል እየተካሄዱ ባለው ጦርነት ምክንያት ሊሆን እንደሚችል ተገምቷል፡፡ የሚኒስትሮች ምክር ቤት በአማራ ክልል…
Read More
መንግሥት ከአማራ ክልልል ጋር በተያያዘ ታዋቂ ግለሰቦችን ሳይቀር እያሰረ እንደሆነ ተገለጸ

መንግሥት ከአማራ ክልልል ጋር በተያያዘ ታዋቂ ግለሰቦችን ሳይቀር እያሰረ እንደሆነ ተገለጸ

ከታዋቂ ሰዎች መካከል አቶ ክርስቲያን ታደለ እና ድምጻዊ ዳኜ ዋለ ዋነኞቹ ናቸው። የአማራ ብሄራዊ ንቅናቄ (አብን) በመወከል የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል የኾኑት አቶ ክርስቲያን ታደለ ትናንት ምሽት አዲስ አበባ ውስጥ በፖሊስ ቁጥጥር ስር እንደዋሉ ታውቋል። አቶ ክርስቲያን በህ/ተ/ም/ቤት ያለመከሰስ መብት ያላቸው ቢሆንም በፖሊስ ታስረዋል ተብሏል። ፖሊስ አቶ ክርስቲያንን ለምን እንዳሠራቸው ያልገለጸ ሲሆን የአዲስ አበባ ምክር ቤት አባል ዶ/ር ካሳ ተሻገር እና ድምፃዊ ዳኜ ዋለም መታሰራቸው ተሰምቷል። ይህ በዚህ እንዳለም የመንግስት ኮሙንኬሽን ሚንስትርዶክተር ለገሰ ቱሉ ዛሬ በሰጡት መግለጫ በአማራ ክልል ያለውን የጸጥታ ችግር የሚያባብሱ ተናግረዋል ። ሚንስትሩ አክለውም የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ በዋናነት በአማራ ክልል ላይ የሚተገበር ቢሆንም፤ በየትኛው የአገሪቱ ክፍል…
Read More
ዶክተር ቴድሮስ አድሀኖም በአማራ ክልል ያለው አለመረጋጋት እንዳሳሰባቸው ገለጹ

ዶክተር ቴድሮስ አድሀኖም በአማራ ክልል ያለው አለመረጋጋት እንዳሳሰባቸው ገለጹ

ዶክተር ቴድሮስ አድሀኖም በአማራ ክልል ያለው አለመረጋጋት እንዳሳሰባቸው ገለጹ። የዓለም ጤና ድርጅት ዳይሬክተር ዶክተር ቴድሮስ አድሀኖም በትዊተር ገጻቸው ላይ እንዳሉት በአማራ ክልል ያለው አለመረጋጋት እንዳሳሰባቸው ገልጸዋል። በኢትዮጵያ ሁለተኛው ሰፊ የህዝብ ብዛት ያለው የአማራ ክልል ዋና ዋና መተላለፊያ መንገዶች መዘጋት የሰብዓዊ ድጋፍ ስራዎችን ያደናቅፋል ሲሉም ዶክተር ቴድሮስ ተናግረዋል። በክልሉ የኢንተርኔት መዘጋት የኮሙንኬሽን ስራውን አስቸጋሪ እንዳደረገውም ዳይሬክተሩ አክለዋል። ግጭቶች በህዝብ ጤና ላይ ወዲያውኑ ጉዳት ያደርሳሉ ያሉት ዶክተር ቴድሮስ ለተራዘመ የጤና እክሎች ይዳርጋሉም ብለዋል። በመሆኑም በአማራ ክልል የጤና መሰረተ ልማቶች ከጉዳት እንዲጠበቁ፣ የዓለም ጤና ድርጅት እና አጋሮች ስራቸውን እንደሚቀጥሉም ዶክተር ቴድሮስ አሳስበዋል። በተያያዘ ዜና በአማራ ክልል የተከሰተውን ግጭት ለመፍታት፤ በሌሎች የኢትዮጵያ ክልሎች የተጀመሩ…
Read More
አሜሪካ በአማራ ክልል የተቀሰቀሰው ግጭት እንዳሳሰባት ገለጸች

አሜሪካ በአማራ ክልል የተቀሰቀሰው ግጭት እንዳሳሰባት ገለጸች

የሀገሪቱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን ከጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ጋር በስልክ ተወያይተዋል። ብሊንከን በዚሁ ውቅት በአማራ እና ኦሮሚያ ክልል ያለው ሁኔታ ለቀጠናው ሰላምና ደህንነት ስጋት የሚፈጥር ነው ብለዋል። ግጭት በተከሰተባቸው አካባቢዎች የእርዳታ እህል በፍትሃዊ መንገድ በሚቀርብበት መንገድ ላይም የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ከጠቅላይ ሚኒስትር አብይ ጋር መክረዋል። በህዳሴው ግድብ ዙሪያ ያሉ ልዩነቶችንም በዲፕሎማሲያዊ መንገድ ለመፍታት አሜሪካ ሙሉ ድጋፍ እንደምታደርግ ብሊንከን ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ነግረዋቸዋል ተብሏል። በአማራ ክልል በሀገር መከላከያ እና ፋኖ መካከል ካሳለፍነው ሚያዝያ ጀምሮ ግጭት ውስጥ ገብተዋል። ግጭቱ ተባብሶ የቀጠለ ሲሆን የክልሉ መንግሥት ጉዳዩ ከአቅሜ በላይ ነው ሲል የፌደራል መንግሥት ጣልቃ እንዲገባ ጠይቋል። በክልል ያለው የጸጥታ ሁኔታ መባባሱን ተከትሎ የኢትዮጵያ…
Read More
የኢትዮጵያ አየር መንገድ የደሴ፣ ጎንደር፣ እና ላሊበላ በረራውን ሰረዘ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ የደሴ፣ ጎንደር፣ እና ላሊበላ በረራውን ሰረዘ

አየር መንገዱ በማህበራዊ ትስስር ገጾቹ ባሰራጨው መረጃ ወደ ደሴ፣ ጎንደር፣ እና ላሊበላ የሚያደርገውን በረራ ሰርዣለሁ ብሏል፡፡ የተሰረዙት በረራዎች ነገ እና ከነገ በስቲያ ሊያደርጋቸው የነበሩ በረራዎች እንደሆኑ ገልጾ አየር መንገዱ ወደ ተጠቀሱት አካባቢዎች ለመጓዝ ትኬት የቆረጡ ደንበኞች በረራዎቹ እንደተመለሱ አስተናግዳለሁም ብሏል፡፡ ይሁንና አየር መንገዱ በምን በረራዎቹን እንደሰረዘ ያልገለጸ ሲሆን በአማራ ክልል እየተካሄዱ ባለው ጦርነት ምክንያት ሊሆን እንደሚችል ተገምቷል፡፡ የሚኒስትሮች ምክር ቤት በአማራ ክልል በተከሰተው የጸጥታ ችግር ምክንያት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ማወጁ ይታወሳል፡፡ በአማራ ክልል ያጋጠመውን የፀጥታ መደፍረስ በመደበኛ የህግ ማስከበር ስርአት ለመቆጣጠር አዳጋች ሆኖ በመገኘቱ የፌደራል መንግስት አስፈላጊውን የህግ ማዕቀፍ እንዲተገብር የአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት መጠየቁ ይታወሳል። በአማራ ክልል በርካታ ከተሞች…
Read More