Gondar

ጎንደር ዩንቨርስቲ የተመሰረተበትን 70ኛ ዓመት እያከበረ ነው

ጎንደር ዩንቨርስቲ የተመሰረተበትን 70ኛ ዓመት እያከበረ ነው

ጎንደር ዩንቨርስቲ ከተቋቋመበት ጊዜ ጀምሮ 100 ሺህ ተማሪዎችን እንዳስመረቀ ተገልጿል። ዩንቨርሲቲው በኢትዮጵያ የጤና ባለሙያዎች ዕጥረት ለመፍታት በሚል በ1947 ዓ.ም መመስረቱም ተገልጿል። የዩንቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ዶ/ር አስራት አጸደወይን እንዳሉት ዩንቨርሲቲው በ70 ዓመት ታሪኩ 100 ሺህ ተማሪዎችን አሰልጥኖ አስመርቋል ብለዋል። በኢትዮጵያ የሐኪሞች ዕጥረትን ተከትሎ የውጭ ሀገራት የህክምና ባለሙያዎች ወደ ሀገር ውስጥ ይገቡ ይነበረ ሲሆን ጎንደር ዩንቨርሲቲ ይህ ችግር በቋሚነት እንዲፈታ የራሱን አስተዋጽኦ መወጣቱም ተጠቅሷል። ጎንደር ዩኒቨርስቲ ሕንፃ ለመጀመሪያ ጊዜ ሲገነባ መሬታቸውን ለሰጡ ግለሰቦች ዕውቅና በመስጠት የአርሶ አደሮች ቀንን እሰይማለሁም ብሏል። በተመሳሳይ በተለያየ መንገድ አሰተዋፅኦ ላደረጉለት ግለሰቦች የሕንፃ፣ የመንገድና የአዳራሽ ስያሜ ሊያደርግ መሆኑን አስታውቋል። ፕሬዚዳንቱ በመግለጫቸው ስያሜው በዩኒቨርስቲውና በሆስፒታሉ ታሪክ ጉልህ ድርሻ ለነበራቸው ግለሰቦች፣…
Read More
በጎንደር እና ባህርዳር ያሉ ከአንድ ሺህ በላይ ሱዳናዊያን ችግር ውስጥ መውደቃቸውን ገለጹ

በጎንደር እና ባህርዳር ያሉ ከአንድ ሺህ በላይ ሱዳናዊያን ችግር ውስጥ መውደቃቸውን ገለጹ

በአማራ ክልል በተለይም ከአንድ ሳምንት በፊት አንስቶ በተከሰተው ጦርነት ምክንያት በክልሉ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መታወጁ ይታወሳል፡፡ በሱዳን በተከሰተው የእርስ በርስ ጦርነት ምክንያት የተሻለ ደህንነት ፍለጋ በሚል በተማ አድርገው ወደ ኢትዮጵያ የገቡ ሱዳናዊያን ዜጎች ችግር ውስጥ መግባታቸውን ለአልዐይን ተናግረዋል፡፡ በተለይም በጎንደር እና በባህርዳር ባሉ ሆቴሎች የቆዩ ሱዳናዊያን በምግብ እጥረት፣ ደህንነት እና ትራንስፖርት ችግር  ገጥሞናልም ብለዋል፡፡ ቁጥራቸው ከአንድ ሺህ በላይ እንደሚሆኑ የነገሩን እነዚህ ሱዳናዊያን መንገደኞች ወደ አዲስ አበባ በመምጣት ከዚያም ወደ ሳውዲ አረቢያ እና ሌሎች ሀገራት የመጓዝ አቅድን ይዘው ወደ ኢትዮጵያ እንደገቡ ተናግረዋል፡፡ ሱዳናዊያኑ በተለይም ከጎንደር እና ብህርዳር ከተሞች ውስጥ ባሉ ሆቴሎች ከተጠለሉት በተጨማሪም በመተማ በኩል አድርገው ወደ ኢትዮጵያ ድንበር ከገቡ በኋላ…
Read More