ethiopianews

ዶክተር ቴድሮስ አድሀኖም በአማራ ክልል ያለው አለመረጋጋት እንዳሳሰባቸው ገለጹ

ዶክተር ቴድሮስ አድሀኖም በአማራ ክልል ያለው አለመረጋጋት እንዳሳሰባቸው ገለጹ

ዶክተር ቴድሮስ አድሀኖም በአማራ ክልል ያለው አለመረጋጋት እንዳሳሰባቸው ገለጹ። የዓለም ጤና ድርጅት ዳይሬክተር ዶክተር ቴድሮስ አድሀኖም በትዊተር ገጻቸው ላይ እንዳሉት በአማራ ክልል ያለው አለመረጋጋት እንዳሳሰባቸው ገልጸዋል። በኢትዮጵያ ሁለተኛው ሰፊ የህዝብ ብዛት ያለው የአማራ ክልል ዋና ዋና መተላለፊያ መንገዶች መዘጋት የሰብዓዊ ድጋፍ ስራዎችን ያደናቅፋል ሲሉም ዶክተር ቴድሮስ ተናግረዋል። በክልሉ የኢንተርኔት መዘጋት የኮሙንኬሽን ስራውን አስቸጋሪ እንዳደረገውም ዳይሬክተሩ አክለዋል። ግጭቶች በህዝብ ጤና ላይ ወዲያውኑ ጉዳት ያደርሳሉ ያሉት ዶክተር ቴድሮስ ለተራዘመ የጤና እክሎች ይዳርጋሉም ብለዋል። በመሆኑም በአማራ ክልል የጤና መሰረተ ልማቶች ከጉዳት እንዲጠበቁ፣ የዓለም ጤና ድርጅት እና አጋሮች ስራቸውን እንደሚቀጥሉም ዶክተር ቴድሮስ አሳስበዋል። በተያያዘ ዜና በአማራ ክልል የተከሰተውን ግጭት ለመፍታት፤ በሌሎች የኢትዮጵያ ክልሎች የተጀመሩ…
Read More
አሜሪካ በአማራ ክልል የተቀሰቀሰው ግጭት እንዳሳሰባት ገለጸች

አሜሪካ በአማራ ክልል የተቀሰቀሰው ግጭት እንዳሳሰባት ገለጸች

የሀገሪቱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን ከጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ጋር በስልክ ተወያይተዋል። ብሊንከን በዚሁ ውቅት በአማራ እና ኦሮሚያ ክልል ያለው ሁኔታ ለቀጠናው ሰላምና ደህንነት ስጋት የሚፈጥር ነው ብለዋል። ግጭት በተከሰተባቸው አካባቢዎች የእርዳታ እህል በፍትሃዊ መንገድ በሚቀርብበት መንገድ ላይም የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ከጠቅላይ ሚኒስትር አብይ ጋር መክረዋል። በህዳሴው ግድብ ዙሪያ ያሉ ልዩነቶችንም በዲፕሎማሲያዊ መንገድ ለመፍታት አሜሪካ ሙሉ ድጋፍ እንደምታደርግ ብሊንከን ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ነግረዋቸዋል ተብሏል። በአማራ ክልል በሀገር መከላከያ እና ፋኖ መካከል ካሳለፍነው ሚያዝያ ጀምሮ ግጭት ውስጥ ገብተዋል። ግጭቱ ተባብሶ የቀጠለ ሲሆን የክልሉ መንግሥት ጉዳዩ ከአቅሜ በላይ ነው ሲል የፌደራል መንግሥት ጣልቃ እንዲገባ ጠይቋል። በክልል ያለው የጸጥታ ሁኔታ መባባሱን ተከትሎ የኢትዮጵያ…
Read More
የኢትዮጵያ አየር መንገድ የደሴ፣ ጎንደር፣ እና ላሊበላ በረራውን ሰረዘ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ የደሴ፣ ጎንደር፣ እና ላሊበላ በረራውን ሰረዘ

አየር መንገዱ በማህበራዊ ትስስር ገጾቹ ባሰራጨው መረጃ ወደ ደሴ፣ ጎንደር፣ እና ላሊበላ የሚያደርገውን በረራ ሰርዣለሁ ብሏል፡፡ የተሰረዙት በረራዎች ነገ እና ከነገ በስቲያ ሊያደርጋቸው የነበሩ በረራዎች እንደሆኑ ገልጾ አየር መንገዱ ወደ ተጠቀሱት አካባቢዎች ለመጓዝ ትኬት የቆረጡ ደንበኞች በረራዎቹ እንደተመለሱ አስተናግዳለሁም ብሏል፡፡ ይሁንና አየር መንገዱ በምን በረራዎቹን እንደሰረዘ ያልገለጸ ሲሆን በአማራ ክልል እየተካሄዱ ባለው ጦርነት ምክንያት ሊሆን እንደሚችል ተገምቷል፡፡ የሚኒስትሮች ምክር ቤት በአማራ ክልል በተከሰተው የጸጥታ ችግር ምክንያት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ማወጁ ይታወሳል፡፡ በአማራ ክልል ያጋጠመውን የፀጥታ መደፍረስ በመደበኛ የህግ ማስከበር ስርአት ለመቆጣጠር አዳጋች ሆኖ በመገኘቱ የፌደራል መንግስት አስፈላጊውን የህግ ማዕቀፍ እንዲተገብር የአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት መጠየቁ ይታወሳል። በአማራ ክልል በርካታ ከተሞች…
Read More