05
Sep
ኢትዮጵያ የ2016 አዲስ ዓመትን ከአምስት ቀናት በኋላ የምታከብር ሲሆን በበዓሉ ዋዜማ የሙዚቃ ኮንሰርቶች ተዘጋጅተዋል። የአዲስ ዓመት ዋዜማ ዕለት ከሚዘጋጁ የሙዚቃ ድግሶች መካከል በአዲስ አበባ ሸራተን ሆቴል የተዘጋጀው አንዱ ነበር። በዚህ የሙዚቃ ኮንሰርት ላይ የውጭ ሀገራት እና ኢትዮጵያዊያን ሙዚቀኞች ስራዎቻቸውን እንደሚያቀርቡ ማስታወቂያዎች በሚዲያዎች በመተላለፍ ላይ ናቸው። ናይጀሪያዊው ዲቫይን ኢኩቦር ወይም በቅጽል ስሙ ሪማ በመባል የሚታወቀው ድምጻዊ ፣ ከሀገር ውስጥ ደግሞ ልጅ ሚካኤል፣ ኩኩ ሰብስቤ እና ሌሎችን ድምጻዊያን በዚህ የአዲስ ዓመት ኮንሰርት ላይ የሙዚቃ ስራቸውን እንደሚያቀርቡ ተገልጾ ነበር። ይሁንና ድምጻዊ ሬማ የክርስትና እምነት ላይ ከዚህ በፊት አሹፏል በሚል የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን አማኞች በዚህ ኮንሰርት ላይ እንዳይገኙ መልዕክት ማስተላለፏን ተከትሎ በርካቶች…