Nigeria

አርቲስቶች እና ስፖንሰሮች የአዲስ ዓመት ዋዜማ ሙዚቃ ኮንሰርቶችን ሰረዙ

አርቲስቶች እና ስፖንሰሮች የአዲስ ዓመት ዋዜማ ሙዚቃ ኮንሰርቶችን ሰረዙ

ኢትዮጵያ የ2016 አዲስ ዓመትን ከአምስት ቀናት በኋላ የምታከብር ሲሆን በበዓሉ ዋዜማ የሙዚቃ ኮንሰርቶች ተዘጋጅተዋል። የአዲስ ዓመት ዋዜማ ዕለት ከሚዘጋጁ የሙዚቃ ድግሶች መካከል በአዲስ አበባ ሸራተን ሆቴል የተዘጋጀው አንዱ ነበር። በዚህ የሙዚቃ ኮንሰርት ላይ የውጭ ሀገራት እና ኢትዮጵያዊያን ሙዚቀኞች ስራዎቻቸውን እንደሚያቀርቡ ማስታወቂያዎች በሚዲያዎች በመተላለፍ ላይ ናቸው። ናይጀሪያዊው ዲቫይን ኢኩቦር ወይም በቅጽል ስሙ ሪማ በመባል የሚታወቀው ድምጻዊ ፣ ከሀገር ውስጥ ደግሞ ልጅ ሚካኤል፣ ኩኩ ሰብስቤ እና ሌሎችን ድምጻዊያን በዚህ የአዲስ ዓመት ኮንሰርት ላይ የሙዚቃ ስራቸውን እንደሚያቀርቡ ተገልጾ ነበር። ይሁንና ድምጻዊ ሬማ የክርስትና እምነት ላይ ከዚህ በፊት አሹፏል በሚል የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን አማኞች በዚህ ኮንሰርት ላይ እንዳይገኙ መልዕክት ማስተላለፏን ተከትሎ በርካቶች…
Read More
ቢሊየነሩ አሊኮ ዳንጎቴ በኢትዮጵያ የስኳር ፋብሪካ ሊገዙ ነው

ቢሊየነሩ አሊኮ ዳንጎቴ በኢትዮጵያ የስኳር ፋብሪካ ሊገዙ ነው

የአፍሪካ ቁጥር አንድ ባለጸጋው ናይጀሪያዊው አሊኮ ዳንጎቴ በኢትዮጵያ የስኳር ፋብሪካ ለመግዛት እንደሚፈልጉ ተገልጿል። የኢትዮጵያ መንግሥት ከአንድ ዓመት በፊት በይዞታው ስር ያሉ የስኳር ፋብሪካዎችን መሸጥ እንደሚፈልግ መግለጹ ይታወሳል። በዚህ መሰረትም የስኳር ፋብሪካዎችን የመግዛት ፍላጎት ያላቸው ግለሰቦች እና ተቋማት ፍላጎታቸውን እንዲያሳውቁ ባወጣው ማስታወቂያ መሰረት ናይጀሪያዊው የአፍሪካ ቀዳሚ ቢሊየነር ፍላጎታቸውን ከገለጹ ባለሀብቶች መካከል አንዱ መሆናቸውን ሪፖርተር ዘግቧል። በኢትዮጵያ የሲሚንቶ ፋብሪካ ያላቸው አሊኮ ዳንጎቴ አሁን ደግሞ የስኳር ፋብሪካ የመግዛት ፍላጎት እንዳላቸው ተገልጿል። ከአሊኮ ዳንጎቴ በተጨማሪም ኮካ ኮላ ኩብንያም በኢትዮጵያ የስኳር ፋብሪካ ለመግዛት ከሚፈልጉ የቢዝነስ ተቋማት መካከል አንዱ ነው ተብሏል። የገንዘብ ሚኒስቴር እና የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ ሰዎች በዚህ ሳምንት የስኳር ፋብሪካዎቹን ጨረታ በተመለከተ በሰጡት መግለጫ…
Read More