Rema

ሸራተን ሆቴል የድምጻዊ ሬማ አዲስ ዓመት ዋዜማ ኮንሰርትን ሰረዘ

ሸራተን ሆቴል የድምጻዊ ሬማ አዲስ ዓመት ዋዜማ ኮንሰርትን ሰረዘ

የ2016 አዲስ ዓመትን አስመልክቶ በሸራተን አዲስ ሆቴል የሙዚቃ ድግስ መዘጋጀቱን የሚገልጹ ማስታወቂያዎች ሲተላለፉ ሰንብተዋል፡፡ በዚህ የአዲስ ዓመት ዋዜማ ላይ የሙዚቃ ስራዎቻቸውን የሚያቀርቡ ድምጻዊያን የማስታወቂያው አንድ አካል የነበሩ ሲሆን ናይጀሪያዊው ዲቫይን ኢኩቦር ወይም በቅጽል ስሙ ሪማ በመባል የሚታወቀው ድምጻዊ ከሌሎች ኢትዮጵያዊያን ድምጻዊያን ጋር በመድረኩ ላይ እንደሚዘፍኑ ተገልጾም ነበር፡፡ ይሁንና ድምጻዊ ሬማ ከክርስትና ሀይማኖት ጋር በተያያዘ ያልተገባ ነገር አድርጓል በሚል ይህን የአዲስ ዓመት ዋዜማ የሙዚቃ ድግስ ላይ ላለመገኘት በማህበራዊ የትስስር ገጾች ላይ ቅስቀሳ ሲደረግ ሰንብቷል፡፡ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያንም በይፋ የቤተ ክርስቲያን በዓላት ሲደርሱ ከሥርዓቷ እና ከአስተምሮዋ ውጪ በ ሆነ መልኩ የተለያዩ አካላት የዳንኪራ ጥሪ በማዘጋጀት የሚያደርጉት እንቅስቃሴ አግባብነት የሌለው መሆኑን…
Read More
አርቲስቶች እና ስፖንሰሮች የአዲስ ዓመት ዋዜማ ሙዚቃ ኮንሰርቶችን ሰረዙ

አርቲስቶች እና ስፖንሰሮች የአዲስ ዓመት ዋዜማ ሙዚቃ ኮንሰርቶችን ሰረዙ

ኢትዮጵያ የ2016 አዲስ ዓመትን ከአምስት ቀናት በኋላ የምታከብር ሲሆን በበዓሉ ዋዜማ የሙዚቃ ኮንሰርቶች ተዘጋጅተዋል። የአዲስ ዓመት ዋዜማ ዕለት ከሚዘጋጁ የሙዚቃ ድግሶች መካከል በአዲስ አበባ ሸራተን ሆቴል የተዘጋጀው አንዱ ነበር። በዚህ የሙዚቃ ኮንሰርት ላይ የውጭ ሀገራት እና ኢትዮጵያዊያን ሙዚቀኞች ስራዎቻቸውን እንደሚያቀርቡ ማስታወቂያዎች በሚዲያዎች በመተላለፍ ላይ ናቸው። ናይጀሪያዊው ዲቫይን ኢኩቦር ወይም በቅጽል ስሙ ሪማ በመባል የሚታወቀው ድምጻዊ ፣ ከሀገር ውስጥ ደግሞ ልጅ ሚካኤል፣ ኩኩ ሰብስቤ እና ሌሎችን ድምጻዊያን በዚህ የአዲስ ዓመት ኮንሰርት ላይ የሙዚቃ ስራቸውን እንደሚያቀርቡ ተገልጾ ነበር። ይሁንና ድምጻዊ ሬማ የክርስትና እምነት ላይ ከዚህ በፊት አሹፏል በሚል የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን አማኞች በዚህ ኮንሰርት ላይ እንዳይገኙ መልዕክት ማስተላለፏን ተከትሎ በርካቶች…
Read More