#5G

ኢትዮ ቴሌኮም በመላው አዲስ አበባ የ5G ኔትወርክ አገልግሎቱን ይፋ አደረገ

ኢትዮ ቴሌኮም በመላው አዲስ አበባ የ5G ኔትወርክ አገልግሎቱን ይፋ አደረገ

ኢትዮ ቴሌኮም የአምስተኛው ትውልድ (5G) የሞባይል አገልግሎትን በአዲስ አበባ በወዳጅነት አደባባይ በተካሄደ መርሃ ግብር በይፋ አስጀምሯል። በመርሃ ግብሩም ተቋሙ ከዚህ ቀደም በቅድመ ገበያ ሙከራ ደረጃ በአዲስ አባባ እና አዳማ ከተሞች አስጀምሮት የነበረውን የ5G የሞባይል አገልግሎት፤ በአዲስ አበባ የተለያዩ አካባቢዎች በሚገኙ በ145 ጣቢያዎች ማስጀመሩን አብስሯል። ይህ የ5G የሞባይል ኔትዎርክ አገልግሎት እስከ 10 ጊጋ ባይት በሰከንድ የሚደርስ ፍጥነት እንዳለው የተገለጸ ሲሆን፤ ዳታ የማስተላለፍ መዘግየትን እጅግ በላቀ ኹኔታ በመቀነስ ወደ 1 ሚሊ ሰከንድ ያደርሳል ተብላል። የ5G አገልግሎት በተለይም በተመሳሳይ ወቅት መከናወን የሚፈልጉ እንደ የማምረቻ ፋብሪካዎች፣ ግብርና፣ ሕክምና ለመሳሰሉ ዘርፎች የላቀ ፋይዳ እንዳለውም ተገልጿል። የ5G አገልግሎት ሥራ ላይ መዋል የማህበረሰቡን ሕይወት የሚያቀሉ ዲጂታል መፍትሄዎችን በቀላሉ…
Read More