Babileelephantpark

የባቢሌ የዝሆኖች መጠለያ ከ200 ሄክታር በላይ መሬት ደን ወደመ

የባቢሌ የዝሆኖች መጠለያ ከ200 ሄክታር በላይ መሬት ደን ወደመ

በኦሮሚያ ክልል ምሥራቅ ሐረርጌ ዞን የሚገኘው የባቢሌ የዝሆኖች መጠለያ ለእርሻ ኢንቨስትመንት በመሰጠቱ ከ200 ሄክታር በላይ የፓርኩ መሬት ደን ሙሉ ለሙሉ መውደሙን የኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ጥበቃ ባለስልጣን ገልጿል፡፡ የኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ጥበቃ ባለስልጣን የብሔራዊ ፓርኮች አስተዳደር መሪ ሥራ አስፈጻሚ ዶክተር አዳነ ጸጋዬ፤ የባቢሌን የዝሆኖች መጠለያ ፓርክ በምሥራቅ ሐረርጌ ዞን በኩል ለእርሻ ኢንቨስትመንት ተሰጥቶ ፓርኩ እየታረሰ በመሆኑ፣ በፓርኩ የሚገኙ ዝሆኖች ለአደጋ ተጋልጠዋል ብለዋል፡፡ የባቢሌን የዝሆኖች መጠለያ በሶማሌ እና በኦሮሚያ ክልሎች ድንበር ላይ የሚገኝ ሲሆን "በኦሮሚያ ክልል በኩል ያለው የፓርኩ ክፍል ለኢንቨስትመንት በመሰጠቱ አሁንም ድረስ እየታረሰ ነው" ሲሉ ገልጸዋል። የፓርኩ መሬት ለኢንቨስትመንት የተሰጠው ፓርኮችን ለመጠበቅና ለማስተዳደር ኃላፊነት የተሰጠው የኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ጥበቃ ባለስልጣን…
Read More