Business

ኢትዮጵያ ከ18 ሀገራት ጋር የንግድ ድርድር ጀመረች

ኢትዮጵያ ከ18 ሀገራት ጋር የንግድ ድርድር ጀመረች

ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት (WTO) አባልነት ድርድር ሂደት 6ኛው የሥራ ቡድን ስብሰባ ላይ፤ በሁለትዮሽ ንግድ ድርድር ዙሪያ 18 ሀገራት ጋር ድርድር ማድረግ መጀመሯን ንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡ የዓለም ንግድ ድርጅት 6ኛ የሥራ ቡድን ስብሰባ ባለፈው ሳምንት በስዊዘርላንድ ጄኔቫ መካሄዱ ይታወሳል። ይህ ስብሰባ ኢትዮጵያ የድርጅቱን አባልነት ጥያቄ ባቀረበች ከ20 ዓመታት በላይ ሂደት ውስጥ ወሳኝ ምዕራፍ የተመዘገበበት እንደነበር ሚኒስቴሩ ገልጿል። የድርድሩ ቡድን መሪ፣ ዋና ተደራዳሪ እና የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) የድርድር ሂደቱን አስመልክቶ፤ ለጋዜጠኞች መግለጫ ሰጥተዋል። በመግለጫቸውም ኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባል እንድትሆን እና ከተለያዩ ሀገራት ጋር ያለው የንግድ ትስስር እንድታጎለብት ለማድረግ ብርቱ ሥራ ሲሰራ መቆየቱን አስታውሰዋል፡፡ ከዚህ…
Read More
የባንኮች ብድር ዕድገት ጣሪያ ወደ 24 በመቶ አደገ

የባንኮች ብድር ዕድገት ጣሪያ ወደ 24 በመቶ አደገ

ብሔራዊ ባንክ አሁን ያለውን የዋጋ ግሽበት የመርገብ አዝማሚያ ለማስቀጠል እና የፋይናንስ ዘርፉን ጤናማነት ለመጠበቅ በመስከረም ወር ላይ ሊነሣ ይችላል ተብሎ የተገመተዉ የባንኮች ዓመታዊ የብድር ዕድገት ጣሪያን ሙሉ ለሙሉ ከማንሳት ይልቅ ገደቡ ለጊዜው ከ18 በመቶ ወደ 24 በመቶ ከፍ እንዲል ወስኗል፡፡ የባንኮች የብድር ዕድገት ገደብ መነሣት የብሔራዊ ባንክን የገንዘብ ፖሊሲ አቋም ለማመልከትና የገንዘብ ፖሊሲ መዋቅሩን የተሻለ ለማድረግ እንደሚረዳ ይታመናል ሲል ኮሚቴው አስረድቷል፡፡ ኮሚቴው  በጉዳዩ ላይ በወደፊት ስብሰባዎቹ ገምግሞ የውሳኔ ሐሳብ አንደሚያቀርብም ጠቅሷል፡፡ የብሔራዊ ባንክ የፖሊሲ ተመን አሁን ባለበት 15 በመቶ እንዲቆይም ወስኗል፡፡ ብሔራዊ ባንክ ለሚሰጣቸው የተቀማጭ ሂሳብ አገልግሎት እና የብድር አገልግሎት የሚከፈሉ የወለድ ተመኖች ባሉበት እንዲቀጥሉ፤ እንዲሁም ባንኮች በብሔራዊ ባንክ የሚያስቀምጡት…
Read More
ኢትዮጵያ የ6 መርከቦች ግዥ መፈፅሟ ተገለ

ኢትዮጵያ የ6 መርከቦች ግዥ መፈፅሟ ተገለ

የመርከቦቹ መገዛት በባህር ትራንስፖርት ላይ ያላትን አቅም የበለጠ ያሳድጋል ተብሎ ታምኖበታል፡፡ የባህር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ የሚያስተዳድራቸው 10 መርከቦች ባለቤት የሆነችው ኢትዮጵያ የማዳበሪያ ምርትን ጨምሮ የሚበዛውን ምርት የምታጓጉዘው እነዚህኑ መርከቦች ተጠቅማ ነው። አሁን ደግሞ የተጨማሪ ስድስት ትላልቅ መርከቦች ግዢ ተፈፅሞ ኢትዮጵያ መርከቦቹን ዘንድሮ እንደምትረከብ ተነግሯል። ይህም ኢትዮጵያ በውሃ ትራንስፖርት ላይ ያላትን አቅም የሚያሳድግ ነው ተብሏል። ከስድስቱ መርከቦች ሁለቱ እስከ 62,000 ቶን የመጫን አቅም ያላቸው እንደሆኑም ተነግሯል። ኢትዮጵያ አሁን ካሏት አስር መርከቦች አባይ ሁለት በመባል የምትጠራው እስከ 63,000 ቶን የመጫን አቅም እንዳላት ይነገራል። ባለፈው ዓመት ኢትዮጵያ ወደ ሀገር ውስጥ ካስገባችው 1.9 ሚሊየን ሜትሪክ ቶን የማዳበሪያ ምርት አብዛኛው ተጓጉዞ ጅቡቲ ወደብ የደረሰው በራሷ መርከቦች…
Read More
የመንግሥት አጠቃላይ የአገር ውስጥ የብድር እዳ ክምችት 2.5 ትሪሊዮን ብር ደረሰ

የመንግሥት አጠቃላይ የአገር ውስጥ የብድር እዳ ክምችት 2.5 ትሪሊዮን ብር ደረሰ

የመንግሥት አጠቃላይ የአገር ውስጥ የብድር ክምችት 2.5 ትሪሊዮን ብር መድረሱን፣ ከዚህም ውስጥ የግምጃ ቤት ቦንድ ግዥ ከፍተኛ ድርሻ ይይዛል ተብሏል፡፡ የገንዘብ ሚኒስቴር በዕዳ አስተዳደር ክፍል በኩል ያዘጋጀውን ወርኃዊ የዕዳ ማስታወቂያ የነሐሴ ወር 2017 ዓ.ም. ሪፖርት፣ የመንግሥት አገራዊ ብድር ዝርዝር መረጃ ይፋ አድርጓል፡፡ በዚህም መንግሥት እ.ኤ.አ. ከጁን 30 ቀን 2025 ጀምሮ አጠቃላይ የአገር ውስጥ ብድር 2.5 ትሪሊዮን ብር መድረሱን እንዳስታወቀ የሪፖርተር ዘገባ ያሳያል፡፡ ከአገር ውስጥ ብድር ድርሻ 80 በመቶ የሚይዘው በረዥም ጊዜ የሚከፈል የግምጃ ቤት ሰነድ እ.ኤ.አ. በኦገስት 2025 የግምጃ ቤት ሰነድ ግዥ ከፍተኛ እንደነበርና ከአጠቃላይ ክምችት አንፃርም 39 በመቶ እንደሚሸፍን ገልጿል፡፡ እስከ ኦገስት 2025 ድረስ ባለው የመንግሥት አጠቃላይ የአገር ውስጥ…
Read More
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዓመታዊ ገቢውን ወደ 25 ቢሊዮን ዶላር እንደሚያሳድግ ገለጸ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዓመታዊ ገቢውን ወደ 25 ቢሊዮን ዶላር እንደሚያሳድግ ገለጸ

አየር መንገዱ ከ10 ዓመት በኋላ ዓመታዊ ገቢውን 25 ቢሊዮን ዶላር የማድረስ እቅድ እንዳለው አስታውቋል። ከ10 ዓመት በኋላ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ገቢ 25 ቢሊዮን ዶላር የሚደርስ መሆኑን የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን ጣሰው ገለጹ፡፡ አቶ መስፍን እንደገለጹት አየር መንገዱ እ.ኤ.አ በ2035 ላይ 209 ዓለም አቀፍ እና 31 የሀገር ውስጥ መዳረሻዎች፣ 271 አውሮፕላኖች እንደሚኖሩትም ጠቅሰዋል፡፡ አየር መንገዱ 67 ነጥበ 2 ሚሊዮን መንገደኞችንም በማጓጓዝ ከ10 ዓመት በኋላ ገቢውንም 25 ቢሊዮን ዶላር ለማድረስ መታቀዱን ገልጸዋል፡፡ ለዚህም አዳዲስ መዳረሻዎችን በማስፋት ትስስሩን ይበልጥ ማጠናከር እና አዳዲስ መዳረሻዎችን መክፈት የሚያስፈልግ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡ ለዚህም አሁን በረራ ከሚደረግባቸው አምስቱ ክፍለ አኅጉሮች ተጨማሪ አውስትራሊያንም የሚጨመር መሆኑን…
Read More
ከተሽከርካሪዎች የሚወጣ በካይ ጋዝ የሚቆጣጠር መመሪያ ተዘጋጀ

ከተሽከርካሪዎች የሚወጣ በካይ ጋዝ የሚቆጣጠር መመሪያ ተዘጋጀ

‎በኢትዮጵያ ደረጃዎች ኢኒስቲትዩት የተዘጋጀው፤ ከተሽከርካሪዎች የሚወጣን ጎጂ የካይ ጋዝ ልቀት ለመቆጣጠር የሚያገለግለው አስገዳጅ መመሪያ ከመስከረም 30 ቀን 2018 ጀምሮ ተግባራዊ እንደሚደረግ የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ አስታውቋል። ዋነኛ ዓላማው የትራንስፖርት ዘርፉ ለበካይ ጋዝ ልቀት የሁለት ሦስተኛ ድርሻ ያለው በመሆኑ በጎጂ በካይ ጋዞች ምክንያት የሚከሰትን የአየር ብክለት መቀነስ ሲሆን፤ አዲሱ መመሪያ ሙሉ ለሙሉ ሲተገበር ተሽከርካሪዎች ወደ አየር የሚለቁትን የበካይ ጋዝ መጠን የሚቆጣጠር መሳሪያ እንዲገጥሙ ይገደዳሉ ተብሏል። የተቋሙ የትራንስፖርት ዘርፍ የአየር ንብረት ክትትል እና ቁጥጥር ቡድን መሪ አቶ ግርማ ሳሙኤል፤ የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ መመሪያው ከጸደቀበት መጋቢት 2017 ጀምሮ ውይይቶች ሲካሄዱበት እንደነበርም ተናግረዋል። በዚህም አስገዳጅ መመሪያው ከጸደቀ በኋላ ከታክሲ ማኅበራት፣ ከክልል ከተማ አስተዳደሮች…
Read More
ኢትዮጵያ ኢንተርኔትን በመዝጋት ከአፍሪካ ቀዳሚዋ ሀገር ተባለች

ኢትዮጵያ ኢንተርኔትን በመዝጋት ከአፍሪካ ቀዳሚዋ ሀገር ተባለች

ኢትዮጵያ ኢንተርኔትን በተደጋጋሚ በመዝጋትና የኢንተርኔትን ነጸነት በመገደብ ከአፍሪካ በአንደኛ ደረጃ ላይ መቀመጧን በብሉምስበሪ አሳታሚ ላይ የታተመ አንድ የጥናት መጽሐፍ አመላከተ። “የኢንተርኔት መዘጋት በአፍሪካ” በሚል ርእስ በፊሊሽያ አንቶኒዮ እና ቶኒ ሮበርትስ የተጠናውና መቀመጫውን በብሪታንያ ባደረገው ብሉምስበሪ አሳታሚ ድርጅት ላይ በመጸሐፍ መልክ ታትሞ የወጣው ጥናት በአውሮፓውያኑ አቆጣጠር ከ2016 እስከ 2024 በአህጉረ አፍሪካ በሀገራት የተፈጸመውን የኢንተርኔት መዘጋት ገምግሟል። በዚህም በአውሮፓውያኑ አቆጣጠር ከ2016 እስከ 2024 ባሉት በለፉት ዘጠኝ ዓመታት 193 የኢንተርኔት መዘጋት በአፍሪካ አህጉር መመዝገቡን ገልጿል። በተጠቀሱት ዘጠኝ ዓመታት ውስጥ በተፈጸሙ የኢንተርኔት መዘጋት ድግግሞሽ መጠኖች ሀገራትን በደረጃ ያስቀመጠው ጥናቱ ኢትዮጵያን በእነዚህ ዓመታት ውስጥ ሰላሳ ጊዜ ኢንትርኔት የዘጋች በሚል ከ55ቱ የአፍሪካ ሀገራት በአንደኛ ደረጃ አስቀምጧታል።…
Read More
ጣልያን በኢትዮጵያ የባቡር መስመር ግንባታ ለማድረግ ተስማማች

ጣልያን በኢትዮጵያ የባቡር መስመር ግንባታ ለማድረግ ተስማማች

የጣልያን ባቡር ኮርፖሬሽን ከኢትዮጵያ ምድር ባቡር ኮርፖሬሽን ጋር የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርሟል። መንግሥት በሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት ምክንያት የተቋረጠውን የአዋሽ- ኮምቦልቻ እና ሐራ ገበያ የባቡር መስመርን ለማጠናቀቅ ከፍተኛ ቁርጠኝነት አለኝ ብሏል። የአዋሽ- ኮምቦልቻ እና ሐራ ገበያ  የባቡር መስመርን ለማጠናቀቅ ከፍተኛ የመንግስት ቁርጠኝነት ምኖሩን የኢትዮጵያ ምድር ባቡር ኮርፖሬሽን አስታወቀ። የኮርፖሬሽኑ የህግ አገልግሎት ሃላፊ አቶ ካሳሁን ሙላቱ እንደገልፁት ኮርፖሬሽኑ የባቡር ትራንስፖርት አገልግሎትን ለማጠናከር ከኮይፓ ኢጣሊያ ጋር ስምምነት አድርጓል። ስምምነቱ አዳዲስ የባቡር መስመሮችን መዘርጋትን እንዲሁም እየተገነቡ ያሉ የባቡር መስመሮችን በፍጥነት አጠናቆ ወደ ስራ ማስገባትን የሚያካትት ነው ብለዋል። ከዛም ባለፈ በጋራ ድርጅቶችን ማቋቋም እንዲሁም ትላልቅ ዎርክ ሾፖሽን ማሻሻል ጨምሮ በርካታ ስትራቴጂካዊ ስራዎች የሚሰራበት የጋራ ስምምነት መሆኑን…
Read More
ለህዳሴው ግድብ ግንባታ 233 ቢልዮን ብር ወጪ መደረጉ ተገለጸ

ለህዳሴው ግድብ ግንባታ 233 ቢልዮን ብር ወጪ መደረጉ ተገለጸ

ለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ 233 ቢልዮን ብር ወጪ መደረጉን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አስታወቀ። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ምርቃትን አስመልክቶ ለመገናኛ ብዙሃን ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቷል። የተቋሙ የኮርፖሬት የኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ሞገስ መኮንን እንደተናገሩት ለህዳሴ ግድብ ግንባታ በአጠቃለይ 233 ቢልዮን ብር ወጪ ተደርጓል። ከዚህ ውስጥ 223 ቢልዮን ወይም 91 በመቶ የሚሆነው ወጪ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የተገኘ ነው ብለዋል። ከመላው ኢትዮጵያዊያን በቦንድ ግዢ 18 ነጥብ 9 ቢልዮን ብር የተሰበሰበ ሲሆን፤ በውጭ ከሚኖሩ ኢትዮጵያዊያንና ትውልደ ኢትዮጵያዊያን 1 ነጥብ 6 ቢልዮን ብር መሰብሰቡንም አቶ ሞገስ አብራርተዋል። እንዲሁም 3 ነጥብ 2 ቢልዮን ብር በስጦታ የተገኘ መሆኑን አንስተዋል። ላለፉት 14 ዓመት በግንባታ ላይ…
Read More
ንግድ ባንክ ለዲያስፖራዎች 50 ቢሊዮን ብር ብድር ለመስጠት ዝግጁ መሆኑን ገለጸ

ንግድ ባንክ ለዲያስፖራዎች 50 ቢሊዮን ብር ብድር ለመስጠት ዝግጁ መሆኑን ገለጸ

ንግድ ባንክ ለዲያስፖራው ማኀበረሰብ 50 ቢሊዮን ብር የብድር አገልግሎት አዘጋጅቼ እየጠበቀ መሆኑን አስታውቋል። የባንኩ የብድር አገልግሎቱ ለኢንቨስትመንት፣ ለመኖሪያ ቤትና አውቶሞቢል ግዥ የቀረበ ነው ተብሏል። የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፕሬዚደንት አቶ አቤ ሳኖ ሰሞኑን በተባበሩት አረብ ኤምሬቶች ከሚኖሩ ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያን  የዲያስፖራ ማህበረሰብ አባላት ጋር ተወያይተዋል፡፡ በውይይቱ ወቅት ፕሬዚደንቱ እንዳስታወቁት ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያን  የዲያስፖራ ማህበረሰብ አባላት በአገር ውስጥ ለሚያካሄዱት የቢዝነስ እንቅስቃሴ፣ ለመኖሪያ ቤትና መሰል ፍላጎቶች የ50 ቢሊዮን ብር የብድር አገልገሎት ተመቻችቷል ብለዋል፡፡ የብድር አገልግሎቱ በተያዘው የ2024/25 በጀት ዓመት ተፈጻሚ እንደሚሆንም ፕሬዝዳንቱ ተናግረዋል፡፡ ባንኩ አገልግሎቱን ለማግኘት ጥያቄ ለሚያቀርቡ የዲያስፖራ ማህበረሰብ አባላት ቀልጣፋና ምቹ አሰራር እንደሚተገብርም አቶ አቤ አስታውቀዋል፡፡ ሙሉ ለሙሉ የመንግስት…
Read More