Business

ኢትዮጵያ ከውጭ እርዳታ የምታገኘው ገቢ ማሽቆልቆሉ ተገለጸ

ኢትዮጵያ ከውጭ እርዳታ የምታገኘው ገቢ ማሽቆልቆሉ ተገለጸ

የኢትዮጵያ ኢኮኖሚክስ አሶሴሼን ባለፉት  2 ዓመታት ኢትዮጵያ ከውጪ የምታገኘው እርዳታ ማሽቆልቆሉን ባደረግሁት ጥናት አረጋግጫለው ብሏል። በተለይ ከ4 ዋና ዋና አበዳሪዎች ማለትም ፈረንሳይ፣ ጀርመን፣ እንግሊዝ እና አሜሪካ ለተከታታይ 3 ዓመታት የተገኘው እርዳታ እንደቀነሰ በጥናቴ አረጋግጫለሁ ብሏል። በየጊዜው ለኢትዮዽያ ኢኮኖሚ የሚበጀውን ሀሳብ የሚያዋጣውና የሚመክረው የኢትዮዽያ የኢኮኖሚክስ አሶሴሽን ተመራማሪዎች እና አጥኝዎች ሰሞኑን በኢትዮዽያ የውጪ  እዳ ጫና እና እርዳታ መዳከም ዙሪያ ውይይት አካሂደዋል። በተለይ ለኢትዮዽያ ይደረግ የነበረው የውጪ እርዳታ መቀነሱ የሚያመጣው ጫና እንዳለ በጥናቱ መብራራቱ ታውቋል። በህፃናት፣ በፋይናንስ አካታችነት፣ በወጣቶች ስራ ፈጠራ፣ በሴቶች እና ተያያዥ ጉዳዮች የተቋረጠው እርዳታ ምን ጫና አመጣ ኢትዮዽያስ ምን ማድረግ ይኖርባታል በሚለው ጉዳይ ምሁራኑ መክረዋል። አዲስ ካሳሁን (ዶ/ር) በኢትዮዽያ ኢኮኖሚክስ…
Read More
ኢትዮጵያ የአፍሪካ ነጻ የንግድ ቀጣና ግብይትን በይፋ ተቀላቀለች

ኢትዮጵያ የአፍሪካ ነጻ የንግድ ቀጣና ግብይትን በይፋ ተቀላቀለች

በኢትዮጵያ የመጀመሪያው የአፍሪካ ነጻ የንግድ ቀጣና ግብይት ሥርዓት በዛሬው ዕለት ተጀምሯል፡፡ የንግድ ማስጀመሪያው ፕሮግራሙን የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር አለሙ ስሜ (ዶ/ር) እና የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) ታድመዋል። ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) በዚህ ወቅት እንዳሉት የአፍሪካ ነጻ የንግድ ቀጣና ግብይት የኢትዮጵያን ወጪ ንግድ ከማሳለጥ ረገድ ከፍተኛ ሚና ይጫወታል ብለዋል፡፡ የንግድና ቀጠናዊ ተስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ ባስተላለፉት መልዕክት፣ የAfCFTA ግብይት የኢትዮጵያን ወጪ ንግድ ከማሳለጥ ባለፈ ለንግድ ዘርፉ ጉልህ አስተዋጽኦ እንደሚያበረክት ገልጸዋል። ከዚህ ባለፈም ለኢትዮጵያን ንግድ ዘርፍ መስፈንጠር ጉልህ አስተዋጽኦ እንደሚያበረክት አስገንዝበዋል፡፡ ግብይቱ መጀመሩን አስመልክቶ ሥጋ፣ አትክልትና ፍራፍሬ እንዲሁም ቡና፣ የጥራጥሬ ምርቶችና የቅባት እህሎች በኢትዮጵያ አየር መንገድ ካርጎና በየብስ ትራንስፖርት አማካይነት ወደ…
Read More
ኢትዮጵያ ታማኝ ግብር ከፋዮች በቪአይፒ ኤርፖርት እንዲስተናገዱ ፈቀደች

ኢትዮጵያ ታማኝ ግብር ከፋዮች በቪአይፒ ኤርፖርት እንዲስተናገዱ ፈቀደች

ወርቅ እና ከዚያ በላይ ሽልማት ያገኙ ታማኝ ግብር ከፋዮች በቪአይፒ ኤርፖርት እንዲስተናገዱ መወሰኑ ተገልጿል። ወርቅ እና ከዚያ በላይ ሽልማት ያገኙ ታማኝ ግብር ከፋዮች በቪ.አይ.ፒ ኤርፖርት እንዲስተናገዱ መንግሥት መወሰኑን ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) ትናግረዋል። ላለፉት አራት አመታት በታማኝነት ፕላቲኒየም ሽልማት ያገኙ 30 ልዩ ተሸላሚዎች የኢትዮጵያ ዜጎች ከሆኑ፤ የድርጅት ባለቤቶች ወይም ሥራ አስኪያጆች ዲፕሎማቲክ ፓስፖርት እንደሚሰጣቸውም ተገልጿል። ይህ የተገለጸው 7ኛው ዙር የታማኝ ግብር ከፋዮች የእውቅና መርሃ ግብር በትናንትናው ዕለት በተካሄደበት ወቅት ሲሆን በመርሃ ግብሩ 700 የሚደርሱ ተቋማት እና አልሚ ድርጅቶች እውቅና ተሰጥቷቸዋል። በዚህም 105 የሚሆኑት በፕላቲኒየም ደረጃ፣ 245 በወርቅ ደረጃ የተቀሩት 350 የሚሆኑት ደግሞ በብር ደረጃ ዕውቅና ያገኙ ናቸው ተሰጥቷቸዋል። ከዚህ…
Read More
ሳፋሪ ኮም ኢትዮጵያ ፍትሐዊ ባልሆነ ውድድር መፈቱን የአለም ባንክ ገለጸ

ሳፋሪ ኮም ኢትዮጵያ ፍትሐዊ ባልሆነ ውድድር መፈቱን የአለም ባንክ ገለጸ

የዓለም ባንክ ባወጣው አዲስ ሪፖርት፣ በኢትዮጵያ የቴሌኮም ገበያ በቅርቡ የገባው ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ፣ ከኢትዮ ቴሌኮም ጋር በሚደረገው ውድድር ፍትሃዊ ያልሆነ የመጫወቻ ሜዳ እንደገጠመውና ለከፍተኛ ኪሳራ እንደተዳረገ ይፋ አድርጓል። "የኢትዮጵያ የቴሌኮም ገበያ ግምገማ" በሚል ርዕስ የቀረበው ይህ ሪፖርት፣ በሁለቱ ኩባንያዎች መካከል ያለውን ያልተመጣጠነ ውድድር በዝርዝር ይተነትናል። ሪፖርቱ እንደሚለው፣ ኢትዮ ቴሌኮም እንደ ሳፋሪኮም 850 ሚሊዮን ዶላር የፈቃድ ክፍያ ባለመክፈሉና በስድስት የገበያ ዘርፎች ላይ የበላይነት ያለው ተቋም (SMP) ሆኖ በመቆጠሩ ውድድሩ ፍትሃዊ አይደለም። ኢትዮ ቴሌኮም ከደንብ አስከባሪው ከተቀመጠው የመገናኛ ዋጋ (MTR) በታች የድምጽ ጥሪ ዋጋ በማቅረቡ፣ ሳፋሪኮም ወደ ኢትዮ ቴሌኮም ደንበኞች በሚደረግ እያንዳንዱ ጥሪ ላይ ኪሳራ እንደሚያስተናግድ ሪፖርቱ ገልጿል (በወር 1.6 ሚሊዮን ዶላር ይገመታል)።…
Read More
በኢትዮጵያ የኢንተርፕርነርሺፕ ባንክ ሊቋቋም መሆኑ ተገለጸ

በኢትዮጵያ የኢንተርፕርነርሺፕ ባንክ ሊቋቋም መሆኑ ተገለጸ

በኢትዮጵያ ሥራ ፈጣሪ ወጣቶችን በፋይናንስ ለመደገፍ 'ኢንተርፕርነርሺፕ ኢንቨስትመንት ባንክ' ሊቋቋም መሆኑ ተገልጿል። ባንኩ በ20 ሚሊዮን ዶላር መነሻ ካፒታል የሚመሰረት ሲሆን፣ ወጣቶች ለድጋፍ የሚያስይዙት ዋስትና የፈጠራ ሀሳባቸውን ብቻ እንደሚሆን ተጠቁሟል። ባንኩን ለማቋቋም የሚያስችል የመግባቢያ ስምምነት በሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል እና በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ብሩክ ታዬ ፊርማ የተረጋገጠ ሲሆን፣ ተቋሙ ለወጣቶች የሥራ ዕድል ፈጠራ እና ለኢንተርፕራይዞች አቅም መጎልበት ወሳኝ ሚና እንደሚጫወት ተገልጿል። ይህ እርምጃ መንግስት የወጣቶችን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ያወጣቸውን ፖሊሲዎች ወደ ተግባር የመቀየር አካል መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትሯ ገልጸው፣ ባንኩ የወጣቶችን ጥያቄ በመመለስ የፈጠራ አቅማቸውን ለማጎልበት ያስችላል ብለዋል። ከመነሻ ካፒታሉ 10 ሚሊዮን ዶላር ከአፍሪካ ልማት ባንክ በድጋፍ…
Read More
ኢትዮጵያ 78 በመቶ የሬሚታንስ ገቢዋን እንደምታጣ ተገለጸ

ኢትዮጵያ 78 በመቶ የሬሚታንስ ገቢዋን እንደምታጣ ተገለጸ

ሀገሪቱ ከሬሚታንስ ገቢ 35 ቢሊዮን ዶላር ገቢ የማግኘት አቅም እንዳላት ተገልጿል ኢትዮጵያ ከውጭ ሀገራት በሕጋዊ መንገድ ከሚላክላት ገንዘብ (ሬሚታንስ) የምታገኘው ገቢ የሀገሪቱን አቅም 22 በመቶ ብቻ መሆኑ ተገልጿል። የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፕሬዝዳንት አቶ አቤ ሳኖ በተለያዩ ሀገራት ከሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን ዲያስፖራዎች ጋር በመወያየት ላይ ናቸው፡፡ ከዚህ በፊት በተባበሩት አረብ ኢምሬት እና ሳውዲ አረቢያ ከተሞች ከኢትዮጵያዊያን ዲያስፖራዎች ጋር የተወያዩት ፕሬዝዳንቱ አሁን ደግሞ በደቡብ አፍሪካ ፕሪቶሪያ ከተማ ከሚገኙ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ጋር ተወያይተዋል፡፡ ፕሬዝዳንቱ በዚህ ጊዜ እንዳሉት ኢትዮጵያ ከሬሚታንስ ገቢ እየተገኘች ያለው ገቢ 7.2 ቢሊየን ዶላር ብቻ ነዉ ብለዋል። አቶ አቤ ሳኖ እንዳስረዱት፣ አሁን ካለው የገንዘብ ፍሰት ቀሪው 78 በመቶ የሚሆነው ወደ ሀገር…
Read More
ኢትዮጵያ በዓመት 111 ሚሊዮን ሊትር የሚያመርት የጋዝ ማጣሪያ አስመረቀች

ኢትዮጵያ በዓመት 111 ሚሊዮን ሊትር የሚያመርት የጋዝ ማጣሪያ አስመረቀች

በዓመት 111 ሚሊየን ሊትር የሚያመርተው የኦጋዴን ፈሳሽ የተፈጥሮ ጋዝ ፕሮጀክት ተመርቋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሶማሌ ክልል ካሉብ በዓመት 111 ሚሊየን ሊትር ማምረት የሚችለውን የኦጋዴን ፈሳሽ የተፈጥሮ ጋዝ ፕሮጀክት የመጀመሪያ ዙር መርቀዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በምረቃ ስነ ስርዓቱ ላይ እንዳሉት በሶማሌ ክልል ካሉብ በዓመት 111 ሚሊየን ሊትር ማምረት የሚችለውን የኦጋዴን ፈሳሽ የተፈጥሮ ጋዝ ፕሮጀክት የመጀመሪያ ዙር መርቀናል ብለዋል። በተመሳሳይ በዓመት 1 ነጥብ 33 ቢሊየን ሊትር የማምረት አቅም የሚኖረውን ሁለተኛውን የነዳጅ ማጣሪያ ስራ ማስጀመራቸውንም ገልጸዋል፡፡ ማጣሪያው ከፈሳሽ ተፈጥሮ ጋዝ ምርት ባሻገር በኃይል ማመንጫ ዘርፉም 1 ሺህ ሜጋ ዋት የማመንጨት አቅም በመያዝ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው አስረድተዋል፡፡ ከሁሉም በላይ ፕሮጀክቱ የጋዝ ማምረቻ ብቻ…
Read More
በሶማሊ ክልል ጎዴ የአፈር ማዳበሪያ እና ነዳጅ ማጣሪያ ግንባታ ተጀመረ

በሶማሊ ክልል ጎዴ የአፈር ማዳበሪያ እና ነዳጅ ማጣሪያ ግንባታ ተጀመረ

ጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ የዩሪያ ማዳበሪያ እና ጌዴ ነዳጅ ማጣሪያ ግንባታን አስጀምረዋል። የዩሪያ አፈር ማዳበሪያ ፋብሪካ በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግ እና ዳንጎቴ ግሩፕ ጋር በመተባበር ይገነባል ተብሏል። ጎልደን ኮንኮርድ ግሩፕ ደግሞ የጎዴ ነዳጅ ማጣሪያ ፋብሪካን እንደሚገነባ ጠቅላይ ሚንስትሩ ገልጸዋል። የጎዴ ነዳጅ ማጣሪያ ከሂላል የነዳጅ ስፍራ ድፍድፍ ነዳጅ በማውጣት፣ በማጣራትና በማጠራቀም በአመት 3.5 ሚሊዮን ቶን የማምረት አቅም አለውም ተብሏል። በሌላ በኩልም የማዳበሪያ ፋብሪካው ከካሉብ የጋዝ ስፍራ በማውጣት እና 108 ኪሎሜትር የማጓጓዣ ቱቦ በመጠቀም በአመት 3 ሚሊዮን ቶን አምርቶ ያቀርባል። ከአንድ ወር በፊት አሊኮ ዳንጎቴ ግሩፕ ከኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግ ጋር የአፈር ማዳበሪያ ማምረቻ ኮምፕሌክስ ስምምነት መፈራረማቸው ይታወሳል፡፡ ፕሮጀክቱ በዓመት እስከ ሦስት ሚሊዮን ሜትሪክ…
Read More
አቢሲንያ ባንክ ሰባት ቢሊዮን ብር ማትረፉን ገለጸ

አቢሲንያ ባንክ ሰባት ቢሊዮን ብር ማትረፉን ገለጸ

አቢሲንያ ባንክ አጠቃላይ ሀብቱ ከ286 ቢሊዮን ብር በላይ መድረሱን አስታውቋል። አቢሲንያ ባንክ በዛሬው ዕለት ዓመታዊ የባለአክስዮኖች 29ኛ መደበኛ እና 16ኛ አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤው አካሂዷል። በጉባኤው ላይ እ.ኤ.አ በ2024/25 የሒሳብ ዓመት ሪፖርት የቀረበ ሲሆን፤ የባንኩ አጠቃላይ ሀብት 286 ነጥብ 2 ቢሊዮን ብር መድረሱን አስታውቋል፡፡ ይህም ካለፈው ዓመት አጠቃላይ ሀብት ማለትም ከ222 ነጥብ 3 ቢሊዮን ብር ጋር ሲነጻጸር የ63 ነጥብ 9 ቢሊዮን ወይም የ28 ነጥብ 8 በመቶ ዕድገት ማሳየቱን የአቢሲኒያ ባንክ የዳይሬክተሮች ቦርድ ሊቀመንበር አቶ መኮንን ማንያዘዋል ገልጸዋል። ባለፈው የሒሳብ ዓመት የባንኩ ጠቅላላ ገቢው 39 ነጥብ 1 ቢሊዮን ብር መድረሱን የገለጹ ሲሆን፤ ውጤቱ ካለፈው ተመሳሳይ ዓመት ጋር ሲነጻጸር የ11 ነጥብ 3 ቢሊዮን…
Read More
ኢትዮጵያ በ1 ቢሊዮን ዩሮቦንድ ዕዳ ዙሪያ አዲስ ውይይት ጀመረች

ኢትዮጵያ በ1 ቢሊዮን ዩሮቦንድ ዕዳ ዙሪያ አዲስ ውይይት ጀመረች

ኢትዮጵያ የ1 ቢሊዮን ዶላር ዩሮቦንድ ዕዳዋን እንደገና ለማዋቀር ከግል ባለቤቶች ጋር ሚስጥራዊ ውይይት ጀምራለች። የኢትዮጵያ መንግስት የ1 ቢሊዮን ዶላር የዩሮቦንድ ዕዳን እንደገና ለማዋቀር (restructure) ከዓለም አቀፍ የቦንድ ባለቤቶች ኮሚቴ ጋር ይፋዊ እና ሚስጥራዊነትን ያካተተ ውይይት መጀመሩን ብሉምበርግ ዘግቧል። ይህ እርምጃ ሀገሪቱ በከባድ የዕዳ ጫናዋን ለማቃለል በምታደርገው ጥረት ውስጥ እንደ ወሳኝ ምዕራፍ ተወስዷል። ውይይቱ "restricted" ተብሎ የተገለጸ ሲሆን፣ ይህ ማለት በድርድሩ ላይ የሚሳተፉት አበዳሪዎች (የቦንዱ ባለቤቶች) "የምስጢራዊነት ስምምነት" (NDA) መፈረም ነበረባቸው። ይህ ስምምነት የኢትዮጵያ መንግስት ለስምምነቱ መሳካት ወሳኝ የሆኑ ሚስጥራዊ የኢኮኖሚ መረጃዎችን ለአበዳሪዎቹ እንዲያካፍል ያስችለዋል። ስምምነቱን የፈረሙ ባለቤቶች በውይይቱ ወቅት የኢትዮጵያን ቦንድ መሸጥም ሆነ መግዛት አይችሉም። ይህ የውይይት እርምጃ የመጣው ኢትዮጵያ…
Read More