መነሻ ገፅ

በደራ ወረዳ ከ100 በላይ ሰዎች በኦነግ ሸኔ ታጣቂዎች ታግተዋል ተባለ

በደራ ወረዳ ከ100 በላይ ሰዎች በኦነግ ሸኔ ታጣቂዎች ታግተዋል ተባለ

በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ደራ ወረዳ ከ100 በላይ ሰዎች በኦነግ ሸኔ ታጣቂዎች መታገታቸውን የታጋቾች ቤተሰቦችና ነዋሪዎች ገልጸዋል፡፡  ታጣቂዎቹ ነዋሪዎችን ማገትና ማፈናቀል ከጀመሩ ረዥም ጊዜያት ቢቆጠሩም፣ በ2015 ግን ለተወሰኑ ወራት ፋታ አግኝቶ እንደነበር፣ ካለፈው ሳምንት ጀምሮ እንደ አዲስ እንደተቀሰቀሰና በዚህም ነዋሪዎቹ እየታገቱ፣ እየተፈናቀሉና ቤት እየተቃጠለ ነው ሲል ሪፖርተር ጋዜጣ ዘግቧል፡፡ በኦነግ ሸኔ ታጣቂዎች ቁጥጥር ሥር የነበሩ የደራ ወረዳ ሰባት ቀበሌዎችን ከሁለት ወራት በፊት በተደረገ ዘመቻ ነፃ ማድረግ ተችሎ እንደነበር ያስረዱት ነዋሪዎቹ፣ ካለፈው ሳምንት ጀምሮ ግን ጥቃት ማገርሸቱን አክለው ገልጸዋል፡፡ ጋዜጣው በስልክ አነጋገርኳቸው ያላቸው አምስት የወረዳው ነዋሪዎች እንደገለጹት፣ የአካባቢው ነዋሪዎች በታጣቂ ቡድኑ እየተሰቃዩ መሆናቸውን፣ በርካታ ሰዎች በየቀኑ እየታገቱና እየተፈናቀሉ እንደሆኑ፣ የታገቱ…
Read More
ኢትዮጵያ ህገ ወጥ የወርቅ እና ጫት ንግድ ፈተና እንደሆነባት ገለጸች

ኢትዮጵያ ህገ ወጥ የወርቅ እና ጫት ንግድ ፈተና እንደሆነባት ገለጸች

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ ከህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ለቀረበላቸው ጥያቄዎች ምላሽ ሰጥተዋል። ጠቅላይ ሚንስትሩ ህገ ወጥ የንግድ እንቅስቃሴ የሀገሪቱን የውጪ ምንዛሪ በከፍተኛ ደረጃ እየጎዳው ነው ብለዋል። በዘንድሮው ዓመት የወርቅ እና የጫት ምርት በኮንትሮባንድ ንግድ አማካይነት እየወጣ መሆኑንም ጠቅሰዋል፡፡ ከአንድ ዓመት በፊት ከአሶሳ 20 ኩንታል ወርቅ ወደ ማዕከላዊ ገበያ ይላክ ነበር ያሉት ጠቅላይ ሚንስትሩ በዚህ  ዓመት ግን ሶስት ኩንታል ብቻ መላኩ ለወርቅ ኮንትሮባንድ ንግድ መስፋፋት ማሳያ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ተናግረዋል፡፡ ከእዚህ ባለፈ የታንታለም ምርት በከፍተኛ ደረጃ ጉጂ ላይ ቢመረትም በህጋዊ መንገድ ወደ ውጪ ተልኮ የውጪ ገቢ ከሚያስገኘው ይልቅ በህገ ወጥ መንገድ ለጎረቤት ሀገራት የሚሸጠው ከፍተኛ ቁጥር እንዳለው አክለው አንስተዋል፡፡ ይህንኑ ከፍተኛ…
Read More
ጠቅላይ ሚኒሰትር አብይ አህመድ ስልጣን እንዲለቁ ተጠየቁ

ጠቅላይ ሚኒሰትር አብይ አህመድ ስልጣን እንዲለቁ ተጠየቁ

ጠቅላይ ሚኒስትር የመንግስታቸውን የስድስት ወራት አፈጻጸም ሪፖርት ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በማቅረብ ላይ ናቸው፡፡ ከአንድ የምክር ቤት አባልም ጠቅላይ ሚኒስትሩ ስልጣን እንዲለቁ ጠይቀዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ የዜጎችን ደህንነት እና የሀገርን ሉዓላዊነት መጠበቅ ዝቅተኛው የመንግስት ኃላፊነት ቢሆንም ይህንን እያደረጉ እንዳልሆነ ጥያቄ ቀርቦባቸዋል፡፡ ዜጎች በማንነታቸው ምክንያት በመንግስት የፀጥታ ኃይሎች ይገደላሉ፤ ይፈናቀላሉ፣ ቤታቸው ይፈርሳል፣ ንብረታቸው ይወድማል የሀገር ሉዓላዊነትን በሚዳፈር መልኩ የጎረቤት ሀገራት ሰራዊቶች በኢትዮጵያ ሰሜን ምዕራብ፣ እና ደቡብ ምዕራብ ወሰኖች በርከታ ኪሎ ሜትሮችን ዘልቀው በመግባት ወረራ ፈፅመዋል ሲሉም ከምክር ቤቱ አባላት ጥያቄ ቀርቦባቸዋል። የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን በሪፖርቱ ደጋግሞ በመንግስት የፀጥታ ኃይሎች ስለሚገደሉ ዜጎች፣ ስለሚፈፀሙ የሰብዓዊ መብት ወንጀሎች ፣ መፈናቀሎች፣ ግድያዎች ፣ ቤት መፍረሶች…
Read More
“የኢትዮጵያ የረቂቅ ሙዚቃ እናት” እማሆይ ፅጌማርያም ገብሩ አረፉ

“የኢትዮጵያ የረቂቅ ሙዚቃ እናት” እማሆይ ፅጌማርያም ገብሩ አረፉ

ፒያኖን በድንቅ ብቃት ስለሚጫወቱ “የፒያኖዋ እናት” የሚል ስያሜን ያገኙት እማሆይ ፅጌማርያም በ100 አመታቸው ነው ያረፉትእማሆይ ጽጌማርያም ከ150 በላይ የረቂቅ ሙዚቃ ድርሰቶችን የጻፉ ሲሆን፥ ሦስት አልበሞችን በሲዲ እና በሸክላ ላይ ማሳተማቸውም ይታወሳል በኢትዮጵያ ቀዳሚዋ የቫዮሊን እና ፒያኖ አቀናባሪ እማሆይ ፅጌማርያም ገብሩ በ100 ዓመታቸው አርፈዋል።እማሆይ ፅጌማርያም ከአባታቸው ከአቶ ገብሩ ደስታ እና እናታቸው ወይዘሮ ካሣዬ የለምቱ በ1915 ዓ.ም በአዲስ አበባ ውስጥ ነው የተወለዱት። እማሆይ ጽጌማርያም ገብሩ በልጅነታቸው ለትምህርት በሄዱባት ስዊዘርላንድ ፒያኖን በደንብ ተምረዋል። ከትምህርት መልስም በ19 አመታቸው ወደ ወሎ ግሸን ማርያም ገዳም በመሄድ በ21 አመታቸው ምንኩስናን መቀበላቸውን የኢቢሲ ዘገባ ያሳያል። ወላጆቻቸው ያወጡላቸው ስም የውብዳር ሲሆን ምንኩስናን ከተቀበሉ በኋላ መጠሪያቸው ወደ እማሆይ ፅጌማርያም ተቀይሯል።…
Read More
በአርባምንጭ ዙሪያ ጫሞ ሀይቅ ላይ በተፈጠረ  ማዕበል የስምንት ሰዎች ህይወት አለፈ

በአርባምንጭ ዙሪያ ጫሞ ሀይቅ ላይ በተፈጠረ ማዕበል የስምንት ሰዎች ህይወት አለፈ

በደቡብ ክልል ጫሞ ሐይቅ ላይ በጀልባ ሲጓዙ የነበሩ 8 ሰዎች ባጋጠማቸው የማዕበል አደጋ ምክንያት ሰጥመው ህይወታቸው አለፈ። " ኢትዮጵያ ኢንሳይደር " የአማሮ ልዩ ወረዳ ኮሚዩኒኬሽን ዋቢ አድርጎ እንደዘገበው አደጋው የደረሰው ትላንት ቅዳሜ ከሰዓት ለኃላ ነው። ባለሞተር ጀልባው የአማሮ ልዩ ወረዳ አልፋጮ ቀበሌ ነዋሪዎችን አሳፍሮ ወደ አርባ ምንጭ በመጓዝ ላይ እያለ በጫሞ ሐይቅ ላይ በነበረው ማዕበል የመስጠም አደጋው አጋጥማል። በአደጋው የጀልባውን ሹፌር ጨምሮ ስምንት ሰዎች ህይወታቸው አልፏል። አደጋው መከሰቱ እንደታወቀ የተጎጂዎችን ህይወት ለማትረፍ ጥረት ቢደረግም በጫሞ ሐይቅ ላይ በነበረው ከፍተኛ ማዕበል ምክንያት አልተሳካም። ከአደጋው መድረስ በኋላ ከአርባ ምንጭ ከተማ በመጡ ዋናተኞች ጭምር ሕይወት ለማዳን ቢሞከርም በሰዓቱ የነበረው ማዕበል አላስቻለም ተብሏል። በጫሞ…
Read More
የኢትዮጵያ ፖለቲካ ፓርቲዎች የህወሀትን ከሽብር መዝገብ መሰረዝን ተቃወሙ

የኢትዮጵያ ፖለቲካ ፓርቲዎች የህወሀትን ከሽብር መዝገብ መሰረዝን ተቃወሙ

የትግራይ ህዝብ ነጻነት ግንባት (ህወሀት) በትግራይ ክልል ያለውን የሀገር መከላከያ ሰሜን እዝ ላይ ጥቃት መክፈቱን ተከትሎ ነበር በሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት የተጀመረው። ለሁለት ዓመት የዘለቀው ይህ ጦርነት ከ800 ሺህ በላይ ዜጎችን እና ከ20 ቢሊዮን ዶላር በላይ ዋጋ የንብረት ውድመት አድርሷል። በፌደራል መንግሥት እና ህወሀት መካከል የተደረገው ይህ ጦርነት ባሳለፍነው ህዳር በአፍሪካ ህብረት አደራዳሪነት በደቡብ አፍሪካ የሰላም ስምምነት ተፈርሟል። ይህን ስምምነት ተከትሎም ጦርነቱ የቆመ ሲሆን በትግራይ ክልል ጊዜያዊ መንግሥት በመመስረት ላይ ይገኛል። እንዲሁም ህወሀት በግንቦት 2021 ላይ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በሽብርተኝነት ተፈርጆ ነበር። ይህ ህግ አውጪ ምክር ቤት ባሳለፍነው ሳምንት ህወሀትን ከሽብር መዝገብ ላይ ሰርዟል። የኢትዮጵያ ማህበራዊ ፍትህ ፓርቲ እና የአማራ…
Read More
የትግራይ አህጉረ ስብከት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ስርዓትን እንዲያከብር ቋሚ ሲኖዶስ ጠየቀ

የትግራይ አህጉረ ስብከት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ስርዓትን እንዲያከብር ቋሚ ሲኖዶስ ጠየቀ

የትግራይ አህጉረ ስብከት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ስርዓትን እንዲያከብር ቋሚ ሲኖዶስ ጠየቀ። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ ከሰሞኑ በትግራይ አህጉረ ስብከት በተሰጠ መግለጫ ዙሪያ ምላሽ ሰጥታለች። ቤተ ክርስቲያኗ በመግለጫዋ እንዳለችው በጦርነቱ ምክንያት በቤተ ክርስቲያኒቱ የበላይ መዋቅርና በትግራይ ክልል አህጉረ ስብከት መካከል አስተዳደራዊና መዋቅራዊ ግንኙነት ተቋርጦ መቆየቱን ገልጻለች። ይህንንም ተከትሎ በጦርነቱ ምክንያት ሁሉም የባንክ ተቋማት ሥራቸውን በማቆማቸው በየጊዜው እንደሌሎች አህጉረ ስብከት ለትግራይ አህጉረ ስብከት ይላክ የነበረው በጀት መላክ አልተቻለም ተብሏል፡፡ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ቀጣይ እርምጃ ምንድን ነው? ቤተክርስቲያኗ ተፈጥሮ የነበረውን ችግር በቀኖናው መሰረት መፈታቱን ገለጸችምንም እንኳን በባንክ መዘጋት ለአገልጋይ ሠራተኞች በጀት መላክ ባይቻልም የደመወዝ መክፈያ የባንክ…
Read More
ሊዮኔል ሜሲ በእግር ኳስ ህይወቱ 800ኛ ጎሉን አስቆጠረ

ሊዮኔል ሜሲ በእግር ኳስ ህይወቱ 800ኛ ጎሉን አስቆጠረ

አርጀንቲናዊው የዓለም ኮኮብ ሊዮኔል ሜሲ በእግር ኳስ ህይወቱ 800ኛ ጎሉን ከመረብ አገናኝቷል። በኳታር አዘጋጅነት የተካሄደው የዓለም ዋንጫን ያሸነፈው የአርጀንቲና ብሔራዊ ቡድን አምበል ሊዮኔል ሜሲ በህይወት ዘመኑ ያስቆጠራቸውን ጎሎች ወደ 800 ከፍ አድርጓል። የሰባት ጊዜ የባሎንዶር አሸናፊው ሜሲ ሀገሩ አርጀንቲና ከፓናማ ጋር የወዳጅነት ጨዋታ ተጫውታ 2ለ0 አሸንፋለች። የአርጀንቲናን የማሸነፊያ ጎሎች ቲያጎ አልማዳ በ11ኛው ደቂቃ እንዲሁም ሊዮኔል ሜሲ ደግሞ በ89ኛው ደቂቃ አስቆጥራል። ሊዮኔል ሜሲ ለአርጀንቲና ብሔራዊ ቡድን ተሰልፎ ያስቆጠራቸውን ጎሎች ወደ 99 ከፍ ሲያደርግ በቀጣይ የማጣሪያ ጨዋታቆች 100ኛ ግቡን እንደሚያስቆጥር ይጠበቃል። የቀድሞው የባርሴሎና እግር ኳስ ክለብ ተጫዋች ሊዮኔል ሜሲ ለባርሳ 672 እንዲሁም አሁን እየተጫወተበት ላለው ፒኤስጂ ደግሞ 29 ጎሎችን አስቆጥሯል። ሊዮኔል ሜሲ…
Read More
ኢትዮ ቴሌኮም ቴሌብር ሱፐር አፕ የተሰኘ አገልግሎት መስጫውን ይፋ አደረገ

ኢትዮ ቴሌኮም ቴሌብር ሱፐር አፕ የተሰኘ አገልግሎት መስጫውን ይፋ አደረገ

ኢትዮ ቴሌኮም ከዚህ በፊት የተለያዩ አገልግሎቶችን ይሰጥበት የነበረውን "ቴሌ ብር" መተግበሪያ አዘምኗል። ዛሬ ይፋ ያደረገው ይህ የደንበኞች አገልግሎት ከዚህ በፊት በአገልግሎት ላይ ከነበሩት ሶስት ተጨማሪ አገልግሎቶችን መስጠት ያስችላል። አዲሶቹ አገልግሎቶች የታቀደ ክፍያ፣ ለቡድን ገንዘብ መላክ እና የእድል ጨዋታዎችን ማከናወን የሚያስችሉ ናቸው። የታቀደ ክፍያ አገልግሎት ደንበኞች የገንዘብ እና አየር ሰዓት ለመላክ እንዲሁም ወርሀዊ የአገልግሎት ክፍያዎችን በቀኑ ለመክፈል ቀድመው ማቀድ የሚያስችል እንደሆነ ተቋሙ አስታውቋል። ሁለተኛው እና ዛሬ ይፋ የተደረገው የቴሌ ብር ተጨማሪ አገልግሎት ከአንድ በላይ ለሆኑ ተቀባዮች አስቀድመው በሚሞሉት መስፈርት መሰረት በአንዴ መላክ ያስችላልም ተብሏል። ሶስተኛው አዲስ አገልግሎት ደግሞ የእድል ጨዋታ የሚባል ሲሆን አጠቃቀምን መሰረት ያደረገ የአጓጊ ሽልማቶች ባለቤት የሚያደርግ እንደሆነ በፕሮግራሙ…
Read More
ሳፋሪ ኮም ከብሔራዊ ባንክ የሞባይል ገንዘብ ዝውውር ፈቃድ እንደሚሰጠው ገለጸ

ሳፋሪ ኮም ከብሔራዊ ባንክ የሞባይል ገንዘብ ዝውውር ፈቃድ እንደሚሰጠው ገለጸ

ብሔራዊ ባንክ ለሳፋሪኮም የሞባይል ገንዘብ ዝውውር በቅርቡ ፈቃድ እንደሚሰጥ አስታውቋል በኢትዮጵያ የመጀመሪያውን የግል የቴሌኮም አገልግሎት ፈቃድ ላገኘው ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ የሞባይል ገንዘብ ዝውውር አገልግሎት እንዲሰጥ የሚያስችለውን ፈቃድ በቅርቡ እንደሚሰጥ ብሔራዊ ባንክ ገልጿል። የብሔራዊ ባንክ ገዥ አቶ ማሞ ምህረቱ መጋቢት እንዳሉት መንግስት የፋይናንስ ዘርፉን ለማዘመንና ለማጠናከር  የተለያዩ እርምጃዎችን እየወሰደ ነው። ከባንክ ውጭ የሆኑ የቴሌኮሙኒኬሽን ኩባንያዎችን፣ ፊንቴክና የክፍያ ኤጀንቶችን የመሳሰሉ ተቋማት በክፍያ አገልግሎት ዘርፉ እንዲሳተፉ መደረጉንም ጠቅሰዋል። ባንክ ገዢው አቶ ማሞ አክለውም በአገሪቱ የመጀመሪያው የግል የቴሌኮም አገልግሎት አቅራቢነት ፈቃድ አግኝቶ ሥራ የጀመረው ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ የሞባይል ገንዘብ አገልግሎት እንዲሰጥ የሚያስችለውን ፍቃድ በቅርቡ እንደሚያገኝ ተናግረዋል። ይህም ዋና መቀጨውን በኬንያ ያደረገው ሳፋሪኮም በስፋት የሚታወቅበትን የኤም-ፔሳ የሞባይል…
Read More