Dera

በአማራ እና ኦሮሚያ አዋሳኝ አካባቢዎች ላይ 300 ዜጎች በታጣቂዎች ተገደሉ

በአማራ እና ኦሮሚያ አዋሳኝ አካባቢዎች ላይ 300 ዜጎች በታጣቂዎች ተገደሉ

የኦሮሚያ እና አማራ ክልል የሚዋሰኑበት የሰሜን ሸዋ ዞን ስራ የሚገኙ ወረዳዎች በኦነግ ሸኔ ታጣቂዎች ተደጋጋሚ ጥቃት እየደረሰባቸው ይገኛል፡፡ ደራ የተሰኘው ወረዳ ደግሞ በኦነግ ሸኔ ታጣቂዎች በተደጋጋሚ ጥቃት የሚደርስበት አካባቢ ሲሆን በሶስት ሳምንታት ውስጥ ብቻ 300 ንጹሃን ዜጎች በታጣቂዎች መገደላቸው ተገልጿል፡፡ ኦነግ ሸኔ ከሶስት ዓመት በፊት  በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በሽብርተኝነት ተፈርጆ መንግስት ይህን የሽብር ቡድን ለማጥፋት እርምጃ እየወሰድኩ ነው ቢልም ቡድኑ ጥቃት ማድረሱን ቀጥሏል፡፡ አንድ ሥማቸው እንዲጠቀስ ያልፈለጉ የደራ ወረዳ ነዋሪ ለአዲስ ማለዳ ጋዜጣ እንዳሉት "በሦስት ሳምንታ ውስጥ ከ300 በላይ ንጹሐን በሸኔ ታጣቂዎች ተገድለዋል።" ያሉ ሲሆን፤ ይህ እርሳቸው ያላቸው ትክክለኛ መረጃ እንደሆነ በመግለጽ፤ የሟቾች ቁጥር ከዚህ ሊያሻቅብ እንደሚችል እርግጠኛ መሆናቸውን…
Read More
በደራ ወረዳ ከ100 በላይ ሰዎች በኦነግ ሸኔ ታጣቂዎች ታግተዋል ተባለ

በደራ ወረዳ ከ100 በላይ ሰዎች በኦነግ ሸኔ ታጣቂዎች ታግተዋል ተባለ

በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ደራ ወረዳ ከ100 በላይ ሰዎች በኦነግ ሸኔ ታጣቂዎች መታገታቸውን የታጋቾች ቤተሰቦችና ነዋሪዎች ገልጸዋል፡፡  ታጣቂዎቹ ነዋሪዎችን ማገትና ማፈናቀል ከጀመሩ ረዥም ጊዜያት ቢቆጠሩም፣ በ2015 ግን ለተወሰኑ ወራት ፋታ አግኝቶ እንደነበር፣ ካለፈው ሳምንት ጀምሮ እንደ አዲስ እንደተቀሰቀሰና በዚህም ነዋሪዎቹ እየታገቱ፣ እየተፈናቀሉና ቤት እየተቃጠለ ነው ሲል ሪፖርተር ጋዜጣ ዘግቧል፡፡ በኦነግ ሸኔ ታጣቂዎች ቁጥጥር ሥር የነበሩ የደራ ወረዳ ሰባት ቀበሌዎችን ከሁለት ወራት በፊት በተደረገ ዘመቻ ነፃ ማድረግ ተችሎ እንደነበር ያስረዱት ነዋሪዎቹ፣ ካለፈው ሳምንት ጀምሮ ግን ጥቃት ማገርሸቱን አክለው ገልጸዋል፡፡ ጋዜጣው በስልክ አነጋገርኳቸው ያላቸው አምስት የወረዳው ነዋሪዎች እንደገለጹት፣ የአካባቢው ነዋሪዎች በታጣቂ ቡድኑ እየተሰቃዩ መሆናቸውን፣ በርካታ ሰዎች በየቀኑ እየታገቱና እየተፈናቀሉ እንደሆኑ፣ የታገቱ…
Read More