ዜና

የኢትዮጵያ እና አረብ ኢምሬት የጦር ጄቶች የጋራ አየር ትርኢት አካሄዱ

የኢትዮጵያ እና አረብ ኢምሬት የጦር ጄቶች የጋራ አየር ትርኢት አካሄዱ

የኢትዮጵያ አየር ሀይል የተመሰረተበትን 88ኛ ዓመት በማክበር ላይ ስትሆን በዛሬው ዕለት ከተባበሩት አረብ ኢምሬት የጦር ጄቶች ጋር በመሆን የአየር ላይ ትርዒት አድርገዋል፡፡ በአዲስ አበባ በተካሄደው በዚህ የጦር አውሮፕላኖች ትርዒት ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድን ጨምሮ በርካታ እንግዶች ተገኝተዋል፡፡ የሁለቱ ሀገራት የጦር አውሮፕላኖች ያካሄዱት የአየር ላይ ትርዒት “የጥቁር አንበሳ የአየር ትርዒት” የሚል ስያሜ እንደተሰጠው የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት አስታውቋል፡፡ ተቀማጭነታቸውን በአዲስ አበባ ያደረጉ ወታደራዊ አታሼዎች ባሳለፍነው ሳምንት ቢሾፍቱ የሚገኘውን የኢትዮጵያን አየር ሀይል ዋና ማዘዣን የጎበኙ ሲሆን በዛሬው በዓል ላይም ተገኝተዋል፡፡ የኢትዮጵያ አየር ኃይል በ1928 ዓ.ም የተመሰረተ ሲሆን በአፍሪካ ካሉ አየር ሀይሎች በእድሜ ትልቁ እንደሆነ ተገልጿል፡፡ በኢትዮጵያ ወታደራዊ ትርዒቶችን በአደባባይ ላይ ማክበር እየጨመረ የመጣ…
Read More
በቢሾፍቱ ከተማ በአምስት ቢሊዮን ዶላር አዲስ የኤርፖርት ከተማ ሊገነባ ነው

በቢሾፍቱ ከተማ በአምስት ቢሊዮን ዶላር አዲስ የኤርፖርት ከተማ ሊገነባ ነው

የኢትዮጵያ ዓየር መንገድ አዲሱን 5 ቢሊየን ዶላር ሚያወጣ ‘የኢትዮጵያ አየር  መንገድ ከተማ’ ግንባታ በአራት ዓመታት ውስጥ ለማጠናቀቅ እየሠራ መሆኑን ገለጸ፡፡ አየር መንገዱ “ኤርፖርት ሲቲ” ብሎ የሚጠራውን ግንባታ ለመጀመር ከጫፍ የደረሰው እየጨመረ የመጣውን የደንበኞች ፍላጎት ለማርካት መሆኑን የኢትዮጵያ ዓየር መንገድ የንግድ ሥራ ዘርፍ ዋና ሥራ አሥፈጻሚ ለማ ያደቻ ተናግረዋል፡፡ የ ‘ዓየር መንገድ ከተማው’ ካልተገነባ ዓየር መንገዱ በዘርፉ እያስመዘገበ ካለው ፈጣን ዕድገት አንጻር እንደሚፈተን ከግምት ውስጥ በማስገባት ፕሮጀክቱ መታቀዱን አብራርተዋል፡፡ ፕሮጀክቱ በአጠቃላይ 5 ቢሊየን ዶላር በጀት የተያዘለት ሲሆን፥ በዓመት 100 ሚሊየን መንገደኞችን ያስተናግዳል ተብሎ ይጠበቃል። አሁን ላይ ዓየር መንገዱ በኦሮሚያ ክልል ከቢሾፍቱ ከተማ ጥቂት ወጣ ብሎ በሚገኝ ሥፍራ የመጀመሪያውን የ ‘ዓየር መንገድ…
Read More
ብሔራዊ ሎተሪ የ8 ሚሊዮን ብር ተሸላሚ እድለኛ እንደጠፋበት ገለጸ

ብሔራዊ ሎተሪ የ8 ሚሊዮን ብር ተሸላሚ እድለኛ እንደጠፋበት ገለጸ

ብሔራዊ ሎተሪ አስተዳድር በየጊዜው ለሽፓጭ ከሚያውላቸው የእድል ሎተሪዎች መካከል የእንቁጣጣሽ ሎተሪ አንዱ ነው። 20 ሚሊዮን ብር የሚያሸልመው ይህ እጣ ባሳለፍነው ጷግሜ 2015 ዓም እጣው የወጣ ሲሆን 1820259 ደግሞ የመጀመሪያ እድለኛ ቁጥር እንደሆነ በወቅቱ ተገልጿል። የብሔራዊ ሎተሪ አስተዳድር ኮሙንኬሽን ዳይሬክተር አቶ ቴድሮስ ንዋይ ለዓልዐይን እንዳሉት "ባሳለፍነው ጷግሜ ላይ ከወጣው የእንቁጣጣሽ ሎተሪ ከሶስት እጣ አሸናፊ በስተቀር የሁለት እጣ አሸናፊዎች እስካሁን አልመጡም" ብለዋል። ብሔራዊ ሎተሪ አስተዳድሩ የሁለት እጣ እድለኞች ማለትም የስምንት ሚሊዮን ብር አሸናፊዎች እስከ ቀጣዩ የካቲት 30 ቀን 2016 ዓ.ም ድረስ ካልመጡ ገንዘቡ ለመንግሥት ገቢ ይሆናልም ብለዋል። 20 ሚሊዮን ብር ከሚያሸልመው እጣ ቁጥር ውስጥ እስካሁን በመተሀራ ከተማ በአንድ የግል ድርጅት ውስጥ በወዛደርነት…
Read More
ኤምፔሳ ሳፋሪኮም ከ1 ሚሊዮን በላይ ደንበኞቼን ልሸልም ነው አለ

ኤምፔሳ ሳፋሪኮም ከ1 ሚሊዮን በላይ ደንበኞቼን ልሸልም ነው አለ

ኤምፔሳ ሳፋሪኮም አዲስ ተጠቃሚ እና ግብይታቸውን በM-PESA የሚያካሒዱ ከአንድ ሚሊዮን በላይ ደንበኞችን፣ ወኪሎችን እና ነጋዴዎችን የሚሸልምበት ከታህሳስ 1 ቀን እስከ መጋቢት 2 ቀን 2016 ዓ.ም ድረስ የሚቆይ የ9ዐ ቀናት የሽልማት መርኃ ግብር ትናንት ታህሳስ 2 ቀን 2016 ዓ.ም በአዲስ አበባ በይፋ አስጀምሯል። ተረክ በኤምፔሳ ደንበኞች እና ድርጅቶች የኤምፔሳ አዲስ ተጠቃሚ በመሆናቸው እና ግብይታቸውን በኤምፔሳ በማካሔዳቸው የእጣ ቁጥሮችን በመሸለም ስለ ዲጂታል የፋይናንስ አገልግሎቱ የተሻለ ግንዛቤ ለመፍጠር እና አጠቃቀሙን ለማጎልበት ያለመ መርኃ ግብር ነው። በእጣዎቹ የሚገኙ ሽልማቶች አራት መኪኖች፣ 12 ባጃጆች፣ 2160 የስልክ ቀፎዎች እና የአየር ሰዓት ስጦታዎች ይሆናሉ፡፡ እያንዳንዳቸው ደንበኞች በአንድ ቀን የሚደርሳቸው ከፍተኛ የእጣ ብዛት 10 ሲሆን ይህም በየእለቱ፣ በሁለት…
Read More
ኢትዮጵያ ብድራቸዉን መክፈል ከማይችሉ ሀገራት ተርታ ተመደበች

ኢትዮጵያ ብድራቸዉን መክፈል ከማይችሉ ሀገራት ተርታ ተመደበች

መንግስት ከወሰደዉ የረጅም ጊዜ ብድር እና ወለድ አከፋፈል ዙሪያ ከአበዳሪዎች ጋር በዚህ ሳምንት ተጨማሪ ውይይት ለማድረግ ማቀዱ ተገልጿል የኢትዮጵያ መንግስት እ.ኤ.አ በ2014 በዩሮ ቦንድ ከተበደረዉ የ1 ቢሊዮን ዩሮ እና ወለዱን 33 ሚሊዮን ዶላር ገንዘብ የመክፈል አቅም ስለመኖሩ አበዳሪዎች ከጥርጣሬ ዉስጥ መገባታቸዉን ብሉምበርግ አስነብቧል። በዘገባዉ ኢትዮጵያ ዛምቢያንና ጋናን በመከተል በአፍሪካ የከሰሩ ሀገራት ተርታን ልትቀላቀል ከጫፍ የደረሰች መሆኑን ዘገባዉ ጠቅሷል። በተያዘዉ ሳምንት ሐሙስ መንግስት ከአበዳሪ አካላት ጋር ዉይይት የማድረግ እቅድ ስለመኖሩ በዘገባው ላይ ተጠቅሷል፡፡ መንግስት ከአንዳንድ አበዳሪ አካላት ጋር ባሳለፍነዉ ሳምንት የተገደበ ዉይይት አድርጎ አበዳሪዎች ኢትዮጵያ ያለባትን የ33 ሚሊዮን ዶላር የወለድ እዳ የመክፈል አቅም እንደሌላት ተገንዝበዋል ብሏል። ለዚህም ኢትዮጵያ የዉጭ ምንዛሬ መጠባበቂያ…
Read More
ፕሮፌሰር ሙላቱ ለማ የዓመቱ ምርጡ ፕሮፌሰር ተባሉ

ፕሮፌሰር ሙላቱ ለማ የዓመቱ ምርጡ ፕሮፌሰር ተባሉ

ዋና መቀመጫውን አሜሪካ ያደረገው ዓለም አቀፉ የፕሮፌሰሮች ማህበር ኢትዮጵያዊውን ፕሮፌሰር ሙላቱ ተሰማ የዓመቱ ምርጥ ምሁር በሚል እውቅና ሰጥቷል፡፡ ማህበሩ በየዓመቱ በመላው ዓለም ላሉ ፕሮፌሰሮች እውቅና የሚሰጥ ሲሆን የ2023 ዓመት እውቅናን ለኢትዮጵያዊው የሂሳብ ፕሮፌሰር ማድረጉ ተገልጿል፡፡ በመላው ዓለም ያሉ ፕሮፌሰሮች ባስገኙት ስኬት፣ የትምህርት አመራር፣ በሙያው ላይ ባደረጉት ቆይታ እና ሌሎች ጥረቶችን ከግምት ውስጥ በማስገባት በየዓመቱ በዚህ ማህበር ይሸለማሉ፡፡ በኢትዮጵያ ያለው የአሜሪካ ኢምባሲ ባወጣው መረጃ መሰረት ፕሮፌሰር ሙላቱ ተሰማ የመጀመሪያ እና ሁለተኛ ድግሪያቸውን ከአዲስ አበባ ዩንቨርሲቲ አግኝተዋል፡፡ የሶስተኛ ድግሪያቸውን ደግሞ በአሜሪካው ኬንት ስቴት ዩንቨርሲቲ እንዳገኙ የተገለጸው ፕሮፌሰር ሙላቱ ላለፉት 28 ዓመታት ደግሞ በዚያው በአሜሪካ ሳቫና ስቴት ዩንቨርሲቲ በማስተማር ላይ እንደሆኑ ተገልጿል፡፡ ፕሮፌሰር…
Read More
አማራ ባንክ ፕሬዝዳንቱን ከሀላፊነት አነሳ

አማራ ባንክ ፕሬዝዳንቱን ከሀላፊነት አነሳ

የአማራ ባንክ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ኄኖክ ከበደ ከሓላፊነታቸው ተነሱ የአማራ ባንክ የዲሬክተሮች ቦርድ ፕሬዝዳንቱ አቶ ሔኖክ ከበደ ባንኩን ለ460 ሚሊዮን ብር ኪሳራ ዳርገዋል በሚል ከሀላፊነት አንስቷል፡፡ ባንኩ ከዋና ሥራ አስፈጻሚው በተጨማሪም የኮርፖሬት አገልግሎት ዋና መኰንኑን አቶ ክንዴ አበበን፣ የአፈጻጸም ድክመት አሳይተዋል በሚል በባንኩ የዳይሬክተሮች ቦርድ ሊቀመንበር  መላኩ ፈንታ ፊርማ ከሓላፊነታቸው አንሥቷል። የባንኩ ቦርድ ውሳኔውን ያሳለፈው፣ ኹለቱም ከፍተኛ ሓላፊዎች፣ ከተሾሙበት ዕለት ጀምሮ፣ በየጊዜው በሚሳዩት የሥራ አፈጻጸም ድክመት፣ የባንኩን ስትራቴጂያዊ ግቦች እና ቁልፍ የአፈጻጸም መመዘኛዎችን ማሳካት አልቻሉም ተብሏል፡፡ ባንኩ በ2014/15 ዓ.ም. ከ306 ሚሊዮን ብር በላይ ትርፍ ለማስመዝገብ ዐቅዶ የነበረ ቢኾንም፣ ብር 460,286,000 ኪሳራ አስመዝግቧል፡፡ ከዚህ በተጨማሪም ፕሬዝዳንቱ በሌላቸው ሥልጣን ባሳለፉት አስተዳደራዊ…
Read More
ኢትዮጵያ በ50 ሚሊዮን ዶላር የትራክተር ፋብሪካ ልትገነባ መሆኗን ገለጸች

ኢትዮጵያ በ50 ሚሊዮን ዶላር የትራክተር ፋብሪካ ልትገነባ መሆኗን ገለጸች

ኢትዮ ኢንጂነሪንግ ግሩፕ በሞጆ ከተማ በ50 ሚሊዮን ዶላር የትራክተር ፋብሪካ ሊገነባ መሆኑን የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አምባሳደር ሱለይማን ደደፎ ተናግረዋል። ፋብሪካው ትራክተር የሚገጣጥም ሳይሆን ትራክተሩን ለማምረት የሚያስችሉ ዕቃዎችን የሚያመርት እራሱን የቻለ ፋብሪካ ይሆናልም ብለዋል። ተገዝተው በሚመጡ ትራክተሮች ብቻ የኢትዮጵያን ግብርና ማዘመን አይቻልም ያሉት አምባሳደር ሱሌይማን፤ ኢትዮጵያ የራሷን “ብራንድ” መትከል ስለሚገባት በሚሊዮን የሚቆጠር ትራክተር የሚያመርት ፋብሪካ መገንባት አለበት ብለን ወደ ተግባር በመግባት ላይ እንገኛለን ብለዋል። ፋብሪካው የትራክተር ሞተር ጭምር የሚያመርት ስለመሆኑ የጠቀሱ ሲሆን፤ ባሉን ፋብሪካዎችም የመኪና የውስጥ ክፍል “ሻንሲ” የመሥራት አቅም እያዳበርን በመሆኑ፤ ሞተር ማምረት ከቻልን መኪና የማምረት አቅም ላይ እንደሚደረስ ተናግረዋል፡፡ አሁን በመላ ሀገሪቱ በተጨባጭ ያሏት የትራክተሮች ቁጥር ከ100 ሺ…
Read More
ቦይንግ አምባሳደር ሔኖክ ተፈራን የአፍሪካ ዳይሬክተር አድርጎ ሾመ

ቦይንግ አምባሳደር ሔኖክ ተፈራን የአፍሪካ ዳይሬክተር አድርጎ ሾመ

የዓለማችን ስመ ገናናው የአቪዬሽን ተቋም ቦይንግ አምባሳደር ሔኖክ ተፈራን የአፍሪካ ዳይሬክተር አድርጎ መሾሙን አስታውቋል፡፡ ኩባንያው እንዳስታወቀው በፈረንሳይ የቀድሞ የኢትዮጵያ አምባሳደር ሔኖክ ተፈራን የአፍሪካ ማኔጂንግ ዳይሬክተር አድርጎ እንደሾመ አስታውቋል፡፡ ቦይንግ አምባሳደር ሔኖክን የሾመው ኩባንያው ከአፍሪካ ጋር የሚኖረውን የንግድ እና ሌሎች ግንኙነት እንዲያሳልጡለት መሆኑን ገልጿል፡፡ አምባሳደር ሔኖክ አዲስ አበባ ሆነው ስራቸውን ያከናውናሉ የተባለ ሲሆን በቦይንግ የመካከለኛው ምስራቅ፣ ቱርክ እና አፍሪካ ፕሬዝዳንት ለሆኑት ኩልጂት ጋታ አውራ ጋር ይሰራሉ ተብሏል፡፡ ቦይንግ የአፍሪካ ቢሮውን በአዲስ አበባ ከሚቀጥለው ዓመት ጀምሮ እንደሚከፍት የገለጸ ሲሆን አምባሳደር ሔኖክ ደግሞ የኩባንያውን የአፍሪካ ስራዎች እንደሚመሩ አስታውቋል፡፡ አምባሳደር ሔኖክ በአቪዬሽን ንግድ ዘርፍ እና መንግስታዊ ግንኙነቶችን በመምራት ጥሩ ልምድ እንዳለቸው የገለጸው ቦይንግ በአፍሪካ…
Read More
በኦሮሚያ የአንድ ቤተሰብ አባላት የሆኑ 11 ሰዎች ተገደሉ

በኦሮሚያ የአንድ ቤተሰብ አባላት የሆኑ 11 ሰዎች ተገደሉ

በአማራ፣ ኦሮሚያ እና ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልሎች የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች መቀጠላቸውን ኢሰመኮ ገለጸ፡፡ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) በአማራ፣ኦሮሚያ እና ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልሎች በተፈጸሙ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች ዙሪያ ሪፖርቱን ይፋ አድርጓል፡፡ እንደ ኢሰመኮ ሪፖርት ከሆነ በአማራ ክልል በአዊ ብሔረሰብ ዞን፣ በአየሁ ጓጉሳ ወረዳ እና በምዕራብ ጎጃም ዞን፣ ቡሬ ዙሪያ ወረዳ፤ እንዲሁም በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል፣ አሶሳ ዞን፣ ኦዳ ብልድግሉ ወረዳ፤ በተጨማሪም በኦሮሚያ ክልል፣ በአርሲ ዞን፣ ሸርካ ወረዳ እና በቄለም ወለጋ ዞን፣ ጊዳሚ ወረዳ በሲቪል ሰዎች ላይ ጥቃቶች መፈጸማቸውን ኮሚሽኑ አስታውቋል፡፡ በአማራ ክልል፣ በአዊ ብሔረሰብ ዞን አስተዳደር፣ በአየሁ ጓጉሳ ወረዳ፣ አምበላ ቀበሌ እና በዚገም ወረዳ ሶሪት ቀበሌ ከጥቅምት 29 ቀን 2016 ዓ.ም. ጀምሮ…
Read More