ዜና

የኢትዮጵያ ካቶሊክ ቤተክርስቲያን የተመሳሳይ ጾታ ጋብቻን እንደማትፈቀድ አስታወቀች

የኢትዮጵያ ካቶሊክ ቤተክርስቲያን የተመሳሳይ ጾታ ጋብቻን እንደማትፈቀድ አስታወቀች

የሮማ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ሊቀ ጳጳስ ፍራንሲስ ባሳለፍነው ሰኞ የቤተ-ክርስትያኗ ካህናት ለተመሳሳይ ፆታ ጥንዶች ቡራኬ መስጠት እንዲችሉ ፈቃድ መስጠታቸው ይታወሳል። ሊቀ ጳጳስ ፍራንሲስ አዲሱን የቫቲካን መመሪያ የሚያትቱ መዛግብትን ማፀድቃቸውን ተከትሎ ነበር የቤተ-ክርስትያኗ ካህናት ለተመሳሳይ ፆታ ጥንዶች ቡራኬ መስጠት እንዲችሉ ፈቃድ መስጠታቸው የተሰማው። ፖፕ ፍራንሲስ፤ የቤተ-ክርስትያኒቱ ቄሶች የተመሳሳይ ፆታ “ያልተለመዱ” ጥንዶችን በአንዳንድ ሁኔታዎች ቡራኬ መስጠት እንዲችሉ ፈቅጃለሁ ሲሉ ተሰምተዋል። ቫቲካን ይህንን ተከትሎ በሰጠው ማብራሪያ ይህ የሚሆነው በተለምዶ በቤተክርስትያኗ በሚካሄዱ ሥነ-ሥርዓቶች ላይ እንዳልሆነ እና አሁንም ቢሆን ትዳር በአንድ ወንድና ሴት መካከል የሚደረግ ሥነ-ሥርዓት እንደሆነ ነው የምናየው ብሏል። የኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን የጳጳሳት ጉባኤ ጠቅላይ ጽህፈት ቤት በጉዳዩ ላይ ከሰሞኑ ባወጣው መግለጫ፤ የሊቀ ጳጳሱ መልዕክት…
Read More
ኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅትን ለመቀላቀል አዲስ ተደራዳሪ ቡድን አዋቀረች

ኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅትን ለመቀላቀል አዲስ ተደራዳሪ ቡድን አዋቀረች

የዓለም ንግድ ድርጅት የአባልነት ድርድርን እና ቀጣናዊ የንግድ ትስስሮችን የሚመራ ብሔራዊ ኮሚቴ በአዲስ መልክ መቋቋሙን የንግድ እና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡ ኮሚቴው ከሚመለከታቸው የመንግስት ተቋማት ከፍተኛ አመራሮችን እንዲሁም ባለሙያዎችን ያካተተ ነው ተብሏል። ኢትዮጵያ የአለም ንግድ ድርጅት አባል ለመሆን በተለያዩ ጊዜያት ፍላጎቷን ብታሳይም ከአባል አገራት ለሚነሱ አንዳንድ የንግድ ዘርፍ አካታችነት አዎንታዊ ምላሽ መስጠት ባለመቻሏ ድርጅቱን መቀላቀል ሳትችል ቆይታለች። የጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ መንግስት ከአምስት ዓመት በፊት ወደ ስልጣን ሲመጣ የዓለም ንግድን በአባልነት መቀላቀል እንደሚፈልግ በይፋ ጥያቄ አቅርቧል፡፡ መንግስት ከወሰዳቸው ስር ነቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያዎች እና አዳዲስ ለውጦች መካከል አገሪቱን በ2021 የአለም ንግድ ድርጅት አባል ማድረግ ይገኝበታል። በዚህም ከ2020 አንስቶ ድርድር እንደ አዲስ…
Read More
ኢትዮጵያ 6 ሚሊዮን ዶላር በስህተት ለሌላ ወገን መክፈሏ ተገለጸ

ኢትዮጵያ 6 ሚሊዮን ዶላር በስህተት ለሌላ ወገን መክፈሏ ተገለጸ

ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ልማት ባንክ ዓመታዊ መዋጮ መከፈል የነበረበትን ስድስት ሚሊዮን ዶላር ገንዘብ በስህተት ወደ ሌላ አካውንት መላኳ ተገልጿል፡፡ የአፍሪካ ልማት ባንክ ከአንድ ወር በፊት በአዲስ አበባ ያሉ ሁለት የባንኩ ሰራተኞች በኢትዮጵያ የጸጥታ ሀይሎች ድብደባ፣ እስር እና እንግልት እንደደረሰባቸው አስታውቆ ነበር። ባንኩ እንዳለው ሁለት ሰራተኞቹ የቬና የዲልሎማሲ ጥበቃ ስምምነትን እና የአፍሪካ ልማት ባንክ ቢሮ አስተናጋጅ ሀገራት ስምምነትን የጣሰ ክስተት በኢትዮጵያ መፈጸሙንም ገልጿል። የተፈጠረውን ክስተት ለኢትዮጵያ መንግሥት በይፋ ማመልከቱን የሚገልጸው የአፍሪካ ልማት ባንክ ጉዳዩ መፈጸም እንደሌለበት፣ ህግ መጣሱን እና ጉዳዩ ተመርምሮ እርምጃ እንደሚወሰድ በኢትዮጵያ በኩል ቃል ተገብቶልኛል ሲልም በወቅቱ አስታውቆ ነበር፡፡ ባንኩ አሁን ላይ በጉዳዩ ዙሪያ ባወጣው መግለጫ የኢትዮጵያ መንግስት ቃል በገባው…
Read More
ካሊፎርኒያ ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት 102 የዲጂታል ማርኬቲንግ  ሰልጣኞቹን አስመረቀ

ካሊፎርኒያ ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት 102 የዲጂታል ማርኬቲንግ  ሰልጣኞቹን አስመረቀ

ከሁለት ዓመት በፊት በዲጂታል ስልጠናዎች ዘርፍ የተሰማራው ካሊፎርኒያ ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት በአጫጭር ስልጠናዎች ያሰለጠናቸውን ተማሪዎች አስመርቋል፡፡ ድርጅቱ ከሚጣቸው ስልጠናዎች መካከልም በዲጂታል ማርኬቲንግ፣ ዌብሳይት ማበልጸግ፣ ኮዲንግ፣ግራፊክ ዲዛይኒንግ እና ተዛማጅ ሙያዎች ዋነኞቹ ናቸው፡፡ መሰረታዊ የኮምፒዩተር እውቀት ካላቸው ፣ማህበራዊ ሚዲያዎችን መጠቀም የሚችሉ ሰዎች ማንኛውም ማንበብ እና መጻፍ የሚችሉ ሰዎች ስልጠናውን ማግኘት እንደሚችሉም የኢንስቲትዩቱ ስራ አስኪያጅ አቶ ሱራፌል አሰፋ በምረቃው ወቅት ተናግረዋል፡፡ ተማሪዎቹ  ለአንድ ወር  ተኩል የተግባር ትምህርትን ጨምሮ  የተለያዩ መሰረታዊ ስልጠናዎችን አግኝተዋል።  ከተመራቂዎቹ  ውስጥ   ከግማሽ በላይ  ወንዶች ሲሆኑ  የዛሬ ተመራቂዎቹ   ሁለተኛ ዙር ተመራቂዎቹ ናቸው። በዲጂታል ማርኬቲንግ  ኢንተርኔትን በመጠቀም  በሞባይል ስልክ  ፣ በማህበራዊ ሚዲያ መድረኮችን፣ ዌብናሮችን፣ በሰርች ኤንጅ ሌሎች ዲጂታል መድረኮችን  በመጠቀም የዛሬ ተመራቂዎች ምርትና…
Read More
በአማራ ክልል የሚገኙ 10 ዩንቨርሲቲዎች በጦርነት ምክንያት ተማሪዎቻቸውን መጥራት አልቻሉም

በአማራ ክልል የሚገኙ 10 ዩንቨርሲቲዎች በጦርነት ምክንያት ተማሪዎቻቸውን መጥራት አልቻሉም

አማራ ክልል የሚገኙ አስር ዩኒቨርሲቲዎች በክልሉ ባለው የፀጥታ ችግር ምክንያት ለነባር እንዲሁም አዲስ ለተመደቡ ተማሪዎቻቸው ጥሪ ሳያደርጉ ወራት መቆጠሩ ይታወቃል፡፡ ከአማራ ክልል ውጪ የሚገኙ ዩንቨርስቲዎች ተማሪዎቻቸውን ጠርተው በማስተማር ላይ ሲሆኑ በአማራ ክልል ባሉ ዩንቨርስቲዎች የተመደቡ ተማሪዎች ግን እስካሁን አልተጠሩም። ይህንን ተከትሎም ተማሪዎቹ ለስነልቦና እና ለተለያዩ ችግሮች መጋለጣቸውን በተደጋጋሚ በማንሳት ላይ ሲሆኑ ዩኒቨርሲቲዎቹ ጥሪ ሳያደርጉ አራት ወራት በማለፉ ተስፋ መቁረጥ ውስጥ መግባታቸውንም ይጠቁማሉ፡፡ "ያለ ትምህርት ቁጭ ብለን ወራት አልፈዋል፣ ፍትህ እንሻለን" የሚሉት ተማሪዎቹ፤ ወደ ሌሎች የትምህርት ተቋማት በጊዚያዊነት መዘዋወርን ጨምሮ አማራጭ መፍትሔዎች እንዲፈለግላቸው ጠይቀዋል፡፡ የትምህርት ሚኒስቴር በበኩሉ በአማራ ክልል ያሉ ዩንቨርሲቲዎች በቅርቡ ለተማሪዎቻቸው ጥሪ እንዲያስተላልፉ መግባባት ላይ መደረሱን አስታውቋል፡፡ በትምህርት ሚኒስቴር…
Read More
ቢጂአይ ኢትዮጵያ በጦርነት ምክንያት ስራው መጎዳቱን ገለጸ

ቢጂአይ ኢትዮጵያ በጦርነት ምክንያት ስራው መጎዳቱን ገለጸ

በኢትዮጵያ ካሉ አልኮል አምራች ኩባንያዎች መካከል ዋነኛው የሆነው ቢጂአይ ኢትዮጵያ ስራ አስፈጻሚ ኤርቬ ሚላድ መግለጫ ሰጥተዋል፡፡ ስራ አስፈጻሚው መግለጫ ከሰጡባቸው ጉዳዮች መካከል የድርጅቱ አዲስ እቅዶች፣ ዋና ቢሮውን ወደ ሰበታ ስለማዞሩ እና ማይጨው፣ ለፐርፐዝ ብላክ ኢትዮጵያ ስለተሸጠው ዋና መስሪያ ቤት ቦታ፣ ትርፍ እና ሌሎችም ጉዳዮች ዋነኞቹ ናቸው፡፡ ኤርቬ ሚላድ በመግለጫቸው ቢጂአይ ከዚህ ቀደም እራሳቸዉን ችለዉ አክሲዮን ማህበር ተብለዉ ሲጠሩ የነበሩት ኩባንያዎች ወደ ቢጂአይ ይዋሃዳሉ ብለዋል፡፡ ድርጅቱ በቀጣዮቹ አምስት ዓመታት ውስጥ የቢራ ምርቱን አሁን ካለበት 5 ሚሊዮን ሄክቶሊትር ወደ 10 ሚሊዮን ሄክቶ ሊትር ማሳደግ የሚያስችሉ የምርት መሻሻያ ስራዎችን እንደሚሰራም ስራ አስፈጻሚው ተናግረዋል፡፡ ከሚሰሩት ስራዎች መካከልም የቢራ ፋብሪካዎችን ምርታማነትን ማሳደግ፣ አዳዲስ ደንበኞችን እና…
Read More
የአፍሪካ ልማት ባንክ የኢትዮጵያ ቢሮውን ሊዘጋ እንደሚችል አስጠነቀቀ

የአፍሪካ ልማት ባንክ የኢትዮጵያ ቢሮውን ሊዘጋ እንደሚችል አስጠነቀቀ

የአፍሪካ ልማት ባንክ ከአንድ ወር በፊት በአዲስ አበባ ያሉ ሁለት የባንኩ ሰራተኞች በኢትዮጵያ የጸጥታ ሀይሎች ድብደባ፣ እስር እና እንግልት እንደደረሰባቸው አስታውቆ ነበር። ባንኩ እንዳለው ሁለት ሰራተኞቹ የቬና የዲልሎማሲ ጥበቃ ስምምነትን እና የአፍሪካ ልማት ባንክ ቢሮ አስተናጋጅ ሀገራት ስምምነትን የጣሰ ክስተት በኢትዮጵያ መፈጸሙንም ገልጿል። የተፈጠረውን ክስተት ለኢትዮጵያ መንግሥት በይፋ ማመልከቱን የሚገልጸው የአፍሪካ ልማት ባንክ ጉዳዩ መፈጸም እንደሌለበት፣ ህግ መጣሱን እና ጉዳዩ ተመርምሮ እርምጃ እንደሚወሰድ በኢትዮጵያ በኩል ቃል ተገብቶልኛል ሲልም በወቅቱ አስታውቆ ነበር፡፡ ባንኩ አሁን ላይ በጉዳዩ ዙሪያ ባወጣው መግለጫ የኢትዮጵያ መንግስት ቃል በገባው መሰረት በአጥፊዎች ላይ እርምጃ እንዳልወሰደ እና ጉዳዩን ስለመመርመሩ መረጃ እንዳልሰጠው ገልጿል፡፡ ይህን ተከትሎም ባንኩ የኢትዮጵያ ቢሮውን ሊዘጋ እና…
Read More
ኢትዮጵያ ከአይኤምኤፍ 3 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ለመበደር እየተነጋገረች መሆኑ ተገለጸ

ኢትዮጵያ ከአይኤምኤፍ 3 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ለመበደር እየተነጋገረች መሆኑ ተገለጸ

ኢትዮጵያ በማካሄድ ላይ ላለችው የኢኮኖሚ ሪፎርም እና ችግር ላይ የሚገኘውን የፋይናንስ ሁኔታዋን ለመቅረፍ ያግዛት ዘንድ ከአለም አቀፉ ገንዘብ ድርጅት (አይ ኤም ኤፍ) 3 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ለመበደር እየተነጋገረች መሆኑን ሮይተርስ ዘግቧል። በሀገሪቱ የሚታየውን አመታዊ የበጀት ጉድለቷን ለሞሙላት ያግዛት ዘንድ በልዩ ሁኔታ ከአይኤም ኤፍ ብድር መጠየቋን ዘገባው አመላክቷል። የመንግሥት ባለስለጣናት  ባለፈው ሳምንት ከአለም አቀፍ ቦንድ ገዢዎች ጋር በነበራቸው ስብሰባ በቀጣዩ የፈረንጆች አመት 2024 መጀመሪያ ሶስት ወራት ከአይ ኤም ኤፍ ጋር የብድር ስምምነት ላይ እደርሳለን ብለው እንድደሚያምኑ ተናግረዋል። ሀገሪቱ ያለት የገቢ ንግድ ማስኬጃ የውጭ ምንዛሬ መጠን ክምችት ዜሮ ነጥብ ሁለት በመቶ ብቻ እንደሆነ በዘገባው ላይ ተጠቅሷል። ኢትዮጵያ የገጠማትን የበጀት ጉድለት ለመሙላት…
Read More
የቻምፒየንስ ሊግ ጥሎ ማለፍ ጨዋታዎች ድልድል ይፋ ሆነ

የቻምፒየንስ ሊግ ጥሎ ማለፍ ጨዋታዎች ድልድል ይፋ ሆነ

ሀያላን የአውሮፓ እግር ኳስ ክለቦች የሚፋለሙበት ተወዳጁ የአውሮፓ ቻምፒዮንስ ሊግ ውድድር ቀጣይ ጨዋታዎች ድልድል ተካሂዷል፡፡ የዓምናው የቻምፒዮንስ ሊግ አሸናፊው የእንግሊዙ ማንችስተር ሲቲ ከዴንማርኩ ኮፐንሀገን ጋር ተደልድሏል፡፡ እንዲሁም ምድቡን በበላይነት ያጠኛቀቀው አርሰናል ከፖርቹጋሉ ፖርቶ ጋር ሲደለደል ናፖሊ ከባርሴሎና፣ ፒኤስጂ ከሪያል ሶሴዳድ፣ የአምናው የፍጻሜ ተፋላሚ ኢንተር ሚላን ከአትሌቲኮ ማድሪድ፣ ፒኤስቪ ከቦሩሲያ ዶርትሙንድ፣ ላዚዮ ከባየር ሙኒክ እንዲሁም ላይፕዝሽ ከሪያል ማድሪድ እንደሚጫወቱ ተገልጿል፡፡ ናፖሊ ከባርሴሎና፣ ላይፕዝሽ ከሪያል ማድሪድ እና ኢንተር ሚላን ከአትሌቲኮ ማድሪድ የሚያደርጓቸው ጨዋታዎች ከባድ ፉክክር ሊደረግባቸው የሚችሉ ጨዋታዎች እንደሚሆኑ ተጠብቋል፡፡ አራት የስፔን ክለቦች ወደ 16 ውስጥ በመግባት የቻምፒዮንስ ሊግ ውድድር ያለፉ ሲሆን ጣልያን ሶስት እንግሊዝ እና ጀርመን ሁለት ሁለት ክለቦቻቸው ይሳተፋሉ፡፡ የ2022/23…
Read More
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ብራዛቪል በረራ የጀመረበትን 40ኛ ዓመት አከበረ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ብራዛቪል በረራ የጀመረበትን 40ኛ ዓመት አከበረ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ኮንጎ ዋና ከተማ ብራዛቪል የቀጥታ በረራ የጀመረበትን ዓመት አክብሯል፡፡ በአፍሪካ ከተመሰረተ ረጅም ዓመት ያስቆጠረው የኢትዮጵያ አየር መንገድ በፈረንጆቹ 1983 ላይ የመጀመሪያውን የቀጥታ በረራ ወደ ብራዛቪል አድርጎ ነበር፡፡ አሁን ላይ አየር መንገዱ በሳምንት 10 በረራዎችን ከአዲስ አበባ-ብራዛቪል የደርሶ መልስ በማድረግ ላይ ይገኛል፡፡ የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአፍሪካ ከ63 በላይ ከተሞች በመብረር ላይ ሲሆን ይህም ከየትኛውም የዓለማችን አየር መንገዶች በላይ በአፍሪካ ሰማይ ላይ የሚበር አየር መንገድ አድርጎታል፡፡ በታህሳስ 1945 የተመሰረተው የኢትዮጵያ አየር መንገድ የመጀመሪያ በረራውን ወደ ግብጽ ካይሮ አድርጓል፡፡ የአየር መንገዱ ስራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን ጣሰው በዱባዩ ኤርሾው ላይ ተገኝተው እንዳሉት አየር መንገዱ ከቦይንግ እና ኤርባስ 78 አውሮፕላኖችን ለመግዛት…
Read More