ዜና

አሜሪካ እና የአፍሪካ ሕብረት የሶማሊያ ሉዓላዊነት እንዲከበር ጠየቁ።

አሜሪካ እና የአፍሪካ ሕብረት የሶማሊያ ሉዓላዊነት እንዲከበር ጠየቁ።

ኢትዮጵያ ከአራት ቀናት ከራስ ገዟ ሶማሊላንድ ጋር ያደረገችው ስምምነት በምስራቅ አፍሪካ አዲስ ትኩሳት እንዲፈጠር ምክንያት የሆነ ሲሆን ሀገራት በጉዳዩ ዙሪያ ምላሽ በመስጠት ላይ ናቸው፡፡ ሱማሊላንድ አንድ አካሌ ናት የምትለው ሶማሊያ ስምምነቱን እንደ ወረራ እንደምትመለከተው ገልጻ ተመድ፣ አፍሪካ ህብረት ፣ የአረብ ሊግ እና ሀገራት ከጎኗ እንዲቆሙ ጥሪ አቅርባለች፡፡ አሜሪካ በጉዳዩ ዙሪያ ምላሽ የሰጠች ሲሆን ለሶማሊላንድ የሀገርነት እውቅና መስጠት ስህተት እንደሆነ ገልጻለች። የአሜሪካ ስቴት ዲፓርትመንት ቃል አቀባይ ማቲው ሚለር እንዳሉት "የሶማሊያን ሉዓላዊነት ከማክበር ባለፈ እውቅና ትሰጣለች፣ በአፍሪካ ቀንድ የተፈጠረው አዲስ ውዝግብም ያሳስበናል" ብለዋል። "ሁሉም አካላት ጉዳዩን ከማካረር ሊቆጠቡ ይገባል" ያሉት ቃል አቀባዩ "አለመግባባቱን በዲፕሎማሲያዊ ድርድር ሊፈቱ ይገባል" ሲሉም አሳስበዋል። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን…
Read More
የኢትዮጵያ እና ሶማሊላንድ ስምምነት በምስራቅ አፍሪካ አዲስ የዲፕሎማሲ ፍትጊያ መፍጠሩ ተገለጸ

የኢትዮጵያ እና ሶማሊላንድ ስምምነት በምስራቅ አፍሪካ አዲስ የዲፕሎማሲ ፍትጊያ መፍጠሩ ተገለጸ

በቀይ ባህር ላይ ወደብ እንደሚያስፈልጋት ስትገልጽ የቆየችው ኢትዮጵያ ከራስ ገዟ ሶማሊላንድ ወደብ በሊዝ መግዛቷን ማስታወቋ ይታወሳል፡፡ የሁለቱ አካላት የመግባቢያ ስምምነት ኢትዮጵያ በበርበራ ወደብ 20 ኪሎ ሜትር ላይ ወደብ እና ወታደራዊ ቤዝ እንዲኖራት የሚፈቅድ ሲሆን በአንጻሩ ደግሞ ኢትዮጵያ ለሶማሊላንድ የሀገርነት እውቅና እንድትሰጥ ይጠቅሳል፡፡ ከዚህ በተጨማሪም ሶማሊላንድ ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ላይ የ20 በመቶ ድርሻ እንዲኖራት ይደረጋል የተባለ ሲሆን በአንድ ወር ውስጥ ተጨማሪ ድርድሮች እንደሚካሄዱ ተገልጿል፡፡ ይህን ተከትሎም ሶማሊያ የኢትዮጵያን እና የግዛቴ አካል ናት የምትላት ሶማሊላንድ ያደረጉት ስምምነት ሉዓላዊነቴን የሚጥስ ዓለም አቀፍ ህግንም የሚጥስ እንደሆነ አስታውቃለች፡፡ ኢትዮጵያ እና ሶማሊላንድ ያደረጉት ስምምነት ሶማሊያ አልሻባብን ለማጥፋት የጀመረችውን ዘመቻ እንደሚያስተጓጉል እና የሽብር ቡድኑ ዳግም እንዲያንሰራራ እንደሚያደርግም…
Read More
ላለፉት ሶስት ዓመት የትጥቅ ትግል ሲያካሂድ የነበረው የአገው ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ የሰላም ስምምነት ፈረመ

ላለፉት ሶስት ዓመት የትጥቅ ትግል ሲያካሂድ የነበረው የአገው ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ የሰላም ስምምነት ፈረመ

ላለፉት ሶስት ዓመት የትጥቅ ትግል ሲያካሂድ የነበረው የአገው ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ ከአማራ ክልል አስተዳድር ጋር የሰላም ስምምነት ተፈራረመ የሰላም ስምምነቱን ተከትሎ የንቅናቄው አመራሮች በተለያዩ የአመራር ቦታዎች ላይ ሹመት እንደሚሰጣቸው ተገልጿል፡፡ የአገው ዴሞክራሲ ንቅናቄ (አዴን) የጥቅምት 2013ቱን የሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት ተከትሎ በአማራ ክልል ዋግኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር በተለይም በአበርገሌና ፃግብጂ ወረዳዎች ትጥቅ ትግል ሲያካሄድ ቆይቷል፡፡ ታጣቂ ኃይሉ በሁለቱ ወረዳዎች ቆላማ አካባቢዎች እስከ 19 የሚሆኑ ቀበሌዎችን ሲቆጣጠር እንደነበረም ንቅናቄውና የመንግስት አካላት አመልክተዋል፡፡ የአገው ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ የመንግሰትን የሰላም ጥሪ ተቀብሎ ታህሳስ 13 ቀን 2016 ዓ ም በአዲስ አበባ ከተማ ከአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ጋር የሰላም ስምምነት ማድረጉንና ትናንት ደግሞ በዋግኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ማዕከል ሰቆጣ ከተማ…
Read More
ኢትዮጵያ ከሶማሌላንድ ወደብ በሊዝ መግዛቷን ገለጸች

ኢትዮጵያ ከሶማሌላንድ ወደብ በሊዝ መግዛቷን ገለጸች

በቀይ ባህር ላይ ወደብ እንደሚያስፈልጋት ስትገልጽ የቆየችው ኢትዮጵያ ከራስ ገዟ ሶማሊላንድ ወደብ በሊዝ መግዛቷን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት አስታውቋል፡፡ እንደ ጽህፈት ቤቱ መግለጫ ከሆነ የባህር በር የምታገኝበትን የመግባቢያ ስምምነት ከሶማሌ ላንድ ጋር ተፈራርማለች፡፡ የባህር በር ሊዝ ስምምነቱን ጠቅላይ ሚኒስትር  ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና የሶማሌ ላንድ ፕሬዝዳንት ሙሴ ቢሂ አብዲ እንደተፈራረሙ ተገልጿል። የኢትዮጵያ እና ራስ ገዟ ሶማሊላንድ ስምምነት ኢትዮጵያ የቀይ ባህር በር እንዲኖራት ለያዘችው ጥረት ጥሩ መደላደል ሊፈጥር ይችላልም ተብሏል፡፡ ይሁንና የባህር በር ሊዝ ስምምነቱ ለምን ያህል ጊዜ፣ በምን ያህል ገንዘብ እና የስምምነቱ ዝርዝር መረጃ እስካሁን በማንኛውም ወገን ይፋ አልተደረገም፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ (ዶ/ር) ከወራት በፊት ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት…
Read More
ኢትዮጵያ በሕገ- ወጥ እንስሳት ንግድ ምክንት በየወሩ 17 ሚሊዮን ዶላር እያጣች ነው ተባለ

ኢትዮጵያ በሕገ- ወጥ እንስሳት ንግድ ምክንት በየወሩ 17 ሚሊዮን ዶላር እያጣች ነው ተባለ

ኢትዮጵያ በቀን ከ1 ሺህ 200 በላይ የቁም እንስሳት በሕገ-ወጥ መንገድ ከአገር በመውጣታቸው በየቀኑ ከ630 ሺህ ዶላር በላይ እንደምታጣ ተገልጿል። በሕገ-ወጥ መንገድ ወደ አገር ውስጥ ገብተው ለአገልግሎት የሚወሉ መድኃኒቶችም የጥራት ደረጃቸውን ያልጠበቁ በመሆናቸው በጤና ሥርዓቱ ላይ ጫና እያሳደሩ መሆኑም ተገልጿል። በኢትዮጵያ የንግድና ዘርፍ ማኅበራት ምክር ቤት አዘጋጅነት ሕገ-ወጥ ንግድን መከላከል ላይ ያተኮረ አገር አቀፍ ጉባዔ በአዲስ አበባ ዛሬ ተካሂዷል። ምክር ቤቱ ሕገ-ወጥ ንግድ በስፋት በሚታይባቸው ዘርፎች ላይ ያካሄዳቸውን ጥናቶች ይፋ አድርጓል። ጥናቶቹ በቁም እንስሳት፣ በመድኃኒት፣ በጨርቃጨርቅ፣ በሎጂስቲክስ ሥርዓት ሕገ-ወጥ እንቅስቃሴዎችና ንግድን በተመለከቱ የሕግ ማዕቀፎች ላይ የተካሄዱ ናቸው። አሁን ላይ የቁም እንስሳትና የመድኃኒት ሕገ-ወጥ ንግድ አሳሳቢ ደረጃ ላይ መድረሱ በጥናቱ ተመላክቷል። በኢንዱስትሪ…
Read More
በአማራ ክልል የሚገኙ ዩንቨርሲቲዎች ከጥር አንድ ጀምሮ ተማሪዎቻቸውን ሊጠሩ ነው

በአማራ ክልል የሚገኙ ዩንቨርሲቲዎች ከጥር አንድ ጀምሮ ተማሪዎቻቸውን ሊጠሩ ነው

ትምህርት ሚኒስቴር ባወጣው መግለጫ በአማራ ክልል የሚገኙ የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች ከጥር 1 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ ባሉት ሁለት ሳምንታት ውስጥ ትምህርት ይጀምራሉ ብሏል፡፡ ሚኒስቴሩ አክሎም በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ክልል በተፈጠረው ወቅታዊ የጸጥታ ችግር ምክንያት በክልሉ የሚገኙ ዩኒቨርስቲዎች በ2016 የትምህርት ዘመን የመጀመሪያዉ ወሰነ-ትምህርት ተማሪዎቻቸውን ለመጥራትና መደበኛ የመማር ማስተማር ስራቸዉን ሙሉ ለሙሉ ለመጀመር አልቻሉም ነበር። በመሆኑም የትምህርት ሚኒስቴር ከክልሉ ኮማንድፖስት፣ የጸጥታ አደረጃጀቶችና የሚመለከታቸዉ አካላት ጋር ተከታታይ ውይይቶችን ሲያካሂድ መቆየቱን ገልጿል። የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ፣ የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አረጋ ከበደ ፣ የአስሩ ዩኒቨርስቲዎች ፕሬዝዳንቶችና ጉዳዩ የሚመለከታቸው የክልሉ ጸጥታ አካላት ታህሳስ 18 ቀን 2016 ዓ.ም  በጉዳዩ ዙሪያ መክረዋልም ተብሏል፡፡ ሚኒስቴሩ በመግለጫው…
Read More
አንድ ሺህ ጥንድ ተጋቢ ሙሽሮች በአንድ ቀን በአንድ ቦታ ሊሞሸሩ ነው

አንድ ሺህ ጥንድ ተጋቢ ሙሽሮች በአንድ ቀን በአንድ ቦታ ሊሞሸሩ ነው

ያሜንት ኢቬንትስ ጥንዶችን ለመሞሸር የያዘውን ፕሮጀከት አላማ ለማሳወቅ እና ከባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ጋር በቀጣይ አብሮ በትብብር ለመስራት የጋራ መግባቢያ ሰነድ ተፈራርሟል፡፡ ያሜንት ኢቭንትስ በዚህ ጊዜ እንዳለው "ቤተሰብን መመስረት ሀገርን መገንባት ነው" በሚል መርህ ጥር 5  ቀን 2016  ዓ.ም አንድ ሺህ ጥንድ ተጋቢዎችን በአዲስ አበባ ሚሊኒየም አዳራሽ ጋብቻ እንዲመሰርቱ የሰርግ ሁነት አዘጋጅቷል። በባህልና ስፖርት ሚኒስቴርና በያሜንት ኢቬንትስ መካከል ዛሬ የተፈረመው የጋራ መግባቢያ ስምምነት ሰነድ የየሺህ ጋብቻ እንደ ሀገር አቀፍ የቤተሰብ ፕሮጀክት እንዲዘልቅ በማድረግ ከቤተሰብ አመሰራረት ጋር የሚገጥሙ ችግሮችን ለማቃለል አላማው ያደረገ ነው፡፡ እንዲሁም ይህ የጋራ ጋብቻ ሁነት አመታዊ ካርኒቫል የህዝብ ለህዝብ ትስስርንና መተማመንን ከማጠናከር ባሻገር ኢትዮጵያ የምትታወቅበትን ጎብኚዎችን እንዲስብ ለማድረግ መታሰቡም…
Read More
ዳሸን ባንክ እና የኢትዮጵያ አየር መንገድ የጉዞ ቲኬት በብድር መሸጥ ጀመሩ

ዳሸን ባንክ እና የኢትዮጵያ አየር መንገድ የጉዞ ቲኬት በብድር መሸጥ ጀመሩ

ዳሸን ባንክ እና የኢትዮጵያ አየር መንገድ ደንበኞች የአየር ትራንስፖርት አገልግሎት ተጠቅመው ክፍያውን ቆይተው የሚከፍሉበትን አዲስ የክፍያ አማራጭ በጋራ አስተዋውቀዋል። አቶ ዮሃንስ ሚሊዮን የዳሽን ባንክ ዲጂታል ባንኪንግ ዋና መኮንን “ጉዞዎ ይቀድማል ክፍያው ይደርሳል” በሚል የተሰየመው ይህ አገልግሎት በደንበኞች ምርጫ መሰረት በ6 ወር ወይም በ12 ወር የብድር ክፍያ የሚሰጥ መሆኑን አመልክተዋል። ደንበኞች የአገልግሎቱ ተጠቃሚ ለመሆን በዳሸን ባንክ የሂሳብ ቁጥር መክፈት እንደሚገባቸው እና በተጨማሪም በባንኩ ቢያንስ ለሶስት ወራት አገልግሎት ያገኙ መሆን እንደሚኖርባቸውም ጠቁመዋል።  አቶ ዮሃንስ አክለውም አገልግሎቱን ለማግኘት ደንበኞች አቅራቢያቸው ወደሚገኝ የዳሸን ባንክ ቅርንጫፍ በሚያመሩበት ወቅት አስፈላጊ ሰነዶችን ማሟላት የሚገባቸው ሲሆን ማስያዣም ማቅረብ እንደሚጠበቅባቸውም ገልፀዋል። ስምምነቱን አስመልክቶ የኢትዮጵያ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና…
Read More
አሜሪካ፣ ካናዳ እና ብሪታንያ ኢትዮጵያ የቬና ዲፕሎማቲክ ስምምነት መጣሷ እንዳሳሰባቸው ገለጹ

አሜሪካ፣ ካናዳ እና ብሪታንያ ኢትዮጵያ የቬና ዲፕሎማቲክ ስምምነት መጣሷ እንዳሳሰባቸው ገለጹ

የአፍሪካ ልማት ባንክ ከአንድ ወር በፊት በአዲስ አበባ ያሉ ሁለት የባንኩ ሰራተኞች በኢትዮጵያ የጸጥታ ሀይሎች ድብደባ፣ እስር እና እንግልት እንደደረሰባቸው አስታውቆ ነበር። ባንኩ እንዳለው ሁለት ሰራተኞቹ የቬና የዲልሎማሲ ጥበቃ ስምምነትን እና የአፍሪካ ልማት ባንክ ቢሮ አስተናጋጅ ሀገራት ስምምነትን የጣሰ ክስተት በኢትዮጵያ መፈጸሙንም ገልጿል። የተፈጠረውን ክስተት ለኢትዮጵያ መንግሥት በይፋ ማመልከቱን የሚገልጸው የአፍሪካ ልማት ባንክ ጉዳዩ መፈጸም እንደሌለበት፣ ህግ መጣሱን እና ጉዳዩ ተመርምሮ እርምጃ እንደሚወሰድ በኢትዮጵያ በኩል ቃል ተገብቶልኛል ሲልም በወቅቱ አስታውቆ ነበር፡፡ ባንኩ አሁን ላይ በጉዳዩ ዙሪያ ባወጣው መግለጫ የኢትዮጵያ መንግስት ቃል በገባው መሰረት በአጥፊዎች ላይ እርምጃ እንዳልወሰደ እና ጉዳዩን ስለመመርመሩ መረጃ እንዳልሰጠው ገልጿል፡፡ የአሜሪካ፣ ካናዳ እና ብሪታኒያ በጉዳዩ ዙሪያ ባወጡት…
Read More
በአማራ ክልል ከሁለት ሚሊዮን በላይ ተማሪዎች ከትምህርት ገበታ ውጪ መሆናቸው ተገለጸ

በአማራ ክልል ከሁለት ሚሊዮን በላይ ተማሪዎች ከትምህርት ገበታ ውጪ መሆናቸው ተገለጸ

በአማራ ክልል ባለው የጸጥታ ችግር ምክንያት ከሁለት ሚሊዮን በላይ ተማሪዎች ከትምህርት ገበታ ውጪ መሆናቸውን የክልሉ ትምህርት ቢሮ ገለጸ። የቢሮው የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ጌታቸው ቢያዝን በክልሉ ያለው የጸጥታ ችግር በተማሪዎች ምዝገባ ሥራ ላይ ከፍተኛ ጫና አሳድሯል ብለዋል። ክልሉ 6.2 ሚሊዮን ተማሪዎችን መዝግቦ ማስተማር ሲገባው ያን ማድረግ አለመቻሉን ኃላፊው ተናግረዋል። ከሁለት ሚሊዮን በላይ ያልተመዘገቡ ተማሪዎች መኖራቸውን የገለፁት ኃላፊው ፤ መማር የሚገባቸው ተማሪዎች የትምህርት ዕድል እንዳያገኙ መደረጉን አመልክተዋል። በጸጥታው ችግር ምክንያት ሁለት ሺህ በሚጠጉ ትምህርት ቤቶች የሚያስተምሩ መምህራን ከመማር ማስተማር ሥራ ውጪ መሆናቸውን ገልፀዋል። ይሁን እንጂ መምህራኑ ወደ ሥራቸው እንዲመለሱ የማድረግ ሥራ እየተሠራ ይገኛል ብለዋል። በክልሉ ባለው ግጭት "ወደ 42 ትምህርት ቤቶች…
Read More