Universities

የሶስት ዩንቨርሲቲ ፕሬዝዳንቶች ከስልጣን ተነሱ

የሶስት ዩንቨርሲቲ ፕሬዝዳንቶች ከስልጣን ተነሱ

ትምህርት ሚኒስቴር ከገንዘብ ብክነት ጋር በተያያዘ የሶስት ዩንቨርሲቲዎችን ፕሬዝዳንት ከሀላፊነት አንስቷል፡፡ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የበጀትና የፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የገንዘብ ሚኒስቴርን የዘጠኝ ወራት ዕቅድ አፈጻጸም በገመገመበት ወቅት እንደተገለፀው ዩንቨርሲቲዎች የበጀት ብክነት ፈጽመዋል ተብሏል። የወላይታ ሶዶ፣ የጋምቤላ እና ሚዛን-ቴፒ ዩኒቨርሲቲፕሬዝዳንቶች በኦዲት ግኝት ከኃላፊነታቸው እንደተነሱ ትምህርት ሚኒስቴር ከህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጋር ባደረገው የስራ ግምገማ ወቅት አስታውቋል፡፡ለአዲስ አበባ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ፣ ደብረብርሃን ዩኒቨርስቲ እና ሌሎች አራት ዩኒቨርሲቲዎች ደግሞ ከባድ የጽሑፍ ማስጠንቀቂያ ተሰጥቷቸዋል። በፌዴራል ዋና ኦዲተር መ/ቤት በተሠራው የተቋማት ኦዲት ሪፖርት የ2014 በጀት ዓመት ተቀባይነት የሚያሳጣ አስተያየት ከተሰጣቸው 24 መሥሪያ ቤቶች ውስጥ 13 ተቋማት ላይ አስተደደራዊ ዕርምጃ መወሰዱን ሚኒስትሩ አህመድ ሽዴ…
Read More
በአማራ ክልል የሚገኙ 10 ዩንቨርሲቲዎች በጦርነት ምክንያት ተማሪዎቻቸውን መጥራት አልቻሉም

በአማራ ክልል የሚገኙ 10 ዩንቨርሲቲዎች በጦርነት ምክንያት ተማሪዎቻቸውን መጥራት አልቻሉም

አማራ ክልል የሚገኙ አስር ዩኒቨርሲቲዎች በክልሉ ባለው የፀጥታ ችግር ምክንያት ለነባር እንዲሁም አዲስ ለተመደቡ ተማሪዎቻቸው ጥሪ ሳያደርጉ ወራት መቆጠሩ ይታወቃል፡፡ ከአማራ ክልል ውጪ የሚገኙ ዩንቨርስቲዎች ተማሪዎቻቸውን ጠርተው በማስተማር ላይ ሲሆኑ በአማራ ክልል ባሉ ዩንቨርስቲዎች የተመደቡ ተማሪዎች ግን እስካሁን አልተጠሩም። ይህንን ተከትሎም ተማሪዎቹ ለስነልቦና እና ለተለያዩ ችግሮች መጋለጣቸውን በተደጋጋሚ በማንሳት ላይ ሲሆኑ ዩኒቨርሲቲዎቹ ጥሪ ሳያደርጉ አራት ወራት በማለፉ ተስፋ መቁረጥ ውስጥ መግባታቸውንም ይጠቁማሉ፡፡ "ያለ ትምህርት ቁጭ ብለን ወራት አልፈዋል፣ ፍትህ እንሻለን" የሚሉት ተማሪዎቹ፤ ወደ ሌሎች የትምህርት ተቋማት በጊዚያዊነት መዘዋወርን ጨምሮ አማራጭ መፍትሔዎች እንዲፈለግላቸው ጠይቀዋል፡፡ የትምህርት ሚኒስቴር በበኩሉ በአማራ ክልል ያሉ ዩንቨርሲቲዎች በቅርቡ ለተማሪዎቻቸው ጥሪ እንዲያስተላልፉ መግባባት ላይ መደረሱን አስታውቋል፡፡ በትምህርት ሚኒስቴር…
Read More