ኢኮኖሚ

በኢትዮጵያ ግዙፉ የድንጋይ ከሰል ማጣሪያ ፋብሪካ በቅርቡ ሥራ ይጀምራል ተባለ

በኢትዮጵያ ግዙፉ የድንጋይ ከሰል ማጣሪያ ፋብሪካ በቅርቡ ሥራ ይጀምራል ተባለ

በደቡብ ኢትዮጵያ ዳውሮ ዞን ታርጫ ከተማ በ5 ነጥብ 2 ቢሊዮን ብር እየተገነባ የሚገኘው የድንጋይ ከሰል ማምረቻ ፋብሪካ ከሁለት ወራት ባነሰ ጊዜ ውስጥ ሥራ እንደሚጀምር ተገልጿል። የከሰል ማዕድን አምራቹ ኢቲ ማይኒንግ ፋብሪካ እንደሚሰኝ ሲገለፅ ፋብሪካው 150 ቶን ከሰል በሰዓት የማምረት አቅምና የሲሚንቶ ፋብሪካዎችን 75 በመቶ የድንጋይ ከሰል ፍላጎት ለማሟላት ያስችላል ተብሏል። የፋብሪካው ፕሮጀክት ማናጀር ኢንጅነር በላይ አሰፋ የኢትዮጵያ የታጠበ ከሰል ፍላጎት ሀገሪቱ በዓመቱ በአማካይ 400 ሚሊዮን ዶላር እያሳጣት መሆኑን ገልፀዋል። ይህ ፋብሪካ ከሁለት ዓመት በፊት ተጀምሮ በአሁኑ ጊዜ አጠቃላይ ሥራው እየተጠናቀቀ በመሆኑ በፋብሪካው የሚሠሩ ቋሚ ሠራተኞች ሥልጠና እየተሰጠና የሙከራ ሥራዎች ከተሠሩ በኋላ ከሁለት ወራት ባነሰ ጊዜ ውስጥ ተመርቆ ሥራ ይጀምራል ተብሏል።…
Read More
ስታንዳርድ ባንክ በኢትዮጵያ መሰማራት እንደሚፈልግ ገለጸ

ስታንዳርድ ባንክ በኢትዮጵያ መሰማራት እንደሚፈልግ ገለጸ

ዋና መቀመጫውን በደቡብ አፍሪካ ያደረገው ስታንዳርድ ባንክ በአፍሪካ ትልቁን ያልተነካ ገበያ እየፈለገ በሚገኝበት በዚህ ጊዜ በኢትዮጵያ የኢንቨስትመንት የባንክ ፍቃድ እንደሚጠይቅ አስታውቋል። የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለስልጣን ከሁለት ሳምንት በኃላ የኢንቨስትመንት የባንክ ፍቃድ ማመልከቻዎችን እንደሚቀበል ከቀናት በፊት መግለፁ አይዘነጋም ። ለዉጪ ፋይናንስ ተቋማት በኢትዮጵያ የኢንቨስትመንት ባንኮች ሆነው እንዲመዘገቡ የቀረበውን ጥሪ ተቀብሎ ፍቃደኝነቱን በማሳየት "ስታንደርድ ባንክ" ከቀዳሚዎቹ ተርታ መሰለፍ ችሏል። በኢትዮጵያ የኢንቨስትመንት ባንክ ፍቃድ ለማግኘት ዝቅተኛው የተከፈለ ካፒታል ለዉጪ ባንኮች 100 ሚሊዮን ብር እና ከባንክ ላልሆኑ የፋይናንስ ተቋማት 25 ሚሊዮን ብር ሀብት ሊኖራቸው ይገባል። ኢትዮጵያ በሚቀጥሉት አምስት ዓመታት በባንክ ዘርፍ ለመሰማራት ፍላጎት ላላቸው የውጭ ባለሀብቶች አምስት የሚደርሱ የባንክ ፈቃድ ለመስጠት ማቀዷን ባሳለፍነው ግንቦት…
Read More
ኢትዮጵያ በነዳጅ የሚሰሩ ተሽከርካሪዎች ወደ ሀገር ውስጥ እንዳይገቡ ልትከለክል መሆኗን ገለጸች

ኢትዮጵያ በነዳጅ የሚሰሩ ተሽከርካሪዎች ወደ ሀገር ውስጥ እንዳይገቡ ልትከለክል መሆኗን ገለጸች

የትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ ሚኒስትር የስድስት ወራት ሪፖርቱን ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አቅርቧል፡፡ ሚኒስትሩ አቶ አለሙ ስሜ በዚህ ጊዜ እንዳሉት በነዳጅ የሚሰሩ ተሽከርካሪዎች ወደ ሀገር እንዳይገቡ የሚደረገው ክልከላ ሙሉ ለሙሉ ተፈፃሚ እንደሚደረግ ተናግረዋል፡፡ የትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ ሚኒስትሩ አቶ ዓለሙ ስሜ (ዶ/ር) ለፓርላማው እንደተናገሩት፥ ነዳጅ የሚወስዱ ተሽከርካሪዎችን ለግል ጥቅማጥቅ ሆነ ለሌላ አላማ ወደ ሀገር ውስጥ እንዳይገቡ የሚደረገውን እገዳ በጥብቅ እንደሚያስፈጽሙ ገልጸዋል። ውሳኔው ከአየር ንብረት ለውጥ ጋር ተያይዞ ለሚነሱ ስጋቶች እና ከባህላዊ የነዳጅ ፍጆታ ጋር ተያይዞ እየጨመረ ለሚመጣው ወጭ ስልታዊ ምላሽ ነውም ተብሏል። እየጨመረ የመጣው የነዳጅ ወጪ ፖሊሲ አውጪዎች አገሪቱ በተለመዱት ተሽከርካሪዎች ላይ ያላትን ጥገኝነት እንዲገመግሙ እና የካርበን በካይ ጋዝ መጠንን ለመቀነስ ከሚደረገው…
Read More
በታሸገ ውሃ ምርቶች ላይ የዋጋ ጭማሪ ሊደረግ ነው

በታሸገ ውሃ ምርቶች ላይ የዋጋ ጭማሪ ሊደረግ ነው

የታሸገ ውሃ አምራቾች በሦስት ወር ውስጥ ለሁለተኛ ጊዜ የዋጋ ጭማሪ ሊያደርጉ መሆኑን አስታውቀዋል፡፡ የታሸገ ውሃ አምራቾች ከቀጣዩ ሳምንት ጀምሮ ተግባራዊ የሚደረግ የዋጋ ጭማሪ ሊያደርጉ መወሰናቸውን ገልጸዋል። አዲስ በሚጠበቀው የታሸገ ውሃ የማከፋፈያ ዋጋ ጭማሪ በሁለት ሊትር ውሃ ላይ እስከ 20 በመቶ ይደረጋል የተባለ ሲሆን ይህም በሶት ወራት ውስጥ ለሁለተኛ ጊዜ ነው። የውሃ አምራቾቹ በኅዳር ወር በተመሳሳይ የ22.5 በመቶ ጭማሪ አድርገው የነበረ ሲሆን በወቅቱ ለዋጋ ማስተካከያው ምክንያት ነው የተባለው የነዳጅ ዋጋ ጭማሪ እና ሌሎች ግብአቶች ወጪያቸው ጨምሯል በሚል ነበር። በቀጣይ ሳምንት ተግባራዊ ይደረጋል የተባለው ጭማሪ ምክንያታዊነቱ ላይ ጥያቄ ያስነሳል የተባለ ሲሆን የዋጋ ጭማሪው በተጠቃሚዎች እና አከፋፋዮች ላይ እክል ሊፈጥር እንደሚችል ተገምቷል ሲል…
Read More
ኢትዮ ቴሌኮም ባለፉት ስድስት ወራት  11 ቢሊዮን ብር ትርፍ ማግኘቱን አስታወቀ

ኢትዮ ቴሌኮም ባለፉት ስድስት ወራት  11 ቢሊዮን ብር ትርፍ ማግኘቱን አስታወቀ

የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈጻሚ የሆኑት ወይዘሪት ፍሬህይወት የ2016 ዓ.ም የስድስት ወራት የስራ አፈጻጸም ሪፖርታቸውን አቅርበዋል፡፡ ተቋሙ በስድስት ወሩ በመላው ሀገሪቱ 232 አዳዲስ የሞባይል  ኔትወርክ ጣቢያዎች አገልግሎት መስጠት ጀምረዋል ብሏል። ኢትዮ ቴሌኮም ባለፉት ስድስት ወራት ውስጥ ተጨማሪ 1 ነጥብ 9 ሚሊዮን  አዲስ የሞባይል  ኔትወርክ ደንበኞችን ማስተናገድ የሚችል መሰረተ ልማት መገንባቱን የገለጸ ሲሆን የድርጅቱ አጠቃይ ደንበኞች ቁጥርም 81 ሚሊዮን እንደደረሱ ተገልጿል፡፡ እንዲሁም በግማሽ ዓመቱ ውስጥ በገጠራማ የሀገሪቱ አካባቢዎች 41 አዲስ የሞባይል ኔትወርክ አገልግሎት መስጠት የሚያስችሉ መሰረተ ልማቶች ተገንብተው ለአገልግሎት ክፍት ሆነዋልም ተብሏል፡፡ ኢትዮ ቴሌኮም በቴሌኮም ደንበኞች ብዛት ከአፍሪካ ሁለተኛው ተቋም ሲሆን ከሶስት ዓመት በፊት ወደ ኢትዮጵያ ለገባው ሳፋሪኮም የቴሌኮም ኩባንያ ጋር ብርቱ ፉክክር እያደረገ እንደሚገኝ ተገልጿል፡፡ ድርጅቱ ባለፉት…
Read More
በኢትዮጵያ በጦርነት ምክንያት 21 የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቶች መዘግየታቸው ተገለጸ

በኢትዮጵያ በጦርነት ምክንያት 21 የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቶች መዘግየታቸው ተገለጸ

የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ለመስራት ካቀዳቸዉ 54 የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቶች ዉስጥ 21 ያህሉን በጸጥታ ችግር መተግበር እንዳልቻለ አስታወቀ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር መሐመድ አብዱራህማን የ 2016 አመት ስድስት ወራት የስራ አፈጻጸም ሪፖርትን ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት  አቅርበዋል። አስተዳደሩ በወራቱ ለማከወን ካከቀዳቸዉ 54 ፕሮጀክቶች ዉስጥ 21 ያህሉን በጸጥታ ችግር መተግበር እንዳልቻለ ዋና ዳይሬክተሩ ለቋሚ ኮሚቴዉ ተናግረዋል። በዚህም በስድስቱ ወራት የነበረዉ የዲዛይን ስራዎች አፈጻጸም 57 በመቶ ሲሆን ይህም ዝቅተኛ እንዲሆን እንዳደረገበት ለምክር ቤቱ ገልጸዋል። በተጨማሪም በዉጭ አማካሪ ድርጅት ለተሰራ ስራ ክፍያ የዉጭ ምንዛሪ በመዘግየቱ የተጓተቱ ፕሮጀክቶች መኖራቸዉንም ዋና ዳይሬክተሩ አንስተዋል። በተለያዩ ምክኒያቶችም 84 ፕሮጀክቶች መቋረጣቸዉ እና ሙሉ በሙሉ የኮንትራት ዉላቸዉ መሰረዙንም…
Read More
የአፍሪካ ልማት ባንክ ከኢትዮጵያ ያስወጣቸውን ሰራተኞች እንደሚመልስ ገለጸ

የአፍሪካ ልማት ባንክ ከኢትዮጵያ ያስወጣቸውን ሰራተኞች እንደሚመልስ ገለጸ

የአፍሪካ ልማት ባንክ ከሁለት ወር በፊት በአዲስ አበባ ያሉ ሁለት የባንኩ ሰራተኞች በኢትዮጵያ የጸጥታ ሀይሎች ድብደባ፣ እስር እና እንግልት እንደደረሰባቸው አስታውቆ ነበር። ባንኩ እንዳለው ሁለት ሰራተኞቹ የቬና የዲልሎማሲ ጥበቃ ስምምነትን እና የአፍሪካ ልማት ባንክ ቢሮ አስተናጋጅ ሀገራት ስምምነትን የጣሰ ክስተት በኢትዮጵያ መፈጸሙንም ገልጿል። የተፈጠረውን ክስተት ለኢትዮጵያ መንግሥት በይፋ ማመልከቱን የሚገልጸው የአፍሪካ ልማት ባንክ ጉዳዩ መፈጸም እንደሌለበት፣ ህግ መጣሱን እና ጉዳዩ ተመርምሮ እርምጃ እንደሚወሰድ በኢትዮጵያ በኩል ቃል ተገብቶልኛል ሲልም በወቅቱ አስታውቆ ነበር፡፡ ባንኩ አሁን ላይ በጉዳዩ ዙሪያ ባወጣው መግለጫ የኢትዮጵያ መንግስት ቃል በገባው መሰረት በአጥፊዎች ላይ እርምጃ እንዳልወሰደ እና ጉዳዩ ስለመመርመሩ መረጃ እንዳልሰጠው ገልጿል፡፡ ይህን ተከትሎም ባንኩ የኢትዮጵያ ቢሮውን ሊዘጋ እና…
Read More
ሶማሊያ የኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላን በግዛቷ እንዳያርፍ ከለከለች፡፡

ሶማሊያ የኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላን በግዛቷ እንዳያርፍ ከለከለች፡፡

የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ እና በራስ ገዟ ሶማሊላንድ ፕሬዝደንት ሙሴ ቢሄ አብዲ ከሶስት ሳምንት በፊት በአዲስ አበባ የመግባቢያ ሰነድ መፈራረማቸው ይታወሳል። ስምምነቱ ኢትዮጵያ በኤደን ባህረ ሰላጤ 20 ኪሎሜትሮች የሚረዝም የባህር ጠረፍ እንድትከራይ እና በምትኩ ለሶማሊላንድ የሀገርነት እውቅና እንድትሰጥ የሚያስችል ነው። ይህ ስምምነት ሶማሊላንድን የራሷ ሉአላዊ ግዛት አድርጋ በምታያት ሶማሊያ ዘንድ ከፍተኛ ቁጣን ቀስቅሷል። ንብረትነቱ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የሆነ የበረራ ቁጥሩ ET8372 የተሰኘ አውሮፕላን ወደ ራስ ገዟ ሶማሊላንድ በዛሬው ዕለት በረራ በማድረግ ላይ እያለ እንዲመለስ መደረጉ ተገልጿል፡፡ የሶማሊያ ሲቪል አቪዬሽን ባለስልጣን በቀድሞ ስሙ ትዊተር አሁን ኤክስ አካውንቱ ይፋ እንዳደረገው የግዛቴ አካል ናት ወደ ሚላት ሶማሊላንድ ሀርጌሳ እየበረረ የነበረ አውሮፕላን እንዳያርፍ…
Read More
በአዲስ አበባ ያሉ የገበያ ቦታዎችን በአንድ ቦታ የሚያገኙበት ሞል ኢን አዲስ የተሰኘ መተግበሪያ ይፋ ሆነ፡፡

በአዲስ አበባ ያሉ የገበያ ቦታዎችን በአንድ ቦታ የሚያገኙበት ሞል ኢን አዲስ የተሰኘ መተግበሪያ ይፋ ሆነ፡፡

ሜልፋን ቴክ በተሰኘ ሀገር በቀል የቴክኖሎጂ ኩባንያ የተሰራው ሞል ኢን አዲስ መተግበሪያ በወጣት ኢትዮጵያዊያን የተሰራ ነው። የመልፋን ቴክኖሎጂ ስራ አስኪያጅ አቶ መልካሙ ምትኩ በፕሮግራሙ ማስጀመሪያ ላይ እንዳሉት መተግበሪያው ፈጣን እና የእለት ተዕለት  ህይወታችንን በማቅለል ረገድ ዓይነተኛ ሚና ይጫወታል። መልፋን ቴክ በቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ዘርፍ ከአምስት አመታት በላይ እየሰራ የሚገኝ ተቋም ከፌደራልና ከክልል አስተዳደሮች፣ ከግልና አንጋፋ ከሆኑ የአገሪቱ ተቋማት ጋር በርካታ ስራዎችን ሲሰራም ቆይቷል ብለዋል። የተለያዩ የሶፍትዌር ስራዎችን፣ የሞባይልና የኮምፒውተር አፕልኬሽኖችን፣ የተቋማትን ሲስተም ማበልፀግን እና ለዲጂታል ኢትዮጵያ እቅድ የበኩሉን አስተዋጽኦ በማድረግ ላይ እንደሚገኝ ስራ አስኪያጁ ተናግረዋል። መልፋን ቴክ ከ45 በላይ ለሚሆኑ ባለሙያዎች የስራ ዕድል ፈጥሮ፣ በመቶዎች የሚቆጠሩ ድርጅቶች በደንበኝነት አፍርቶ፣ ከ14…
Read More
የኢትዮጵ አየር መንገድ ወደ ካዛብላንካ ሞሮኮ አዲስ የጭነት በረራ ጀመረ

የኢትዮጵ አየር መንገድ ወደ ካዛብላንካ ሞሮኮ አዲስ የጭነት በረራ ጀመረ

አየር መንገዱ በአፍሪካ ያሉትን የጭነት መዳረሻዎች ብዛት ወደ 35 አሳድጓል። ወደ ካዛብላንካ የሚደረገው የጭነት በረራ ከ100 ቶን በላይ የመሸከም አቅም ባለው ቦይንግ 777-200F የእቃ ጭነት አውሮፕላን ነው ተብሏል። የኢትዮጵ አየር መንገድ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን ጣሰው “ወደ ካዛብላንካ ሞሮኮ አዲስ የጭነት በረራ አገልግሎት መስጠት በመጀመራችን ደስታ ተሰምቶናል ብለዋል በመልዕክታቸው። ይህ በረራ መጀመሩ በአፍሪካ ያለንን የዕቃ ጭነት መዳረሻ ቁጥር 35 ሲያደርስ፤ በተመሳሳይ ብሔራዊ አየር መንገዱ በእቃ ጭነት አገልግሎት ዘርፍ አስተማማኝ እና ቀልጣፋ አገልግሎት ለማቅረብ ያለውን ቁርጠኝነት የሚያረጋግጥ እንደሆነ ገልጸዋል። የኢትዮጵያ አየር መንገድ በጭነት በረራ መዳረሻዎች ብዛት ከአፍሪካ ቀዳሚ እና በዓለም የአየር የዕቃ ጭነት አገልግሎት መስክ ቁልፍ ሚና በመጫወት ላይ የሚገኝ…
Read More