Hotelbusiness

በአዲስ አበባ አስተማማኝ የፀጥታ ሁኔታ ባለመኖሩ የሆቴሎች ገቢ እየቀነሰ ነው ተባለ

በአዲስ አበባ አስተማማኝ የፀጥታ ሁኔታ ባለመኖሩ የሆቴሎች ገቢ እየቀነሰ ነው ተባለ

አስተማማኝ የፀጥታ ሁኔታ ባለመኖሩ የሆቴሎች ገቢ እየቀነሰ መሆኑን የአዲስ አበባ ሆቴል ባለቤቶች ማህበር እስታወቀ። ተደራራቢ ችግር እንደፈተነው የሚነገረው የሆቴል ስራ አገልግሎት አሁን ደግሞ የተረጋጋ ሰላም ባለመኖሩ ከአገልግሎቱ እየወጡ የሚገኙ ድርጅቶች መኖራቸው ታውቋል። የአዲስ አበባ ሆቴል ባለቤቶች ማህበር ፕሬዚዳንት ወይዘሮ አስቴር ሰለሞን ኮቪድ19 ካደረሰው ጉዳት ያላገገሙ ሆቴሎች አሁን ደግሞ በፀጥታ ችግር ምክንያት ከውጭ የሚገቡ ደንበኞቻቸውን እንደልብ ማግኘት አልቻሉም ብለዋል። ለተከታታይ ዓመታት የዘለቀው የፀጥታ ችግር አሁንም መቀጠሉ በኮከብ ደረጃ ያሉ ሆቴሎች ገቢያቸውን በሀገር ውስጥ ደንበኞች ብቻ መሸፈን አዳጋች እንዳደረገባቸውም ገልፀዋል። በኮቪድ 19 ወቅት ሆቴሎች ሰራተኞችን እንዳይበትኑና ለአንዳንድ ወጪዎች እስከ 5 በመቶ የወለድ ምጣኔ ብድር ማግኘታቸውን ያስታወሱት ፕሬዚዳንቷ፥ አሁን ላይ ይህ ድጋፍ መቅረቱን…
Read More
የሆቴል ባለቤቶች የባንክ ዕዳ መክፈያ ጊዜ እንዲራዘምላቸው ጠየቁ

የሆቴል ባለቤቶች የባንክ ዕዳ መክፈያ ጊዜ እንዲራዘምላቸው ጠየቁ

የኢትዮጵያ የሆቴል እና ቱሪዝም አሠሪዎች ፌዴሬሽን እንደገለጸው በኢትዮጵያ የሆቴል እና ቱሪዝም ስራ በየጊዜው እየተዳከመ መሆኑን አስታውቋል፡፡ የፌዴሬሽኑ ፕሬዚዳንት ዶክተር ፍትህ ወልደሰንበት ለቪኦኤ እንዳሉት የሆቴል እና ቱሪዝም ቢዝነስ በዓለም ላይ በኮሮና ቫይረስ ምክንያት ተዳክሞ የነበረ ቢሆንም አሁን ላይ ወደ ቀድሞ አቋሙ ተመልሷል ብለዋል፡፡ በኢትዮጵያም የሆቴል ኢንዱስትሪ ከኮሮና ቫይረስ ጉዳት እንዲያገግም ለመንግስት በቀረቡለት ምክረ ሀሳቦች መሰረት እርምጃ መውሰዱ ዘርፉን ከባሰ ጉዳት ታድጎታል ብለዋል። የኮቪድ ፕሮቶኮል በሚል ወደ ስራ የተተገበረው አሰራር በኮሮና ቫይረስ ምክንያት ስራ አቁመው የነበሩ ሆቴሎችን ወደ ስራ እንዲመለሱ ማድረጉን ፕሬዝዳንቱ ተናግረዋል። ይሁንና በኢትዮጵያ ግን በየጊዜው እየተዳከመ እና በርካታ የሆቴል ቢዝነስ ባለሀብቶች እና ባለሙያዎች ወደ ሌላ ቢዝነስ እየገቡ መሆኑንም ፕሬዝዳንቱ ተናግረዋል፡፡…
Read More