መነሻ ገፅ

በአዲስ አበባ አንድ የወረዳ አመራር በፖሊስ ተገደሉ

በአዲስ አበባ አንድ የወረዳ አመራር በፖሊስ ተገደሉ

በአዲስ አበባ አንድ የወረዳ አመራር በፖሊስ ተገደሉ በአዲስ አበባ ከተማ የቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ 08 ዋና ስራ አስፈፃሚ የሆኑት አቶ አለባቸው አሞኜ በቢሯቸው ውስጥ በአዲስ አበባ ፖሊስ አባል ተገደሉ። የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ባወጣው መግለጫ ግድያውን የፈፀመው በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ የካሳንቺስ አካባቢ ፖሊስ ጣቢያ የማህበረሰብ አቀፍ ፖሊስ አገልግሎት የቀጠና ኦፊሰር የሆነ አባል ነው፡፡ የፖሊስ አባሉ የግል ጉዳዩ እንዲፈፀምለት በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ለወረዳ 8 አስተዳደር ጽ/ቤት ያመለከተውን ማመልከቻ ለመከታተል ወደ ወረዳው መጽህፈት ቤት መሄዱን ኮሚሽኑ ገልጿል፡፡ የወረዳው ስራ አስፈጻሚም ጉዳዩን ተመልክቶ ምላሽ እንደሚሰጠው የተገለፀለት ቢሆንም ጥያቄዬ እንዳይፈፀም የከለከልከው አንተነህ በሚል ምክንያት ቢሯቸው ውስጥ በስራ ላይ እንዳሉ በታጠቀው ሽጉጥ መግደሉን…
Read More
በአዲስ አበባ የአንድ ወረዳ ስራ አስፈጻሚ ተገደሉ

በአዲስ አበባ የአንድ ወረዳ ስራ አስፈጻሚ ተገደሉ

በአዲስ አበባ የአንድ ወረዳ ስራ አስፈጻሚ ተገደሉ በአዲስ አበባ ከተማ የቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ 08 ዋና ስራ አስፈፃሚ የሆኑት አቶ አለባቸው አሞኜ በቢሮአቸው ውስጥ ተገደሉ። የክፍለ ከተማው ኮሚኒኬሽን ባሰራጨው መረጃ ፤ " አቶ አለባቸው አሞኜ ቢሯቸው ውስጥ ቁጭ ብለው የህዝብ አገልግሎት በሚሰጡበት ወቅት ከአንድ ተገልጋይ በሽጉጥ ተገድለዋል። ክፍለ ከተማው ስለ ግድያው ተጨማሪ መረጃ ባያደርግም ግድያውን ፈጽማል የተባለለው ተጠርጣሪ በፖሊስ ቁጥጥር ስር ውሏል ብሏል። ክፍለከተማው ባወጣው መግለጫ " አቶ አለባቸው በስራ ቁርጠኝነት የሚታወቁ ናቸው" "በበርካታ መንግስታዊና ህዝባዊ ተግባራት አርዓያነት ያለው ስራ የሰሩና ያስተባበሩ አመራራችን ነበሩ " ሲል ገልጿል። አመራሩ በደረሰባቸው ጥቃት ወደ ህክምና ቦታ ቢወሰዱም ህይወታቸውን ማትረፍ እንዳልተቻለ ተገልጿል።
Read More
ቅዱስ ጊዮርጊስ እግር ኳስ ክለብ በመቻል ተሸነፈ

ቅዱስ ጊዮርጊስ እግር ኳስ ክለብ በመቻል ተሸነፈ

በቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕርሚየር ሊግ 23ኛ ሳምንት መርሐ ግብር መሪው ቅዱስ ጊዮርጊስ ከመቻል ጋር ያደረጉትን ጨዋታ 1 ለ 0 በሆነ ውጤት ተሸንፏል። የመቻልን የማሸነፊያ ግብ የቀድሞ የፈረሰኞቹ ተጨዋች ከነዓን ማርክነህ በፍፁም ቅጣት ምት ከመረብ ማሳረፍ ችሏል። ፈረሰኞቹ በዛሬው ጨዋታ ሙሸነፋቸውን ተከትሎ በውድድር አመቱ ሁለተኛ ሽንፈታቸውን አስተናግደዋል። የቀድሞው መከላከያ እግር ኳስ ክለብ የአሁኑ መቻል ማሸነፉን ተከትሎ ነጥቡን 33 በማድረስ 5ኛ ደረጃ ላይ ሲቀመጥ ሽንፈት ያስተናገደው ቅዱስ ጊዮርጊስ በ51 ነጥብ ሊጉን እየመራ ይገኛል። የሊጉ መሪ ቅዱስ ጊዮርጊስ ሽንፈት ማስተናገዱን ተከትሎ ከተከታዩ ባህርዳር ከተማ ጋር ያለው የነጥብ ልዩነት ወደ አራት ጠቧል። በቀጣይ የሊጉ መርሐ ግብር ቅዱስ ጊዮርጊስ ከ ሀዋሳ ከተማ እንዲሁም መቻል ከ ሲዳማ…
Read More
የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ፍሰት የሁለት ቢሊዮን ዶላር ጉድለት አሳየ

የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ፍሰት የሁለት ቢሊዮን ዶላር ጉድለት አሳየ

ኢትዮጵያ ባለፉት ዘጠኝ ወራት 4 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ከውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ለመሳብ አቅዳ እንደነበር ተገልጿል፡፡ የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባቀረበው ሪፖርቱ ላይ እንደገለጸው ባለፉት ዘጠኝ ወራት ውስጥ ከውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት 2 ነጥብ 7 ቢሊዮን ዶላር አግኝታለች፡፡ የኢንቨስትመንት ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ሌሊሴ ነሜ እንዳሉት ባለፉት ዘጠኝ ወራት ውስጥ 4.5 ቢሊዮን ዶላር ኢንቨስትመንት ወደ አገር ውስጥ ለመሳብ ታቅዶ 2.67 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ተገኝቷል፡፡ የኮሚሽኑ አፈጻጸም የዕቅዱን 61 በመቶ ብቻ ያሳካ ሲሆን በሰሜን ኢትዮጵያ የነበረው ጦርነት፣ በኦሮሚያ እና ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ያለው አለመረጋጋት እንዲሁም በዩክሬን እና ሩሲያ ጦርነት ምክንያት ያጋጠመው የዓለም ኢኮኖሚ መቀዛቀዝ ለአፈጻጸሙ መቀነስ ዋነኛ ምክንያቶች ናቸው ተብሏል፡፡ ወደ…
Read More
ብሔራዊ ባንክ ለኤምፔሳ የሞባይል ፋይናንስ አገልግሎት ፈቀድ ሰጠ

ብሔራዊ ባንክ ለኤምፔሳ የሞባይል ፋይናንስ አገልግሎት ፈቀድ ሰጠ

ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ የሞባይል የገንዘብ ክፍያ አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችለውን ፈቃድ ከብሔራዊ ባንክ አግኝቷል። ከሁለት ዓመት በፊት ወደ ኢትዮጵያ የገባው ሳፋሪ ኮም ኢትዮጵያ የቴሌኮም ኩባንያ አሁን ደግሞ ተጨማሪ ፈቃድ ማግኘቱን አስታውቋል። ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ በኤምፔሳ አማካኝነት የሞባይል የገንዘብ ክፍያ አገልግሎት መስጠት የሚያስችለውን ፈቃድ ከብሔራዊ ባንክ አግኝቷል። የብሔራዊ ባንክ ገዥ ማሞ ምህረቱ ባንኩ የዲጅታል ፋይናንስ አገልግሎት መስጠት የሚያስችለው የሞባይል የገንዘብ ክፍያ አገልግሎት ፈቃድን ለሳፋሪ ኮም መስጠቱን አስታውቀዋል፡፡ ይህም ሳፋሪኮም በኢትዮጵያ የሞባይል የገንዘብ ክፍያ አገልግሎት ፈቃድ ያገኘ የመጀመሪያው የውጭ አገር ኩባንያ እንደሚያደርገው የብሔራዊ ባንክ መረጃ ያመለክታል፡፡ ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ከሰሞኑ በፈረንሳይ የኢትዮጵያ አምባሳደር የነበሩት አምባሳደር ሔኖክ ተፈራን አዲስ ሀላፊነት መስጠቱ ይታወሳል። አምባሳደር ሔኖክ የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ የውጭ ጉዳዮች…
Read More
ከኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ፓርኮች 51 ባለሀብቶች ለቀው መውጣታቸው ተገለጸ

ከኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ፓርኮች 51 ባለሀብቶች ለቀው መውጣታቸው ተገለጸ

በኢትዮጵያ የተሰማሩ የውጭ ሀገራት ኢንቨስተሮች በሙስና ምክንያት ከሚሰሩባቸው የኢንዱስትሪ ፓርኮች ለቀው እየወጡ እንደሆነ ተገልጿል፡፡ የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን የበጀት ዓመቱን ዘጠኝ ወራት እቅድ አፈጻጸም ሪፖርት ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አቅርቧል፡፡ በኢትዮጵያ በተለያዩ የምርት ዘርፎች የተሰማሩ የውጭ ሀገራት ኩባንያዎች ከመንግስት ተቋማት መሪዎች እና ባለሙያዎች በሚጠየቁ ክፍያ ምክንያት መማረራቸው ተገልጿል፡፡ ምክር ቤቱ የኢንቨስትመንት ኮሚሽኑንን ሪፖርት በገመገመበት ወቅት እንደገለጸው በኦሮሚያ ክልል ዱከም ከተማ አቅራቢያ በሚገኘው ኢስተርን ኢንዱስትሪ ፓርክ ያሉ ኩባንያዎች ቅሬታ እንዳላቸው ገልጸዋል፡፡ የምክር ቤቱ አባላት በዚህ ኢንዱስትሪ ፓርክ ባደረጉት ምልከታ ኢንቨስተሮች የሚጠይቋቸውን ከትንሽ እስከ ትልቅ አገልግሎቶች በገንዘብ እየገዙ ነው ብለዋል፡፡ እንዲሁም በፓርኩ ላይ የባለቤትነት ስሜት ባለመኖሩ ፓርኮች ውስጥ እየገቡ ዘረፋ እየተፈጸባቸው መሆኑን የምክር…
Read More
ድምጻዊ አቤል ተስፋዬ ”ሳምራ” በሚል የሰየመውን የኢትዮጵያ ቡና ለገበያ አቀረበ

ድምጻዊ አቤል ተስፋዬ ”ሳምራ” በሚል የሰየመውን የኢትዮጵያ ቡና ለገበያ አቀረበ

ከኢትዮጵያዊ ቤተሰቦቹ በካናዳ ተወልዶ ያደገው ድምጻዊ አቤል ተስፋዬ “ዘ ዊክኤንድ”፤ የእናቱን እና የቤተሰቡን ትውልድ አገር ለማክበር በሚል በእናቱ ሥም የሰየመውን ”ሳምራ” የተሰኘ የኢትዮጵያ ቡና ለአለም ዓቀፍ ገበያ አቀረበ። አቤል ቡናውን ከ“ብሉ ቦትል ኮፊ” ጋር በመተባባር ለሽያጭ ማቅረቡን በትዊተር ገጹ ላይ ባሰፈረው ጽሁፍ ይፋ አድርጓል። አቤል ተስፋዬ እና የሪከርድ ኩባንያው በጋራ በመሆን “ብሉ ቦትል ኮፊ” በሚል ሥም ባቋቋሙት ድርጅት ሥር የኢትዮጵያን ባሕል እና የኢትዮጵያን ቡና በዓለም ደረጃ መሸጥ መጀመራቸውን ገልጿል፡፡ አቤል የ“ሳምራ ቡና” ወደገበያ መግባትን አስመልክቶ በተሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ "የኢትዮጵያ ባህል የማንነቴ ወሳኙ አካል ነው” ያለ ሲሆን፤ ከ‘ብሉ ቦትል ኮፊ’ ጋር በመሆን የኢትዮጵያን ባሕል፣ ወጎች፣ እሴቶች እና ቡና ላይ የዓለም…
Read More
ሳፋሪ ኮም ኢትዮጵያ አምባሳደር ሔኖክ ተፈራን ሾመ

ሳፋሪ ኮም ኢትዮጵያ አምባሳደር ሔኖክ ተፈራን ሾመ

ከሁለት ዓመት በፊት ወደ ኢትዮጵያ የገባው ሳፋሪኮም ቴሌኮም ኩባንያ አዲስ ሀላፊ ሾሟል። ላለፉት ሶስት ዓመታት በፈረንሳይ የኢትዮጵያ አምባሳደር የነበሩት አምባሳደር ሔኖክ ተፈራ በሳፋሪኮም ኢትዮጵያ አዲስ ሀላፊነት ተሰጥቷቸዋል። አምባሳደር ሔኖክ የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ የውጭ ጉዳዮች እና ቁጥጥር ሀላፊ ሆነው ተሹመዋል። ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ለኢትዮ ነጋሪ እንዳረጋገጠው አምባሳደር ሔኖክ የቀድሞውን የድርጅቱ መሪ የነበሩት ማቲው ሀሪሰንን ተክተዋል። አምባሳደር ሔኖክ ተፈራ ከ2018 እስከ 2022 ድረስ በፈረንሳይ የኢትዮጵያ አምባሳደር ሆነው አገልግለዋል። ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ከ20 በላይ ከተሞች የቴሌኮም አገልግሎት በመስጠት ላይ ሲሆን በቅርቡም በኤምፔሳ አማካኝነት የሞባይል ፋይናንስ አገልግሎት ፈቃድ ከብሔራዊ ባንክ እንደሚያገኝ ተገልጿል።
Read More
አቶ ልደቱ አያሌው እጃቸውን ለመስጠት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚመጡ ገለጹ

አቶ ልደቱ አያሌው እጃቸውን ለመስጠት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚመጡ ገለጹ

ፖለቲከኛው ልደቱ ወደ ኢትዮጵያ የሚመጡት በሽብርተኝነት ለቀረበባቸው ክስ በአደባባይ ለመሟገት እንደሆነ ተናግረዋል መንግስት ህገ መንግስታዊ ስርዓቱን ለማናጋት ሙከራ አድርገዋል በሚል በሽብርተኛነት ከወነጀላቸው ግለሰቦች መካከል አንዱ የሆኑት አቶ ልደቱ የተከሰሱበትን ክስ በአደባባይ ለመሞገት መወሰናቸው በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ላይ ጽፈዋል፡፡ በፅሁፋቸውም “ከአገዛዙ አፈና ፣ እስርና ግድያ ሸሽቶ በማምለጥ የሚመጣ መፍትሄ የለም። ትግላችን ሰላማዊና ህጋዊ እስከሆነ ድረስ በገፍ እየታሰርንና እየሞትን አገዛዙ በሀይልና በአፈና ሊያሸንፈን እንደማይችል ተስፋ ልናስቆርጠው ይገባል። በዚህ መጠን ዋጋ ለመክፈል ካልቆረጥን በስተቀር የአገርና የህዝብ ህልውና ከጥፋት ሊድን አይችልምና።” ያሉ ሲሆን “ይህንን በለጋ የልጅነት ዘመኔ ለራሴ የገባሁትን የትግል ቃል-ኪዳንና የምታመንለትን የሰላማዊነትና ህጋዊነት መርህ መሰረት በማድረግ ወደ አገሬ ለመመለስና የዶ/ር ዐቢይን የፈጠራ የአሸባሪነት…
Read More
በአማራ ክልል የተጀመረው “ህግ የማስከበር ዘመቻ” ለሰብዓዊ መብት ስጋት መሆኑ ተገለጸ

በአማራ ክልል የተጀመረው “ህግ የማስከበር ዘመቻ” ለሰብዓዊ መብት ስጋት መሆኑ ተገለጸ

የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) የ2015 ዓ.ም. በጀት ዓመት የ9 ወር የሥራ ክንውን ሪፖርቱን ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የዴሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አቅርቧል፡፡ ኮሚሽኑ ባቀረበው የሥራ ዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት ባደራጃቸው ዘጠኝ የትኩረት መስኮች የተከናወኑ ዋና ዋና ተግባራት፣ የተገኙ ውጤቶች እና ያጋጠሙ ተግዳሮቶች በዝርዝር ተካትተዋል፡፡  በቀረበው ሪፖርት የሰብአዊ መብቶች ክትትልና ምርመራን በተመለከተ ኮሚሽኑ በዋናው መሥሪያ ቤቱና በከተማ ጽሕፈት ቤቶቹ በ1491 ሰዎች 1680 ጉዳዮች ላይ አቤቱታ የቀረቡለት ሲሆን ከነዚህም መካከል በኮሚሽኑ ሥልጣን ሥር የሚወድቁ 1084 አቤቱታዎችን ተቀብሎ ማስተናገዱ ተገልጿል፡፡ አቤቱታ ከቀረበባቸው ጉዳዮች መካከል አብዛኞቹ የሲቪል እና የፖለቲካ መብቶችን የተቀሩትደግሞ የኢኮኖሚያዊናየማኅበራዊ መብቶችንየተመለከቱ ናቸው።  ኮሚሽኑ በ48 ማረሚያ ቤቶች እና በ323 ፖሊስ ጣቢያዎች አካሄድኩት ባለው…
Read More