Ethiopia

በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን በተፈጸመ የድሮን ጥቃት 30 ንጹሃን ተገደሉ

በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን በተፈጸመ የድሮን ጥቃት 30 ንጹሃን ተገደሉ

በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ሞጃ እና ወደራ ወረዳ ሳሲት በተባለች ከተማ ህዝብ ያሳፈረ አይሱዙ ተሽከርካሪ ላይ በተፈጸመው ጥቃት 30 ሰዎች ሲገደሉ 18 ሰዎች መቁሰላቸውን ነዋሪዎች ተናግረዋል፡፡ ከአምስት ቀን በፊት ሳሲት በተባለችው ከተማ አቅራቢያ 50 ሰዎችን ያሳፈረ አይሱዙ ተሽከርካሪ መንገደኞችን ለማውረድ በቆመበት ተፈጽሟል በተባለው ጥቃት 18 ሰዎች መቁሰላቸውንም ነው የአይን እማኞችን የጠቀሰው የሪሊፍ ዌብ ዘገባ የሚያሳየው። የድሮን ጥቃቱ ሲፈጸም በአካባቢው በመከላከያ ሰራዊትና በፋኖ ታጣቂዎች መካከል ጦርነት እንዳልነበር የተናገሩት ነዋሪዎች፥ ጥቃቱ ከተፈጸመ በኋላም ድሮኖች በአካባቢው ሲሽከርከሩ እንደነበር ገልጸዋል። የድሮን ጥቃቱ የተፈጸመው መከላከያ ሰራዊት እና የፋኖ ታጣቂዎች ውጊያ ከሚያደርጉበት አካባቢ በ24 ኪሎሜትር ርቀት ላይ እንደተፈጸመ ሮይተርስ ዘግቧል፡፡ “መጀመሪያ ከባድ ፍንዳታ ሰማን ከዚያም…
Read More
የኢትዮጵያ እንባ ጠባቂ ተቋም መቀሌ ቅርንጫፍ ቅሬታዎችን ማየት እንዳልቻለ ተናገረ

የኢትዮጵያ እንባ ጠባቂ ተቋም መቀሌ ቅርንጫፍ ቅሬታዎችን ማየት እንዳልቻለ ተናገረ

በትግራይ ክልል ጦርነት የቆመ ቢሆንም ከጫፍ ጫፍ ተንቀሳቅሶ መስራት አደጋች ሆኗል ተብሏል፡፡ በክልሉ ከመልካም አስተዳድር ጥያቄዎች ይልቅ የምግብ ጉዳይ ዋነኛው ችግር እንደሆነም ተገልጿል፡፡ በሰሜን ኢትዮጵያ ለሁለት ዓመት በቆየው ጦርነት ምክንት ስራ አቁሞ ከነበሩ አገልግሎት ሰጪ ተቋማት መካከል የኢትዮጵያ ህዝብ እንባ ጠበቃ ተቋም መቀሌ ቀርንጫፍ አንዱ ነበር፡፡ ይህ ጦርነት በደቡብ አፍሪካ በአፍሪካ ህብረት አደራዳሪነት በተደረገው የፕሪቶሪያ ስምምነት መሰረት ጦርነቱ የቆመ ሲሆን አገልግሎት ሰጪ ተቋማትም ዳግም ስራ ጀምረዋል፡፡ ከታህሳስ 2015 ዓ.ም ጀምሮ ሥራውን በአዲስ መልክ የጀመረው የኢትዮጵያ እንባ ጠባቂ ተቋም መቀሌ ቅርንጫፍ በበጀት እጥረት ምክንያት ጉዳዮችን ለመመልከት አዳጋች እየሆነበት እንደመጣ የቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ ተወካይ የሆኑት ወ/ሮ ደጋፊት ረዳ ለኢትዮ ነጋሪ ተናግረዋል። ተወካይዋ እንዳሉት…
Read More
የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ከ4 ዓመታት በኋላ ወደ አዲስ አበባ ሊመለስ ነው

የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ከ4 ዓመታት በኋላ ወደ አዲስ አበባ ሊመለስ ነው

የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የ2016 እግር ኳስ ውድድር የጨዋታ ፕሮግራም ባሳለፍነው ነሀሴ ከወጣ በኋላ መስከረም 20 ቀን 2016 ዓም መጀመሩ ይታወሳል፡፡ የፕሪሚየር ሊጉ የመክፈቻ ጨዋታን ባለሜዳው አዳማ ከነማ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ መካከል ተደርጎም ነበር፡፡ የፕሪሚየር ሊጉ ጨዋታዎች ላለፉት አራት ዓመታት በአዳማ፣ ድሬዳዋ፣ሐዋሳ እና ባህርዳር ስታዲየሞች ሲካሄዱ ቆይተዋል፡፡ የአዲስ አበባ ስታዲየም በእድሳት ምክንያት የፕሪሚየር ሊግ እና የብሔራዊ ቡድን ጨዋታዎችን ወደ ክልል ከተሞች እንዲዞሩ የግድ ሆኖ ቆይቶም ነበር፡፡ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ሼር ካምፓኒ እንደገለጸው የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ የመጨረሻዎቹ ሶስት ሳምንታት በአዲስ አበባ ስታዲየም እንደሚደረግ ገልጿል። የ2016 የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የሁለተኛ ዙር የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ውድድር መርሃ ግብርና የውድድር ሜዳዎች ይፋ ተደርገዋል። በዚህም በስታዲየሞች…
Read More
ኢትዮጵያ ወደ ውጭ ሀገራት ከተላከ ቅባት እና ጥራጥሬ እህሎች 285 ሚሊዮን ዶላር ገቢ አገኘች

ኢትዮጵያ ወደ ውጭ ሀገራት ከተላከ ቅባት እና ጥራጥሬ እህሎች 285 ሚሊዮን ዶላር ገቢ አገኘች

ባለፉት ስድስት ወራት ከቅባትና ጥራጥሬ እህሎች የወጪ ንግድ 285 ነጥብ 53 ሚሊየን የአሜሪካን ዶላር ገቢ መገኘቱን የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር ገልጿል፡፡ በተያዘው በጀት ዓመት የመጀመሪያዎቹ ስድስት ወራት ከቅባት እህሎች የወጪንግድ 109 ነጥብ 66ሚሊየን የአሜሪካን ዶላር ገቢ የተገኘ ሲሆን አፈጻጸሙም 109 በመቶ መሆኑን ሚኒሰቴሩ በስድስት ወራት አፈጻጸም ሪፖርቱ ገልጿል፡፡ ይህም ካምናው ተመሳሳይ ወቅት አፈጻጸም ጋር ሲነጻጸር የ26 ሚሊየን ዶላር ብልጫ እንዳለው ሪፖርቱ አመላክቷል፡፡ በስድስት ወራቱ በጥራጥሬ እህል የተገኘው ገቢ 176 ሚሊየን የአሜሪካን ዶላር ሲሆን ካለፈው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸርም የ77 ሚሊየን ዶላር ብልጫ እንዳለው በሪፖርቱ ተመላክቷል፡፡ በዚህም ባለፉት ስድስት ወራት ከቅባትና ጥራጥሬ እህሎች የወጪ ንግድ በድምሩ 285 ነጥብ 53 ሚሊየን የአሜሪካን…
Read More
በአዲስ አበባ አስተማማኝ የፀጥታ ሁኔታ ባለመኖሩ የሆቴሎች ገቢ እየቀነሰ ነው ተባለ

በአዲስ አበባ አስተማማኝ የፀጥታ ሁኔታ ባለመኖሩ የሆቴሎች ገቢ እየቀነሰ ነው ተባለ

አስተማማኝ የፀጥታ ሁኔታ ባለመኖሩ የሆቴሎች ገቢ እየቀነሰ መሆኑን የአዲስ አበባ ሆቴል ባለቤቶች ማህበር እስታወቀ። ተደራራቢ ችግር እንደፈተነው የሚነገረው የሆቴል ስራ አገልግሎት አሁን ደግሞ የተረጋጋ ሰላም ባለመኖሩ ከአገልግሎቱ እየወጡ የሚገኙ ድርጅቶች መኖራቸው ታውቋል። የአዲስ አበባ ሆቴል ባለቤቶች ማህበር ፕሬዚዳንት ወይዘሮ አስቴር ሰለሞን ኮቪድ19 ካደረሰው ጉዳት ያላገገሙ ሆቴሎች አሁን ደግሞ በፀጥታ ችግር ምክንያት ከውጭ የሚገቡ ደንበኞቻቸውን እንደልብ ማግኘት አልቻሉም ብለዋል። ለተከታታይ ዓመታት የዘለቀው የፀጥታ ችግር አሁንም መቀጠሉ በኮከብ ደረጃ ያሉ ሆቴሎች ገቢያቸውን በሀገር ውስጥ ደንበኞች ብቻ መሸፈን አዳጋች እንዳደረገባቸውም ገልፀዋል። በኮቪድ 19 ወቅት ሆቴሎች ሰራተኞችን እንዳይበትኑና ለአንዳንድ ወጪዎች እስከ 5 በመቶ የወለድ ምጣኔ ብድር ማግኘታቸውን ያስታወሱት ፕሬዚዳንቷ፥ አሁን ላይ ይህ ድጋፍ መቅረቱን…
Read More
25 የምናባዊ ግብይት አቀላጣፊ ድርጅቶች ማዕከላቸውን በኢትዮጵያ መክፈታቸው ተገለጸ

25 የምናባዊ ግብይት አቀላጣፊ ድርጅቶች ማዕከላቸውን በኢትዮጵያ መክፈታቸው ተገለጸ

ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ ተቋማት ወደ ሀገሯ እንዲመጡ በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን እና ሌሎች ተቋማት በኩል እያስተዋወቀች ትገኛለች። በዚህም መሰረት እስካሁን 25 የዳታ ማይኒንግ ድርጅቶች የተመዘገቡ ሲሆን ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሀይል ጋር የሀይል አቅርቦት ስምምነት በመፈራረም ላይ ናቸው። ከ25ቱ ተቋማት ውስጥም አራቱ ሥራ መጀመራቸውን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የገበያና ቢዝነስ ልማት መምሪያ አስታውቋል። የመምሪያው ዳይሬክተር አቶ ህይወት እሸቱ እንዳስታወቁት የዳታ ማይኒንግ ኩባንያዎቹ በሀገር ውስጥ ኃይል የሚጠቀሙ ቢሆንም የፍጆታ ሂሳባቸውን በዶላር እንዲከፍሉ ከስምምነት ተደርሷል ብለዋል፡፡ የኢንቨስትመንት ፍቃድና ሌሎች አስፈላጊ መስፈርቶችን ካሟሉት ከሃያ አምስቱ ድርጅቶች መካከል አራቱ ከ10 እስከ 100 ሜጋ ዋት ድረስ ኃይል መጠቀም ጀምረዋልም ተብሏል። ለመጀመሪያ ጊዜ  በሀገር ውስጥ በውጭ ምንዛሪ ከተከናወነው ሽያጭ አስቀድመው…
Read More
ማውሪታኒያ የአፍሪካ ህብረት ሊቀመንበርነትን ከኮሞሮስ ተረከበች።

ማውሪታኒያ የአፍሪካ ህብረት ሊቀመንበርነትን ከኮሞሮስ ተረከበች።

37ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ በአዲስ አበባ በመካሄድ ላይ ሲሆን የህብረቱ አባል ሀገራት መሪዎች በመሳተፍ ላይ ናቸው፡፡ ምዕራብ አፍሪካዊቷ ማውሪታኒያ በ2024 የአፍሪካ ህብረትን በሊቀመንበርነት እንድትመራ የተመረጠች ሲሆን የሊቀመንበርነት ቦታውን ከ2023 የህብረቱ ሊቀመንበር ከነበረችው ኮሞሮስ ተረክባለች፡፡ የማውሪታኒያ ፕሬዝደንት መሀመድ ኦዉልድ ጋዞኒ ከወቅቱ የህብረቱ ሊቀመንበር ከኮሞሮሱ ፕሬዝደንት አዛሊ አሶውማኒ ተረክበዋል። የአፍሪካ ህብረት ሊቀመንበርነት ስልጣን የህብረቱ አባል ሀገራት በየዓመቱ እየተቀያየሩ የሚያገኙት ስልጣን ሲሆን ከህብረቱ ኮሚሽን ኮሚሽነር ጋር በመሆን ስራን ማቀላጠፍ እንዲሁም አፍሪካን የሚመለከቱ ዓለም አቀፍ መድረኮች ላይ የመሳተፍ ሀላፊነት አለበት፡፡ ፕሬዝደንት ኦውልድ ዛሬ የተመረጡት የህብረቱ ስራ አስፈጻሚ ምክር ቤት የሆነው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ባለፈው ረብዕ እና ሐሙስ ዕለት ባካሄዱት ጉባኤ እንዲመረጡ ይሁንታ ከሰጣቸው…
Read More
አቶ ዱላ መኮንን የዳሸን ባንክ ቦርድ ሊቀ-መንበር ሆነው ተመረጡ

አቶ ዱላ መኮንን የዳሸን ባንክ ቦርድ ሊቀ-መንበር ሆነው ተመረጡ

የዳሸን ባንክ ባለአክሲዮኖች ባካሄዱት 30ኛው መደበኛ ጉባኤ የተመረጠውና የምርጫውም ውጤት በኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የፀደቀለት አዲሱ የዳሸን ባንክ ቦርድ ባደረገው የመጀመሪያ ጉባኤ ላይ ባለፉት ሶስት ዓመታት ባንኩን በዳይሬክተሮች ቦርድ ሊቀ-መንበርነት ያገለገሉትን አቶ ዱላ መኮንንን በድጋሚ በዳይሬክተሮች ቦርድ ሊቀ-መንበርነት መርጧል፡፡  አዲሱ ቦርድ የካቲት 05 ቀን 2016 ዓ.ም በሸራተን አዲስ ሆቴል ባካሄደው ጉባኤ ለቀጣይ ሶስት አመታት ዳሸን ባንክን በዳይሬክተሮች ቦርድ ሊቀ-መንበርነት እንዲያገለግሉ በድጋሜ የመረጣቸው አቶ ዱላ መኮንን በአሁኑ ወቅት የሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ የማዕድን ዘርፍ ምክትል ዋና ስራ አስፈፃሚ ሆነው በማገልገል ላይ ይገኛሉ፡፡  አዲሱ ሊቀመንበር አቶ ዱላ መኮንን የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን ከአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ በኤሌክትሪካል ኢንጅነሪንግ፣ እንዲሁም የማስተርስ ዲግሪያቸውንም በቢዝነስ አስተዳደር ከዚሁ ዩኒቨርሲቲ አግኝተዋል፡፡…
Read More
አዲሱ የአውሮፓ ህብረት ሕግ በአምስት ሚሊዮን ኢትዮጵያዊያን ገበሬዎች ላይ የሕልውና አደጋ ደቅኗል ተባለ

አዲሱ የአውሮፓ ህብረት ሕግ በአምስት ሚሊዮን ኢትዮጵያዊያን ገበሬዎች ላይ የሕልውና አደጋ ደቅኗል ተባለ

የአውሮፓ ህብረት ከሁለት ሳምንት በፊት ባወጣው አዲስ ህግ የአካባቢ ጥበቃ ስራዎችን የሚጎዱ ምርቶችን ወደ ህብረቱ አባል ሀገራት ገበያዎች እንዳይገቡ እና እንዳይሸጡ አደርጋለሁ ብሏል፡፡ የምድርን ሙቀት ለመከላከል እና የደን ምንጣሮን ለመከላከል ይረዳል በሚል የተዘጋጀው ይህ ህግ ከደን ምርቶች ጋር የተያያዙ ምርቶች በአውሮፓ የገበያ እድል እንዳያገኙ መከልከል እና የአካባቢ ጥበቃ ስራዎችን ማበረታታት የህጉ ዋነኛ ዓላማ ነው፡፡ ይህ ሕግ የጫካ ቡናዎችን ወደ አውሮፓ እና ሌሎች ዓለም ገበያ መዳረሻዎች የምትልከው ኢትዮጵያን እንደሚመለከት ስጋቶች ተነስተዋል፡፡ የኢትዮጵያ ቡና ማህበር ጉዳዩ እንዳሳሰበው ገልጾ አዲሱ የአውሮፓ ህግ የኢትዮጵያን ነባራዊ ሁኔታ እንዲረዳ ካልተደረገ ሚሊዮኖች ወደ ድህነት ሊወርዱ ይችላሉ ሲሉ አስጠንቅቀዋል፡፡ የማህበሩ ፕሬዝዳንት ሁሴን አምቦ (ዶ/ር) ለአልዐይን እንዳሉት “በኢትዮጵያ ቡና…
Read More
ኢትዮጵያ የክሪፕቶከረንሲ መረጃ ማዕከል መሆን የሚያስችላትን ስምምነት ተፈራረመች

ኢትዮጵያ የክሪፕቶከረንሲ መረጃ ማዕከል መሆን የሚያስችላትን ስምምነት ተፈራረመች

ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የምናበዊ ገንዘብ ወይም የክሪፕቶከረንሲ ግብይት ፍላጎት እየጨመረ ሲሆን በኢትዮጵያም አጀንዳ ከሆነ አምስት ዓመት ሆኖታል፡፡ ከሁለት ዓመት በፊት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የትኛውንም ክሪፕቶ ከረንሲ ግብይት እንዳልፈቀደ እና ግብይት ሲፈጽሙ የተገኙ ሰዎችም በህግ ተጠያቂ እንደሚሆኑ አስታውቆ ነበር፡፡ ካሳለፍነው ዓመት ጀምሮ በኢትዮጵያ የቢትኮይን ግብይት መፈጸም የሚያስችሉ መሰረተ ልማት ግንባታ የሚያደርጉ ኩባያዎች ፍላጎት እየጨመረ መጥቷል፡፡ ኢትዮጵያ አሁንም የክሪፕቶከረንሲ ግብይት እንዲደረግ ያልፈቀደች ሲሆን የዳታ ማዕከል ግንባታዎች እንዲካሄዱ ግን ስምምነቶችን በመፈራረም ላይ ነች፡፡ በዛሬው ዕለትም ዌስት ዳታ ማዕከል የተሰኘው ኩባንያ የ250 ሚሊዮን ዶላር ስምምነት በአዲስ አበባ ከኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግ ጋር ተፈራርሟል፡፡ በዚህ ስምምነት መሰረት የቢትኮይን ግብይት እና አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ጉዳዮች ዙሪያ ስልጠና መስጠት…
Read More