Christiantadele

በእስር ላይ የነበሩት አቶ ክርስቲያን ታደለ ያለመከሰስ መብት ተነሳ

በእስር ላይ የነበሩት አቶ ክርስቲያን ታደለ ያለመከሰስ መብት ተነሳ

የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባካሄደው ስብሰባ የአቶ ክርስቲያን ታደለን ያለመከሰስ መብትን  በሁለት ተቃውሞ እና በሁለት ድምጸ ተዐቅቦ አንስቷል። አቶ ክርስቲያን ታደለ ከሶስት ዓመት በፊት በተካሄደው ሀገር አቀፍ ምርጫ የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) ፓርቲን ወክለው ከቋሪት ወረዳ ተመርጠዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ሪፖርታቸውን ለምክር ቤቱ በሚያቀርቡበት ወቅት ጠንካራ ጥያቄዎችን በማንሳት እና ትችቶችን በመሰንዘር የሚታወቁት አቶ ክርስቲያን ታደለ ከስድስት ወራት በፊት ታስረዋል፡፡ ያለመከሰስ መብታቸው ሳይነሳ ላለፉት ስድስት ወራት በእስር ላይ የቆዩት አቶ ክርስቲያን ታደለ በዛሬው ዕለት ያለመከሰስ መብታቸው ተነስቷል፡፡ ሌላኛው የምክር ቤት አባል አቶ ደሳለኝ ጫኔ (ዶ/ር) ከሁለት ወራት በፊት ያለ መከሰስ መብታቸው ሳይነሳ በተመሳሳይ በእስር ላይ ያሉ ሲሆን እስካሁን ክስ ሳይመሰረትባቸው…
Read More