10
Sep
የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ባቀረበው ጥያቄና ከተለያዩ አካላት ጋር ባደረገው ጥረት፣ ከ600 በላይ ሰዎች ከእስር መፈታታቸውን ገልጿል። ኮሚሽኑ ባወጣው መግለጫ፣ በተለያዩ ወንጀሎች የተፈረደባቸው እና ጉዳያቸው በፍርድ ሂደት ላይ የሚገኙ ዜጎች ጉዳያቸው በልዩ ሁኔታ እንዲታይ ጥያቄ አቅርበዋል። ኢሰመኮም ይህንን ጥያቄ መነሻ በማድረግ ጉዳዩን ለመንግሥት ማቅረቡን አስታውቋል። ኮሚሽኑ እንደገለጸው፣ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጉዳዩን በአዎንታ ተቀብለው፣ የሕግ የበላይነትን በጠበቀ መልኩ ለሰላም፣ ለሀገራዊ መግባባትና ለዴሞክራሲ የሚያግዙ እርምጃዎች እንዲወሰዱ ለሚመለከታቸው የመንግሥት መዋቅሮች አቅጣጫ ሰጥተዋል ተብሏል። በዚህ መሠረት በተቀመጠው የሕግና የይቅርታ ሂደት መሠረት፣ በተለያዩ ወንጀሎች የተፈረደባቸው በይቅርታ እንዲፈቱ፣ በክስ ሂደት ላይ ያሉ ተከሳሾችም ክሳቸው ተቋርጦ ከእስር እንዲለቀቁ ተወስኗል ሲል ኢሰመኮ ገልጿል። ከእስር ከተለቀቁት…