Ethiopia

ራይላ ኦዲንጋ ለአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበርነት እንደሚወዳደሩ ገለጹ

ራይላ ኦዲንጋ ለአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበርነት እንደሚወዳደሩ ገለጹ

ኬንያዊው ራይላ ኦዲንጋ የወቅቱ የወቅቱን የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ሙሳ ፋኪ ማሃማትን ለመተካት በሚደረገው ምርጫ ላይ መወዳደር እንደሚፈልጉ ተናግረዋል፡፡ ከፈረንጆቹ 2017 ጀምሮ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር የሆኑት ሙሳ ፋኪ መሃማት የስልጣን ጊዜያቸው የፊታችን ሐምሌ ያበቃል፡፡ ይህን ተከትሎም ሙሳ ፋኪ መሀማትን ለመተካት ሀገራት ከወዲሁ እጩዎቻቸውን እያቀረቡ ሲሆን ኬንያዊው ተቃዋሚ ፖለቲከኛ ራይላ ኦዲንጋ ለአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበርነት እንደሚወዳደሩ አስታውቀዋል፡፡ ራይላ ኦዲንጋ ለዚህ እንዲረዳቸው የቀድሞ የናይጀሪያ ፕሬዝዳንት እና የአፍሪካ ህብረት የአፍሪካ ቀንድ መልዕክተኛ ኦሊሶጎኖ ኦባሳንጆ ሀገራትን እንዲያሳምኑለት እንደመረጣቸውም ተናግሯል፡፡ የኬንያ ፕሬዝዳንት ለመሆን አራት ጊዜ ተወዳድረው የተሸነፉት ራይላ ኦዲንጋ በቀጣይ ግንቦት በሚደረገው ምርጫ ለማሸነፍ የተወሰኑ ሀገራትን ለማሳመን ጥረት መጀመራቸውን ቢቢሲ ዘግቧል፡፡ ይሁንና ራይላ ኦዲንጋ…
Read More
የአፍሪካ ህብረት ሳይጋበዙ ጉባኤውን ለመሳተፍ የሚመጡ ሰዎችን አስጠነቀቀ

የአፍሪካ ህብረት ሳይጋበዙ ጉባኤውን ለመሳተፍ የሚመጡ ሰዎችን አስጠነቀቀ

የአፍሪካ ህብረት አባል ሀገራት ውጭ ጉዳይ ሚንስትሮች የሚሳተፉበት 44ኛው የአፍሪካ ህብረት ስራ አስፈጻሚዎች ምክር ቤት ስብሰባ በአዲስ አበባ በመካሄድ ላይ ነው። የህብረቱ የመሪዎች ጉባኤ ደግሞ የፊታችን ቅዳሜ እና እሁድ የሚካሄድ ሲሆን በዚህ ጉባኤ ላይ ለመሳተፍ ለሚመጡ ታዛቢ ሀገራት ማስጠንቀቂያ አውጥቷል፡፡ ህብረቱ ባወጣው መግለጫ በታዛቢነት እንዲሳተፉ ከተጋበዙ ሀገራት እና ተቋማት ውጪ የሚመጡ ተሳታፊዎችን እንደማያስተናግድ አስጠንቅቋል፡፡ 37ኛው የህብረቱ መሪዎች እና 44ኛው የህብረቱ ስራ አስፈጻሚ ምክር ቤት ጉባኤን በታዛቢነት እንዲሳተፉ ከተፈቀደላቸው ሀገራት እና ተቋማት ውጪ እንዳይመጡ እና ፈቃድ የተሰጣቸው ደግሞ ከአንድ ተወካይ በላይ እንዳይመጡ ሲልም ህብረቱ አሳስቧል፡፡ ከዚህ በፊት በአፍሪካ ህብረት ጉባኤዎች ላይ በታዛቢነት እንዲሳተፉ ፈቃድ የተሰጣቸው ሀገራት እና ተቋማትም ፈቃዳቸውን እንዲያድሱ ሲልም…
Read More
የጀርመኑ ናቡ የተሰኘው የአካባቢ ጥበቃ ተቋም የአፍሪካ ቢሮውን በኢትዮጵያ ከፈተ

የጀርመኑ ናቡ የተሰኘው የአካባቢ ጥበቃ ተቋም የአፍሪካ ቢሮውን በኢትዮጵያ ከፈተ

ከ125 ዓመት በፊት የተመሰረተው የጀርመኑ የተፈጥሮ እና ብዝሀ ህይወት ጥበቃ ተቋም (ናቡ) የአፍሪካ ቢሮውን በአዲስ አበባ ከፍቷል፡፡ የናቡ ፕሬዝዳንት ጆርግ አንድሪያስ ክሩገር እንዳሉት ኢትዮጵያ የብዝሃ ህይወት ሀብት በብዛት ከሚገኙባቸው ሀገራት መካከል አንዷ በመሆኗ እና ከአፍሪካ ጋር ለሚኖረን ግንኙነት መግቢያ በመሆኗ ቢሯቸውን በአዲስ አበባ ለመክፈት እንደወሰኑ ተናግረዋል፡፡ ኢትዮጵያን ጨምሮ በሌሎች የአፍሪካ ሀገራት እና ተቋማት ጋር ያለንን ግንኙነት በማቀላጠፍ ተጨማሪ የተፈጥሮ እና ብዝሃ ህይወት ጥበቃ ስራዎችን ለማስራት ቢሯችንን በአዲስ አበባ ለመክፈት አነሳስቶናልም ብለዋል፡፡ ከአንድ ክፍለ ዘመን በላይ ያስቆጠረው ይህ የተፈጥሮ እና ብዝሃ ህይወት ጥበቃ ተቋም በአውሮፓ፣ እስያ እና አፍሪካ ሀገራት ጋር በጋራ እየሰራ መሆኑን አስታውቋል፡፡ በአፍሪካ ኢትዮጵያን ጨምሮ በ7 ሀገራት ላይ እየሰራ…
Read More
በደላንታ ኦፓል በማውጣት ላይ እያሉ የተቀበሩ 20 ወጣቶችን ለማትረፍ ህዝቡ ሌት ተቀን እየቆፈረ ነው ተባለ

በደላንታ ኦፓል በማውጣት ላይ እያሉ የተቀበሩ 20 ወጣቶችን ለማትረፍ ህዝቡ ሌት ተቀን እየቆፈረ ነው ተባለ

በአማራ ክልል ደቡብ ወሎ ዞን ደላንታ ወረዳ 018 ቀበሌ ልዩ ስሙ አለኋት ተብሎ በሚጠራ ስፍራ ነበር ኦፓል ማዕድን በማውጣት ላይ የነበሩ ወጣቶች መውጫ ስፍራ በአለት የተደፈነባቸው፡፡ በማህበር ተደራጅተው ኦፓል እንዲያወጡ የተደራጁት እነዚህ ወጣቶች ቁጥራቸው 20 ሲሆን ከመሩት በህይወት ለማትረፍ የአካባቢው ማህበረሰብ ሌት ተቀን በፈረቃ እየቆፈረ መሆኑን የዞኑ መንግስት ኮሙንኬሽን መምሪያ ሃላፊ አቶ እያሱ ለአልዐይን ተናግረዋል፡፡ እንደ አቶ እያሱ ገለጻ ከሆነ ወጣቶቹ ሌሊት ላይ ማዕድኑን ለማውጣት እየቆፈሩ እያሉ መውጫቸው በዓለት የተዘጋ ሲሆን በአካባቢው የነበሩ በተመሳሳይ ስራ ላይ የተሰማሩ ወጣቶች ጉዳዩን ለህዝብ አሳውቀዋል፡፡ ጥር 30 ቀን የተከሰተው ይህ አደጋ ከመሬት ውስጥ ባለው ዋሻ ውስጥ ያሉትን ወጣቶች የደላንታ ወረዳ እና የአካባቢው ማህበረሰብ በዘመቻ…
Read More
ኢትዮጵያ የመኖሪያ ፈቃድ የሌላቸው የውጭ ሀገራት ዜጎች መመዝገቢያ ጊዜን አራዘመች

ኢትዮጵያ የመኖሪያ ፈቃድ የሌላቸው የውጭ ሀገራት ዜጎች መመዝገቢያ ጊዜን አራዘመች

የኢትዮጵያ ኢሚግሬሽንና የዜግነት አገልግሎት ከሁለት ሳምንት በፊት ባወጣው መግለጫ የውጭ ሀገር ዜጎች ሀሰተኛ ሰነዶችን ተጠቅመው ወደ ሀገር ውስጥ መግባታቸውን ደርሼበታለሁ ብሎ ነበር፡፡ የኢሚግሬሽንና የዜግነት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ሰላማዊት ዳዊት በሰጡት መግለጫ በርካታ የውጭ ሀገር ዜጎች ሀሰተኛ ቋሚ የመኖሪያ ፈቃድ፣ ሀሰተኛ ጊዚያዊ የመኖሪያ ፈቃድ፣ ሀሰተኛ ፓስፖርት፣ ሀሰተኛ ቪዛ እና ሀሰተኛ ሰነድ አዘጋጅተው በሀገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች እየኖሩ ይገኛል ብለዋል። በተደረገው የማጣራት ስራ ከ18 ሺህ በላይ ሀሰተኛ ጊዚያዊ የመኖሪያ ፈቃድ፣ ከ1 ሺህ 500 በላይ ሀሰተኛ ቪዛ እና ከአንድ ሺህ 800 በላይ የትውልደ ኢትዮጵያዊ መታወቂያን ያሰሩ ዜጎች በሀገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች መገኘታቸውንም ዳይሬክተሯ ተናግረዋል። በመሆኑም ህገወጥ ሰነድ ያለቸው ዜጎች ከጥር እስከ ጥር 30 ቀን 2016…
Read More
ኢትዮጵያ የሳሞአ ስምምነትን እንድትሰርዝ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ጠየቀ

ኢትዮጵያ የሳሞአ ስምምነትን እንድትሰርዝ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ጠየቀ

የኢትዮጵያ የሀይማኖት ተቋማት ጉባኤ እንዳስታወቀው ኢትዮጵያ በአውሮፓ ኅብረት፣ አፍሪካ፣ ካሪቢያን እና ፓስፊክ ሀገራት መካከል የተፈረመውንና የሳሞአ ስምምነት በመባል የሚታወቀውን የንግድና የኢኮኖሚ አጋርነት ስምምነትን ውድቅ እንድታደርግ ጠይቋል፡፡ ተቋሙ ይህ ስምምነት የተጠቀሰው የወሲብና የስነ ተዋልዶ ጤና እና መብቶች በሚል ዘርፍ የተደረገው ስምምነት ከግብረሰዶም መብቶች፤ ከፆታ መቀየር፤ ከጽንስ ማቋረጥ እንዲሁም የወሲብ ንግድን የሚያበረታታ እንደሆነ አስታውቋል፡፡ በስምምነቱ የአፍሪካ ፕሮቶኮል አንቀፅ 40.6 ላይ በአህጉሪቱ ለሚገኙ ልጆችና ታዳጊዎች ሁሉን አቀፍ የወሲብ ትምህርት የተባለ እጅግ አደገኛ ልቅ የወሲብ ትምህርት እንዲማሩ የሚያስገድድ በመሆኑ እንደሚቃወመውም ገልጿል፡፡ ሌላኛው ተቋሙ የተቃወመው የፆታ ትንኮሳን ማስቀረት በሚል የተቀመጠው ይዘት በጣም አሻሚ የሆነ ግብረሰዶማዊ አስተሳሰቦችን ለማስረፅ እንዲረዳው በሰነዱ በበርካታ ክፍሎች ውስጥ " አካታች "…
Read More
አሜሪካን ሆስፒታል-ዱባይ በኢትዮጵያ ቢሮውን እንደሚከፍት አስታወቀ

አሜሪካን ሆስፒታል-ዱባይ በኢትዮጵያ ቢሮውን እንደሚከፍት አስታወቀ

ድርጅቱ ከኢትዮጵያ በተጨማሪ በአፍሪካና በምስራቅ አውሮፓ ሀገራት ውስጥ 30 ወኪል ቢሮዎችን እከፍታለሁ ብሏል፡፡ ሪቭኤክሴል እና አሜሪካን ሆስፒታል ዱባይ ከሰሃራ በታች ባሉ ሀገራት የጤና አገልግሎት ተደራሽነትን ለማስፋት ስትራቴጂያዊ አጋርነትን እንደፈጠሩ አስታውቋል፡፡ አሜሪካን ሆስፒታል-ዱባይ በአፍሪካና ምስራቅ አውሮፓ 30 ወኪል ቢሮዎችን የመክፈት ዕቅዱን ያስጀመረ ሲሆን በዱባይ ጤና ባለስልጣን ዕውቅና ያላቸው 3 የህክምና ቱሪዝም ቢሮዎችን በናይጄርያ የተለያዩ ከተሞች ከፍቷል፡፡ በዓለምአቀፍ የንግድ መፍትሄዎች መሪ ተዋናይ የሆነው ሪቭኤክሴል ዓለምአቀፍ ከሰሀራ በታች ባሉ የአፍሪካ ሀገራትን የጤና አገልግሎት ተደራሽነት ለማሳደግ ያለውን ቁርጠኝነት በማጠናከር ከአሜሪካን ሆስፒታል-ዱባይ ጋር የለውጥ ስትራቴጂያዊ አጋርነቱን በይፋ አሳውቋል፡፡ የአሜሪካን ሆስፒታል-ዱባይ ይህንን ያረጋገጠው በ30 ወሳኝ የአፍሪካና የምስራቅ አውሮፓ ከተሞች የወኪል ቢሮዎች የማስፋፍያ ዕቅዱ አካል ሆኖ በናይጄርያ…
Read More
ደብረጽዮን ገ/ሚካኤል ከአራት ዓመት በኋላ ወደ አዲስ አበባ መጡ

ደብረጽዮን ገ/ሚካኤል ከአራት ዓመት በኋላ ወደ አዲስ አበባ መጡ

የትግራይ ክልል የቀድሞ ፕሬዝዳንት ደብረጽዮን ገ/ሚካኤል ከአራት ዓመት በኋላ ወደ አዲስ አበባ መጡ:: ደብረጽዮን ገብረሚካኤል ኢትዮጵያ ለዓመታት ወደ ጦርነት እንድተገባ የተገደደችበትን የሀገር መከላከያ ሰራዊት ሰሜን እዝ እሳቸው የሚመሩት የትግራይ ልዩ ሀይል እንዲያጠቃ ማድረጋቸው አይዘነጋም፡፡ ከአንድ ሚሊዮን በላይ ኢትዮጵያዊያን የተገደሉበት እና 28 ቢሊዮን ዶላር የሚያወጣ ንብረት የወደመበት ይህ ጦርነት ከአንድ ዓመት በፊት በአፍሪካ ህብረት አደራዳሪነት በደቡብ አፍሪካ ፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት ከተፈረመ በኋላ ቆሟል፡፡ ደብረጽዮን ገብረሚካኤል በዛሬው ዕለት ከአራት ዓመት በኋላ ከመቀሌ ወደ አዲስ አበባ የመጡ ሲሆን ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ጋር ፊት ለፊት ተገናኝተዋል፡፡ ደብረጽዮን እና ሌሎች የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ኃላፊዎች ከጠቅላይ ሚኒስትር አብይ ጋር በአዲስ አበባ በፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት አፈጻጸም…
Read More
በኢትዮጵያ የሚገኘው ባለ ጥቁር ጎፈር አንበሳ የመጥፋት አደጋ ተጋርጦበታል ተባለ

በኢትዮጵያ የሚገኘው ባለ ጥቁር ጎፈር አንበሳ የመጥፋት አደጋ ተጋርጦበታል ተባለ

የኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ጥበቃ ባለስልጣን እንዳስታወቀው የኢትዮጲያው ጥቁር ጎፈር አንበሳ ከጊዜ ወደ ጊዜ ቁጥሩ እየተመናመነ በመምጣቱ የመጥፋት አደጋ ተጋረጦበታል ተብሏል፡፡ በባለስልጣኑ የዱር እንስሳት ህገወጥ ዝውውር ቁጥጥር ከፍተኛ ባለሙያ የሆኑት አቶ ዳንኤል ጳውሎስ እንደተናገሩት ህገወጥ የነዋሪዎች ሰፈራ፣ የደን ጭፍጨፋ መኖር፣ የእርሻ ስራ እና  ግጦሽ  መበራከት የእንስሳቶቹ ስፍራ እንዲወድም ያደረጉ ዋና ዋና ምክንያቶች ናቸው። በዚህም አንበሳን ጨምሮ የዱር እንስሳት የሚፈልጉትን ምግብ እንዳያገኙና በምግብ ሰንሰለት ውስጥ ችግር እንዲፈጠር ብሎም ለህገወጥ አደን  በስፋት ተጋላጭ እንዲሆኑ አድርጓቸዋል ሲሉ አክለዋል። በአፍሪካ ቀንድ አካባቢ የተለየ የአንበሳ ዝርያ ነው ተብሎ የሚታወቀው እና የመጥፋት አደጋ ያጠላበት የጥቁር ጎፈር አንበሳ  ቆዳም በአብዛኛው  በኬንያ ፣በሱዳን እና በደቡብ ሱዳን በኩል የህገወጥ ዝውውር …
Read More
አሜሪካ በመርዓዊ ከተማ የተፈጸመው የንጹሃን ግድያ በገለልተኛ ወገን እንዲመረመር ጠየቀች

አሜሪካ በመርዓዊ ከተማ የተፈጸመው የንጹሃን ግድያ በገለልተኛ ወገን እንዲመረመር ጠየቀች

ከአማራ ክልል ዋና ከተማ ከሆነችው ባህርዳር በቅርብ ርቀት ላይ በምትገኘው መራዊ ከተማ ባሳለፍነው ሳምንት ከሰሞኑ በመንግስት የጸጥታ ሀይሎች እና ፋኖ ታጣቂዎች መካከል ከባድ ውጊያ ተቀስቅሶ ነበር፡፡ በዚህ ውጊያ ምክንያት የፋኖ ታጣቂዎች የመራዊ ከተማን ተቆጣጥረው የነበረ ቢሆንም በኋላ ለቀው መሄዳቸውን ተከትሎ ወደ ከተማው የገባው የሀገር መከላከያ ሰራዊት ከ50 በላይ የከተማዋ ነዋሪዎችን እንደገደሉ ቢቢሲ ነዋሪዎችን አነጋግሮ ዘግቧል፡፡ እንደ ነዋሪዎቹ አስተያየት ከሆነ የሀገር መከላከያ ሰራዊት ነዋሪዎቹን ከመንገድ ላይ እና መኖሪያ ቤታቸው በማሰባሰብ ገድለዋቸዋል፡፡ በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኤርቪን ማሲንጋ በኢምባሲው ማህበራዊ ትስስር ገጾች ላይ ባወጡት መግለጫ በመርዓዊ ከተማ የተፈጸመው የንጹሃን ዜጎች ግድያ እንደሚያሳስባቸው፣ ጉዳዩ በገለልተኛ አካል እንዲመረመር ጠይቀዋል፡፡ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በአማራ እና ኦሮሚያ…
Read More