HIVAIDS

በትግራይ ክልል የኤች አይ ቪ ስርጭት ወደ ከፋ ደረጃ መሻገሩን ክልሉ አስታወቀ

በትግራይ ክልል የኤች አይ ቪ ስርጭት ወደ ከፋ ደረጃ መሻገሩን ክልሉ አስታወቀ

በትግራይ ክልል ባለው አሁናዊ ሁኔታ የህጻናት የተጓዳኝ በሽታ መድኃኒት እና   የኤች አይ ቪ መመርመሪያ ኪት  እጥረት መኖሩን የትግራይ ክልል ጤና ቢሮ አሰታወቀ፡፡ የትግራይ ክልል ጤና ቢሮ የዘርፈ ብዙ ምላሽ የኤች አይ ቪ  መከላከል እና መቆጣጠር ስራ ሂደት አስተባባሪ የሆኑት አቶ ፍሥሀ ብርሃነ ለትግራይ ቴሌቪዥን እንደተናገሩት ከሶስት አመት በፊት በኤች አይቪ ስርጭት እና መቆጣጠር የተሻለ ጤና  አፈፃፀም ነበረው ብለዋል። አሁን ላይ ግን  የኤችአይቪ ስርጭቱ ወደ ከፋ ሁኔታ ውስጥ ገብቷል። በፀጥታ እጦት ወቅት በርካታ ሴቶች እና እናቶች የመደፈር አደጋ ተጋላጭ በመሆናቸው  እንዲሁም መድኃኒት ተጠቃሚ የነበሩ ሰዎችም በመድሀኒት እጥረት በማቋረጣቸው  ለበሽታው ስርጭት መስፋፋት ዋነኛ ምክንያቶች ናቸው ብለዋል፡፡ ከዚህ ቀደም የክልሉ ጤና ቢሮ ባደረገው ጥናት…
Read More
በትግራይ ክልል የኤች አይ ቪ ቫይረስ ሥርጭት አስደንጋጭ መሆኑ ተገለጸ

በትግራይ ክልል የኤች አይ ቪ ቫይረስ ሥርጭት አስደንጋጭ መሆኑ ተገለጸ

በትግራይ ክልል ከ100 ሰዎች ውስጥ 10ሩ የኤችአይቪ ኤድስ ቫይረስ በደማቸው ውስጥ አለባቸው ተብሏል፡፡ በትግራይ ክልል ከሰሜኑ ጦርነት በኋላ የኤች አይ ቪ ቫይረስ ሥርጭት በአስደንጋጭ ሁኔታ ጨምሯል የተባለ ሲሆን ስርጭቱ በ10 ነጥብ 5 በመቶ መጨመሩን የክልሉ ጤና ቢሮ ለአዲስ ማለዳ ገልጿል፡፡ የትግራይ ክልል ጤና ቢሮ ምክትል ኃላፊ ዶክተር ርእየ ኢሳያስ በሰሜኑ ጦርነት ወቅትም ሆነ ከጦርነቱ በኋላ ልቅ በሆኑ ወሲባዊ ጥቃቶች ምክንያት የቫይረሱ ስርጭት በከፍተኛ ሁኔታ መጨመሩን ተናግረዋል፡፡ በዚህም በክልል በሚገኙ 37 የጤና ተቋማት በተደረገ የኤች አይ ቪ ኤድስ ምርመራ፤ እስከ ጦርነቱ ጅማሮ 1 ነጥብ 8 በመቶ የነበረው የቫይረሱ ስርጭት አሁን ላይ 10 ነጥብ 5 በመቶ መድረሱን አስረድተዋል፡፡ በክልሉ ከ120 ሺሕ በላይ…
Read More