EthioNegari

የአድማስ ዲጂታል ሎተሪ ሽልማት ወደ አራት ሚሊዮን አደገ

የአድማስ ዲጂታል ሎተሪ ሽልማት ወደ አራት ሚሊዮን አደገ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ሎተሪ አስተዳደር በቅርቡ የጀመረው አድማስ ድጅታል ሎተሪ የሽልማት መጠኑን ማሳደጉን ገልጿል፡፡ አድማስ ድጅታል ሎተሪ ከመስከረም 2015 ዓ.ም ጀምሮ ለአንደኛ አሸናፊ አንድ ነጥብ አምስት ሚሊዮን ብር በመሸለም ነበር የጀመረው፡፡ በመቀጠልም የሽልማት መጠኑን ወደ ሶስት ሚሊዮን ብር ከፍ የተደረገው አድማስ ድጅታል ሎተሪ ደንበኞች የእጅ ስልካቸውን በመጠቀም በሶስት ብር እና በአምስት ብር የሎተሪ እጣ የሚቆርጡበት የሎተሪ ስርዓት ነው፡፡ በደምበኞች አስተያየት መሰረት ቀደም ሲል የነበበረውን የዕጣ ሽልማት የአንደኛው ዕጣ 4 ሚሊዮን ብር፣ የሁለተኛው ዕጣ 2 ሚሊዮን ብር የሶስተኛው ዕጣ 1 ሚሊዮን ብር በማድረግ ተደርጓል ተብሏል፡፡ እንዲሁም ደንበኞች ከሰኔ 24 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ አንድ እጣ በ10 ብር በ605 ላይ ማንኛውም ፊደል በመላክ…
Read More
ፓስተር ዮናታን የ77 ሚሊዮን ብር የባንክ እዳ እንዳለባቸው ተገለጸ

ፓስተር ዮናታን የ77 ሚሊዮን ብር የባንክ እዳ እንዳለባቸው ተገለጸ

በፓስተር ዮናታን ንብረቶች ላይ ንብ ባንክ የሐራጅ ሽያጭ ማስታወቂያ አወጣ። ንብ ኢንተርናሽናል ባንክ አ.ማ ላበደረው ንብረት የሐራጅ ሽያጭ አውጥቷል። ንብ ባንክ በሰኔ 22 ቀን የአዲስ ዘመን ጋዜጣ ላይ ባስወጣው የሀራጅ ሽያጭ ማስታወቂያ መሰረት በአዲስ አበባ እና ሀዋሳ ባሉ የመኖሪያ ቤት እና ንግድ ድርጅቶችን ለመሸጥ ለተጫራጮች ማስታወቂያ አውጥቷል። አበዳሪው ወይም የመያዢያ ሰጪ ስም፣ አበዳሪው ቅርንጫፍ፣ የሚሸጠው ንብረት ዓይነትና የሚገኝበት ቦታ፣ የሐራጁ መነሻ በብር፣ የሐራጁ ቀንና ሰዓትም ተገልጿል። ጨረታ ከወጣባቸው ንብረቶች መካለም አቶ ዮናታን አኪሊሉ አንጀሎ አራት ኪሎ ፕሪሚየም፣ በስማቸው የተመዘገበ ሀዋሳ ምሥራቅ ከተማ የሚገኝ 400 ሜትር ካሬ ቦታ ያለው ባለ 3 ወለል መኖሪያ ቤት ሲሆን የሐራጁ መነሻ ዋጋ 22 ሚሊዮን ብር…
Read More
በኢትዮጵያ በአንድ ዓመት ውስጥ ብቻ 200 ሺህ ዜጎች መሞታቸው ተገለጸ

በኢትዮጵያ በአንድ ዓመት ውስጥ ብቻ 200 ሺህ ዜጎች መሞታቸው ተገለጸ

በፈረንጆች 2022 ብቻ በኢትዮጵያ በረሃብና በበሽታ ከ200 ሺሕ በላይ ሰዎች መሞታቸው ተገለጸ በፈረንጆቹ 2022 ዓመት ብቻ በኢትዮጵያ በረሃብ እና ከረሀብ ጋር ተያይዘው ከሚከሰቱ በሽታዎች በተያያዘ ከ200 ሺሕ በላይ ሰዎች ሕይወታቸው ማለፉ ተገልጿል። በዚህም በኢትዮጵያ በረሃብና ተያያዥ በሽታዎች የሚሞቱ ሰዎች ቁጥር በየዓመቱ እየጨመረ መምጣቱ የተጠቀሰ ሲሆን፤ ዓለም አቀፍ ድርጅቶች ለእርዳታ የሚልኩት እህል ለግል ጥቅም ሲውል እና በገበያ ላይ ሲሸጥ አረጋግጠናል በሚል የሰብዓዊ እርዳታ መቋረጡም፣ በዚህ ወቅት በረሃብ እና በበሽታ ለሞቱ ሰዎች እንደ ዋና ምክንያት ተጠቅሷል። እንዲሁም በዚያው ዓመት በተፈጠሩ ግጭቶች የተገደሉ ሰዎች ቁጥር ከ100 ሺሕ በላይ መሆኑን ግሎባል ፒስ ኢንዴክስ በድኅረ ገጹ አስነብቧል፡፡ ከሰሃራ በታች ባሉ የአፍሪካ አገራት የእርስ በርስ ግጭት…
Read More

አሜሪካ በኢትዮጵያ ጦርነት 350 ሺህ ሰዎች መገደላቸውን ገለጸች

አሜሪካ ኢትዮጵያን ከሰብዓዊ መብት ጥሰት ፈጻሚ ሀገርነት ዝርዝር ውስጥ ሰርዛለች። በሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት መቀስቀሱን ተከትሎ ነበር አሜሪካ ኢትዮጵያን የከፋ የሰብዓዊ መብት ጥሰት ፈጻሚ ሀገር ዝርዝር ውስጥ የመዘገበቻት። ይህን ተከትሎም ዋሽንግተን ለኢትዮጵያ ታደርጋቸው የነበሩ የልማት ስራዎች ድጋፎችን አቋርጣ ቆይታለች። እንደ ፎሬይን ፖሊሲ ዘገባ ከሆነ አሜሪካ ኢትዮጵያ አሁን ላይ የከፋ የሰብዓዊ መብት ጥሰት የሚፈጸምባት ሀገር አይደለችም የሚል አቋም ላይ ደርሳለች። በኮሮና ቫይረስ፣ በጦርነት እና በዓለም አቀፍ ንግድ መቀዛቀዝ ምክንያቶች ኢትዮጵያ እንደ ሌሎች ሀገራት የብድር መክፈያ ጊዜ ሽግሽግ እንዲደረግ አስቀድማ ጠይቃ ነበር። ይሁንና አሜሪካ በኢትዮጵያ ላይ በጣለችው እገዳ ምክንያት ዓለም ባንክ እና አይኤምኤፍ ለብዙ በማደግ ላይ ላሉ ሀገራት ያደረጉትን የገንዘብ ድጋፍ ለኢትዮጵያ ማድረግ…
Read More
ለ15ኛ ጊዜ ሎተሪ የደረሳቸው የጎንደሩ እድለኛ አባት

ለ15ኛ ጊዜ ሎተሪ የደረሳቸው የጎንደሩ እድለኛ አባት

ግለሰቡ በአንድ ዓመት ውስጥ የገናን እና ፋሲካ በዓል ሎተሪን አሸንፈዋል አቶ መሃመድ አህመድ አህመድ ይባላሉ፤ተወልደው ያደጉት ጎንደር ነው፡፡ አቶ መሃመድ ሙሉ ስማቸው መሃመድ አህመድ ቢሆንም በተደጋጋሚ ሎተሪ ስለጎበኛቸው የአባታቸው ስም ወደ ሎተሪ ተቀይሮ በሚኖሩበት ከተማ መሃመድ ሎተሪ እየተባሉ በመጠራት ላይ ናቸው፡፡ አቶ መሃመድ ሎተሪ 15 ጊዜ የሎተሪ እድል አሸናፊ መሆናቸውን የብሔራዊ ሎተሪ አስተዳደር መረጃ ያመላከታል፡፡ ከ1977 አመት ጀምሮ እስከ 2007 ዓ.ም ድረስ ሎተሪ ቆርጠው ያጡት ብር እንደሌለ እኝህ አባት ይናገራሉ፡፡ አቶ መሃመድ ከ500 ብር ጀምሮ እስከ 75ሺህ ብር ድረስ አሸናፊ ሆነዋል፡፡ የእኝህ አባት እድለኝነት የሚያስገርመው ደግሞ የገና ሎተሪ እጣ አሸናፊ ሆነው በዛው አመት በፋሲካም አሸናፊ መሆናቸው ነው፡፡ በሎተሪ ተስፋ ቆርጠው…
Read More
ኢትዮጵያ ብሪክስን ለመቀላቀል ጥያቄ አቀረበች

ኢትዮጵያ ብሪክስን ለመቀላቀል ጥያቄ አቀረበች

የኢትዮጵያ መንግስት በፈረንጆቹ 2009 የተመሰተረተውንና ብራዚል፣ ሩሲያ፣ ህንድ፣ ቻይና እና ደቡብ አፍሪካ በጥምረት የመሰረቱትን "ብሪክስ" (BRICS) የተሰኘ የአገራት ስብስብ ለመቀላቀል ጥያቄ ማቅረቧን አስታውቃለች፡፡ የውጭ ጉዳይ ሚንስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር መለስ አለም በሳምንታዊ መግለጫቸው እንደገለጹት ኢትዮጵያ የብዙ አለማቀፍ ተቋም መስራች መሆኗን ጠቅሰው የተባበሩት መንግስታት፣ የአፍሪካ ህብረት እና የገለልተኛ አገሮች ንቅናቄና መስራችና ጠንካራ ተሳትፎ ያላት አገር ናት ብለዋል፡፡ በመሆኑም አሁን እየተለወጠ ባለው የዓለም ሁኔታና የኃይል አሰላላፍ አንጻር የኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅምን ለማረጋገጥ የሚረዱ ዓለም አቀፍ ተቋማት አባል በመሆን መንግሥት እንደሚሠራ ተናግረዋል። "ከእነዚህ ተቋማት መካከል አንዱ 'ብሪክስ' ነው ፣ ከኢትዮጵያ መንግስት በኩል ጥያቄ ቀርቧል፣ በጎ ምላሻ ያገኛል ብለን እናስባለን ፣ ክትትልም የምናደርግበትም ይሆናል" ብለዋል…
Read More
ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ በአንዋር ሶሳ ምትክ አዲስ ሀላፊ ሾመ

ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ በአንዋር ሶሳ ምትክ አዲስ ሀላፊ ሾመ

ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ አዲስ ሀላፊ ተሾመለት። ላለፉት ሁለት ዓመታት ሳፋሪኮም ኢትዮጵያን በሀላፊነት ሲመሩ የቆዩት አንዋር ሶሳ መልቀቃቸው ይታወሳል። ድርጅቱ ባሳለፍነው ሳምንት እንዳለው አንዋር ሶሳ ከቀጣዩ ወር ጀምሮ በሀላፊነታቸው እንደማይቀጥሉ አስታውቋል። ይህን ተከትሎም የቀድሞው የኤምቲኤን ኡጋንዳ ሀላፊ የነበሩት ዊም ቫንሄልፑት አንዋር ሶሳን ተክተው ወደ አዲስ አበባ እንደሚመጡ ሮይተርስ ዘግቧል። በዜግነት ቤልጂየማዊ የሆኑት አዲስ የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ስራ አስፈጻሚ ከቀጣዩ መስከረም ጀምሮ ድርጅቱን መምራት ይጀምራሉ። ሳፋሪሎም ኢትዮጵያ በኤምፔሳ አማካኝነት ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የሞባይል ፋይናንስ አገልግሎት ለመስጠት ፈቃድ ማግኘቱ ይታወሳል። በፈረንሳይ የኢትዮጵያ የቀድሞ አምባሳደር የሆኑት ሔኖክ ተፈራን የውጭ ግንኙነት ሀላፊ አድርጎ የሾመው ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ከሶስት ሚሊዮን በላይ ደንበኞች ማፍራቱንም አስታውቋል። ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ከኢትዮ ቴሌሎም ብርቱ…
Read More
ኢትዮጵያ የቀድሞ የባህር ሀይል የውጊያ ጀልባዎችን ለግዳጅ ዝግጁ አደረገች

ኢትዮጵያ የቀድሞ የባህር ሀይል የውጊያ ጀልባዎችን ለግዳጅ ዝግጁ አደረገች

ወደብ አልባ የሆነችው የኢትዮጵያ መከላከያ ዋና አዘዥ ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ፈጣን ተዋጊ ጀልባዎችን ጎብኝተዋል፡፡ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ የአየር ኃይል አቪዬሽን ከባድ ጥገና ማዕከል ወደ አገልግሎት የመለሳቸውን ፈጣን ተዋጊ ጀልባዎችን እንደጎበኙ የሀገር መካለከያ በፌስቡክ ገጹ አስታውቋል። ተዋጊ ጀልባዎቹ በቀድሞ የኢትዮጵያ ባሕር ኃይል አገልግሎት የሠጡ ሲሆን ዳግም የባሕር ኃይሉን ዝግጁነት ያጠናክራሉም ተብሏል። የአየር ኃይል አቪዬሽን ከባድ ጥገና ማዕከል ከ30 አመት በላይ ተገለው እና አገልግሎት መስጠት ያቆሙ ጀልባዎችን የፈጣን ተዋጊ ጀልባ ቴክኖሎጂ እና መሳሪያዎች በመግጠም ለግዳጅ ዝግጁ መደረጋቸውም ተገልጿል። ኢትዮጵያ የባህር ሀይልን እንዳዲስ በማደራጀት ላይ መሆኗን ከሁለት ዓመት በፊት መግለጿ ይታወሳል፡፡ የቀድሞ የኢትዮጵያ አካል የሆነችው ኤርትራ…
Read More
ኢትዮጵያን በመጎብኘት ላይ የነበረ ሩሲያዊ ዜጋ ህይወቱ አለፈ

ኢትዮጵያን በመጎብኘት ላይ የነበረ ሩሲያዊ ዜጋ ህይወቱ አለፈ

ግለሰቡ በኦሮሚያ ክልል ቢሾፍቱ ከተማን በመጎብኘት ላይ እያለ ህይወቱ ማለፉ ተገልጿል፡፡ የ55 ዓመት እድሜ እንዳለው የተገለጸው ይህ ሩሲያዊ በኦሮሚያ ክልል ቢሾፍቱ ከተማ ኩሪፍቱ ሀይቅ ላይ በመዋኘት ላይ እያሉ ህይወቱ አልፏል ተብሏል፡፡ በቢሾፍቱ ኩርፊቱ ሀይቅ በመዝናናት ላይ ከነበሩት የዉጭ ሀገር ዜጎች መካከል አንድ የሩሲያ ዜግነት ያለዉ የ 55 ዓመት ህይወቱ ማለፉን እሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አስታውቋል። የኮሚሽኑ የህዝብ ግንኙነት ባለሙያ አቶ ንጋቱ ማሞ እንደተናገሩት ግለሰቡን ለሞት ያበቃዉ በኩሪፍቱ ሀይቅ 150 ሜትር ጥልቀት ባለው ኩሪፍቱ ሀይቅ ዘልቆ በመዋኘት ላይ ሳለ ህይወቱ ማለፉን ተገልጿል፡፡ ግለሰቡ ባሳለፍነው እሁድ ሰኔ 18 ቀን 2015 ዓ.ም ለመዋኘት ወደ ሀይቁ ውስጠኛው ክፍል ከገባ በኋላ ሳይመለስ ቀርቷል…
Read More
ወይዘሪት ብርቱካን ሚዴቅሳ ከሀላፊነት ለቀቁ

ወይዘሪት ብርቱካን ሚዴቅሳ ከሀላፊነት ለቀቁ

ወይዘሪት ብርቱካን ሚዴቅሳ ከሀላፊነት ለቀቁ ከ2011 ዓ.ም ታህሳስ ወር ጀምሮ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዋና ሰብሳቢ ሆነው ስራ የጀመሩት ወይዘሪት ብርቱካን ሚዴቅሳ በጠየና ምክንያት የስራ መልቀቂያ ደብዳቤ ማስገባታቸውን ሰማያዊ ማረጋገጫ ባለው የፌስቡክ ገጻቸው ላይ ገልጸዋል፡፡ “ባለፉት  አራት አመት ከስድስት ወራት ሶስት ህዝበ ውሳኔዎችን እና አገራዊ ምርጫን በማካሄድ እና ፓለቲካ ፓርቲዎችን በማስተዳደር የተሰጡኝን ሃላፊነቶች ህጋዊነት ፍትሀዊነት እና ቅንነትን በተከተለ ሁኔታ ለማከናወን ስጥር ቆይቻለሁ” ብለዋል። “ሆኖም ጤናዬን በሚገባ ለመጠበቅ የረጅም ጊዜ እረፍት የሚያስፈልገኝ ሆኖ በመገኘቱ ከ ነሀሴ 1 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ቦርድ ሰብሳቢነቴ በገዛ ፍቃዴ  መልቀቄን ለተወካዮች ምክር ቤት አፈጉባኤ ጽህፈት ቤት ሰኔ 5 ቀን 2015 ዓ.ም አሳውቄያለሁ” ሲሉም…
Read More