EthioNegari

በህዳሴው ግድብ ግንባታ ወቅት 15 ሺህ ኢትዮጵያዊያን መሞታቸው ተገለጸ

በህዳሴው ግድብ ግንባታ ወቅት 15 ሺህ ኢትዮጵያዊያን መሞታቸው ተገለጸ

የውሀ እና ኢነርጂ ሚንስትር ሀብታሙ ኢተፋ ከሪፖርተር መጽሄት ጋር በነበራቸው ቃለ መጠይቅ ላይ እንዳሉት በታላቂ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ወቅት 15 ሺህ ዜጎች ህይወታቸውን አጥተዋል። ህይወታቸውን ካጡ ዜጎች መካከል የቀድሞው የግድቡ ግንባታ ፕሮጀክት ስራ አስኪያጅ ኢንጅነር ስመኘው በቀለ አንዱ ሲሆኑ ለብቻቸው መታሰቢያ ሀውልት እንደማይቆምላቸውም ሚንስትሩ ተናግረዋል። "የጸጥታ ሀይሎች፣ ሹፌሮች፣ ሰራተኞች እና ሌሎሽም የህብረተሰብ ክፍሎች ህይወታቸውን አጥተዋል ስለዚህ ይህ በሆነበት ሁኔታ ለግለሰቦች የተለየ መታሰቢያ ሀውልት የለም" ሲሉም ሚንስትሩ በቃለ መጠይቁ ወቅት ገልጸዋል። በግዝፈቱ ከአፍሪካ ቁጥር አንድ የሆነው የህዳሴው ግድብ በሚቀጥለው ሳምንት እንደሚመረቅ ይጠበቃል። ጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ (ዶ/ር) ከሰሞኑ በኢትቪ በተላለፈ ንግግራቸው ለግድቡ ግንባታ አስተዋጽኦ ያደረጉ አካላትን አመስግነዋል። የቀድሞ ጠቅላይ ሚንስትር…
Read More
ንግድ ባንክ ለዲያስፖራዎች 50 ቢሊዮን ብር ብድር ለመስጠት ዝግጁ መሆኑን ገለጸ

ንግድ ባንክ ለዲያስፖራዎች 50 ቢሊዮን ብር ብድር ለመስጠት ዝግጁ መሆኑን ገለጸ

ንግድ ባንክ ለዲያስፖራው ማኀበረሰብ 50 ቢሊዮን ብር የብድር አገልግሎት አዘጋጅቼ እየጠበቀ መሆኑን አስታውቋል። የባንኩ የብድር አገልግሎቱ ለኢንቨስትመንት፣ ለመኖሪያ ቤትና አውቶሞቢል ግዥ የቀረበ ነው ተብሏል። የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፕሬዚደንት አቶ አቤ ሳኖ ሰሞኑን በተባበሩት አረብ ኤምሬቶች ከሚኖሩ ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያን  የዲያስፖራ ማህበረሰብ አባላት ጋር ተወያይተዋል፡፡ በውይይቱ ወቅት ፕሬዚደንቱ እንዳስታወቁት ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያን  የዲያስፖራ ማህበረሰብ አባላት በአገር ውስጥ ለሚያካሄዱት የቢዝነስ እንቅስቃሴ፣ ለመኖሪያ ቤትና መሰል ፍላጎቶች የ50 ቢሊዮን ብር የብድር አገልገሎት ተመቻችቷል ብለዋል፡፡ የብድር አገልግሎቱ በተያዘው የ2024/25 በጀት ዓመት ተፈጻሚ እንደሚሆንም ፕሬዝዳንቱ ተናግረዋል፡፡ ባንኩ አገልግሎቱን ለማግኘት ጥያቄ ለሚያቀርቡ የዲያስፖራ ማህበረሰብ አባላት ቀልጣፋና ምቹ አሰራር እንደሚተገብርም አቶ አቤ አስታውቀዋል፡፡ ሙሉ ለሙሉ የመንግስት…
Read More
የካፒታል ገበያ ባለስልጣን በጋራ ኢንቨስትመንት ፈንዶች ላይ አዲስ መመሪያ አወጣ

የካፒታል ገበያ ባለስልጣን በጋራ ኢንቨስትመንት ፈንዶች ላይ አዲስ መመሪያ አወጣ

በአሁኑ ወቅት በካፒታል ገበያ ሥር በተለያዩ ዘርፎች አገልግሎት ለመስጠት 10 ተቋማት የፈቃድ ማመልከቻ አስገብተው እየተጠባበቁ እንደሚገኝ የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለስልጣን አስታውቋል። በባለስልጣን መስሪያ ቤቱ የምዝገባና ፈቃድ አሰጣጥ ኃላፊ አቶ እንድሪስ ሰልማን፤ በኢትዮጵያ ያለው የካፒታል ገበያ ገና በማደግ ላይ የሚገኝ መሆኑን ገልጸዋል። ሆኖም ከጊዜ ወደጊዜ ፍላጎቱ እየጨመረ እንደሚመጣ ገልጸው፤ ያንን ፍላጎት ለመሙላት የሚያስችል ተጨማሪ አገልግሎት ሰጪዎች ገበያውን ሊቀላቀሉ የሚችሉበት ዕድል እንዳለ ተናግረዋል። በዚህም ወደ 10 ተቋማት እንዲሁም በግለሰብ ደረጃ ደግሞ አንድ ሰው የኢንቨስትመንትና የሰነደ መዋዕለ ነዋይ አማካሪነትን ጨምሮ በተለያዩ ዘርፎች የፈቃድ ማመልከቻ በማስገባት እየተጠባበቁ እንደሚገኙ አስታውቀዋል። ያመለከተው አካል በሙሉ ፈቃድ ይሰጠዋል ማለት እንዳልሆነ የገለጹት ኃላፊው፤ "በተቀመጠው የፈቃድ አሰጣጥ መመሪያ መስፈርት መሰረት…
Read More
ኢትዮጵያ ግብጽን በስጋትነት እንደማትመለከታት ገለጸች

ኢትዮጵያ ግብጽን በስጋትነት እንደማትመለከታት ገለጸች

ግብፅ ህዳሴ ግድቡን በተመለከተ እያደረገች ያለችውን ጫና ኢትዮጵያ በስጋት አንደማትመለከተው የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በሰጠው ሳምንታዊ መግለጫ ግብፅ የታላቁ ህዳሴ ግድቡን በተመለከተ የዲፕሎማሲ ጫና ለመፍጠር የምታደርገው ጥረት ለኢትዮጵያ ስጋት አይሆንም ሲል ተናግሯል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር  ነቢያት ጌታቸው የግብፅ አካሄድ ስጋት የማይሆነው ከዚህ ቀደምም የነበረ ስለሆነ ነው ብለዋል። የህዳሴ ግድቡ ምርቃት መቃረቡን ያስታወሱት አምባሳደር  ነቢያት ጌታቸው የቅኝ ግዛት እሳቤዎች ተቀባይነት የላቸውም ብለዋል። በለፉት 14 ዓመታት በመላው ኢትዮጵያዊያን ድጋፍ ከፍተኛ መሰናክሎችን አልፎ ህዳሴ ግድቡ የመመረቅያው ዋዜማ ላይ እንገኛለን ያሉት አምባሳደሩ ምርቃቱንም ኢትዮጵያዊያን  እና የኢትዮጵያን በጎ የሚመኙ አብረውን የሚያከብሩት  ይሆናል ሲሉ አስረድተዋል፡፡ ለምርቃቱ በስም ያልዘረዘሯቸው እንግዶች እንደተጋበዙ…
Read More
ቢሊየነሩ አሊኮ ዳንጎቴ በኢትዮጵያ የአፈር ማዳበሪያ ፋብሪካ ለመገንባት ተስማማ

ቢሊየነሩ አሊኮ ዳንጎቴ በኢትዮጵያ የአፈር ማዳበሪያ ፋብሪካ ለመገንባት ተስማማ

የአፈር ማዳበሪያ ማምረቻ ኮምፕሌክስ የድርሻ ስምምነት መፈረሙን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ገልጸዋል፡፡ ፕሮጀክቱ በዓመት እስከ ሦስት ሚሊዮን ሜትሪክ ቶን ማዳበሪያ ማምረት የሚያስችል መሆኑንም ጠቅላይ ሚኒስትሩ ተናግረዋል፡፡ በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግ እና በዳንጎቴ ግሩፕ መካከል የማዳበሪያ ማምረቻ ኮምፕሌክስ የድርሻ ስምምነት መፈረሙን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ አስታውቀዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት፤ "ወደ ምግብ ዋስትና እና የግብርና ሽግግር በምናደርገው ጉዞ አንድ ሌላ እጥፋት ላይ በመድረሳችን ኢትዮጵያውያን ሁሉ እንኳን ደስ አለን!" ብለዋል። 2 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ኢንቨስትመንት የሚፈስበት ይህ ሜጋ ፕሮጀክት በዓመት እስከ ሦስት ሚሊዮን ሜትሪክ ቶን ማዳበሪያ የሚያመርት ሲሆን፤ "ይህም ኢትዮጵያን ከዓለም ግንባር ቀደም አምራቾች አንዷ ያደርጋታል" ብለዋል። "ፕሮጀክቱ በሀገር…
Read More
የክልል አየር ማረፊያዎች ዓለም አቀፍ በረራዎች ማስተናገድ ሊጀምሩ ነው

የክልል አየር ማረፊያዎች ዓለም አቀፍ በረራዎች ማስተናገድ ሊጀምሩ ነው

ዓለም አቀፍ በረራዎችን ከአዲስ አበባ ዓለም አቀፍ ኤርፖርት በተጨማሪ በሌሎች የክልል አየር ማረፊያዎች ማስተናገድ ሊጀመር መሆኑን የሲቪል አቪዬሽን ባለስልጣን አስታውቋል። ባለስልጣኑ የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዶ/ር አለሙ ስሜ፣ የኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽን ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ ዮሃንስ አበራ፣ ሌሎች የሥራ ኃላፊዎች እና የግል አየር ትራንስፖርት ኦፕሬተር ተወካዮች በተገኙበት፤ የአየር ትራንስፖርት ዘርፍ የባለድሻ አካላት የጋራ የምክክር መድረክ አካሂዷል። በባለስልጣኑ የአየር ትራንስፖርትና ዓለም አቀፍ ጉዳዮች አማካሪ አቶ እንደሻው ይገዙ ባቀረቡት ሪፖርት፤ በ2018 ዓ.ም ዓለም አቀፍ በረራዎችን ከአዲስ አበባ ዓለም አቀፍ ኤርፖርት በተጨማሪ በሌሎች የሀገሪቱ ክልል ኤርፖርቶች ማስተናገድ እንደሚጀመር ተናግረዋል። "የክልል ኤርፖርቶችን ማስተሳሰር የቱሪዝም ፍሰቱ እንዲጨምር እንዲሁም የደንበኛውን እንግልት መቀነስ የሚያስችል ነው" ያሉት አቶ…
Read More
ጃፓን ለአትሌት አበበ ቢቂላ የመታሰቢያ መንገድ ሰየመች

ጃፓን ለአትሌት አበበ ቢቂላ የመታሰቢያ መንገድ ሰየመች

በጃፓን ካሳማ ከተማ ለአትሌት አበበ ቢቂላ የመታሰቢያ መንገድ ተሰየመ በጃፓን ካሳማ ከተማ አትሌት አበበ ቢቂላን ለማስታወስ የግማሽ ማራቶን መንገድ በስሙ መሰየሙን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል። የስያሜ ስነ-ስርዓቱ የኢንዱስትሪ ሚኒስትር አቶ መላኩ አለበልን፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ሃደራ አበራን፣ በጃፓን የኢትዮጵያ አምባሳደር ዳባ ደበሌን እና የካሳማ ከተማ ከንቲባን ጨምሮ በርካታ ባለስልጣናት በተገኙበት ተከናውኗል። በስነ-ስርዓቱ ላይ የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አለበል ይህ የመታሰቢያ ስያሜ ለአትሌቱ ክብር ከመስጠት በተጨማሪ በኢትዮጵያ እና በጃፓን መካከል ያለውን ጥብቅ ወዳጅነት እና የባህል ትስስር የሚያሳይ እንደሆነ ገልጸዋል። አትሌት አበበ ቢቂላ በ1964ቱ የቶኪዮ ኦሎምፒክ ያገኘው ድል ኢትዮጵያን ያስጠራ ብቻ ሳይሆን በሁለቱ አገራት መካከል ያለውን ግንኙነትም አጠናክሯል ብለዋል። በጃፓን…
Read More
ልማት ባንክ ከ24 ቢሊዮን ብር በላይ ብድር መሰብሰቡን አስታወቀ

ልማት ባንክ ከ24 ቢሊዮን ብር በላይ ብድር መሰብሰቡን አስታወቀ

የኢትዮጵያ ልማት ባንክ በ2017 በጀት ዓመት የሥራ አፈጻጸም ግምገማ ወቅት፣ ከ24 ቢሊዮን ብር በላይ የብድር ክምችት ማሰባሰቡን ይፋ አድርጓል። ይህ ባንኩ ለተለያዩ ፕሮጀክቶች አበድሮ የነበረውን ገንዘብ ከባለዕዳዎች መልሶ የሰበሰበው መጠን አፈጻጸም ከታለመለት ግብ በ5 በመቶ ብልጫ ያለው ሲሆን፣ ከባለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር ደግሞ የ51.6 በመቶ ዕድገት ማሳየቱ ተገልጿል። የባንኩ ዋና ትኩረት ለኢንዱስትሪ፣ ለግብርና እና ለሌሎች ቁልፍ የኢኮኖሚ ዘርፎች የፋይናንስ ድጋፍ ማድረግ እንደሆነ ይታወቃል። የኢትዮጵያ ልማት ባንክ በዚሁ በጀት ዓመት 18.0 ቢሊዮን ብር ገቢ በማሰባሰብ ከባለፈው ዓመት ጋር ሲነጻጸር የ30.7 በመቶ ጭማሪ ማሳየቱን ተጠቅሷል፡፡ የኢትዮጵያ ልማት ባንክ በግብርና፣ ማዕድን ማውጣት፣ ማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ ለሚሰማሩ ኢንቨስትመንቶች የገንዘብ አቅርቦት የሚያመቻች መንግስታዊ ተቋም…
Read More
በኢትዮጵያ ከተመዘገቡ 6 ሺህ ቤት አልሚዎች ውስጥ ስራ ላይ ያሉት ከ400 አይበልጥም ተባለ

በኢትዮጵያ ከተመዘገቡ 6 ሺህ ቤት አልሚዎች ውስጥ ስራ ላይ ያሉት ከ400 አይበልጥም ተባለ

ከፌዴራልና ከክልል በአጠቃላይ በሀገር አቀፍ ደረጃ በሪል እስቴት ልማት ዘርፍ ለመሳተፍ ፈቃድ የወሰዱና የተመዘገቡ 6 ሺሕ የሚሆኑ አልሚዎች ያሉ ቢሆኑም፤ በሥራ ላይ የሚገኙት ግን ከ400 እንደማይበልጡ የኢትዮጵያ ሪል እስቴት አልሚዎች ማህበር አስታውቋል። የሪል እስቴት ዘርፉ ከአልሚዎች፣ ከገዢዎችና ከፋይናንስ ተቋማት ጨምሮ፤ በርካታ ችግሮች እና ተነሳሽነት ያልነበረበት እንደነበር የገለጹት፤ የማህበሩ ም/ፕሬዝዳንት ኢንጂነር ጀበል ጀማል ናቸው። ያለውን ችግር ለማስተካከልና በዘርፉ መተጋገዝ ካለና በጋራ መስራት ከተቻለ፤ የተሻለ ለውጥ ሊመጣ እንደሚችል በማመን የሪል እስቴት አልሚዎች ማሕበር መመስረት መቻሉንም አንስተዋል። ማሕበሩ ከመንግሥትና ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን በ29 አባላት መመስረት እንደቻለ አስታውሰው፤ አሁን ላይ ከ100 በላይ አባልትን በውስጡ መያዙን ገልጸዋል። አሁን ላይ እንደሀገር ከተመዘገቡት 6 ሺሕ…
Read More
ኢትዮጵያ በውጭ ሀገራት የሚሰማሩ ስራ ተቋራጭ ድርጅቶችን የማሳደግ እቅድ እንዳላት ተገለጸ

ኢትዮጵያ በውጭ ሀገራት የሚሰማሩ ስራ ተቋራጭ ድርጅቶችን የማሳደግ እቅድ እንዳላት ተገለጸ

10 የስራ ተቋራጭ ድርጅቶች ከኢትዮጵያ ውጪ ውጪ ባሉ ሀገራት መሰማራታቸውን የከተማ እና መሰረተ ልማት ሚንስቴር አስታውቋል ሚንስቴሩ በሌሎች የአፍሪካ ሀገራት የተሰማሩ የኢትዮጵያ ስራ ተቋራጭ ድርጅቶችን ቁጥር 20 የማድረስ እቅድ መያዙን ገልጿል። የሀገራቱን አስፈላጊ መስፈርት አሟልተውና በጨረታ አሸንፈው በተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት ውስጥ በኮንስትራክሽን ሥራዎች ላይ የሚሳተፉ ተቋራጮችን ቁጥር ወደ 20 ከፍ ለማድረግ እየተሰራ እንደሆነ የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር አስታውቋል። የሚንስትሩ ሕዝብ ግንኙነት እና ኮሙኒኬሽን ሥራ አስፈጻሚ አቶ ኢትዮጵያ በዴቻ፤ "ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ የግንባታ ሥራ ለማከናወን ፈቃድ ተሰጥቷቸው በሌሎች የአፍሪካ ሀገራት የኮንትራት ሥራዎችን ወስደው በግንባታ ላይ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን የግንባታ ስራ ተቋራጮች ቁጥር ከ10 አይበልጥም" ብለዋል፡፡ በመሆኑም ሚኒስቴሩ ይህን የግንባታ ሥራ ተቋራጮች…
Read More