መነሻ ገፅ

በኢትዮጵያ ውስጥ የሚፈጸሙት ጥቃቶች እንዲመረመሩ ለዓለማቀፉ ማሕበረሰብ ጥሪ ቀረበ

በኢትዮጵያ ውስጥ የሚፈጸሙት ጥቃቶች እንዲመረመሩ ለዓለማቀፉ ማሕበረሰብ ጥሪ ቀረበ

አምስት ፓርቲዎች የመሰረቱት 'ትብብር ለኢትዮጵያ አንድነት' የተሰኘው ቅንጅት፣ በኢትዮጵያ ውስጥ የሚፈጸሙት ጥቃቶች እንዲመረመሩ ለዓለማቀፉ ማሕበረሰብ ጥሪ አቅርቧል፡፡ ቅንጅቱ በቅርቡ  በአርሲ የተፈጸመውን ግድያ አስመልክቶ ባወጣው መግለጫ፤“ በኢትዮጵያ የሚፈጸሙት ማንነትና ሃይማኖት ተኮር ጥቃቶች መንግሥታዊ መዋቅርን የተከተሉ፣ ሥርዓታዊና ተጨማሪ እጅ ያለበት ስለመኾኑ ምርመራ እንዲደረግ ” ጥሪውን አቅርቧል። ቅንጅቱ፤ “ጠያቂም ተጠያቂም ባለመኖሩ መግደል ቀላል ኾኗል” በሚል  ያወጣው መግለጫ፤ “ እንዲህ ዓይነቱን ግዙፍ ኢ-ሰብዓዊ ድርጊት" በጽኑ እንደሚያወግዝ አስታውቆ፣ "እልቂት የየቀን ገጠመኙ ለኾነው የአካባቢው ማኅበረሰብም" ብርታትና መጽናናትን ተመኝቷል። መላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ)፣ የኢትዮጵያ ሕዝብ አንድነት ፓርቲ (ኢሕአፓ)፣ እናት ፓርቲ፣ አዲሲ ኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (አኢዴፓ) እና አማራ ግዮን ንቅናቄ ( አግን) የመሠረቱት ' ትብብር ለኢትዮጵያ አንድነት…
Read More
ኢትዮጵያ በአፍሪካ ነፃ ንግድ ቀጠና እድል ምርቶቿን ወደ ሶስት ሀገራት እየላከች ነው ተባለ

ኢትዮጵያ በአፍሪካ ነፃ ንግድ ቀጠና እድል ምርቶቿን ወደ ሶስት ሀገራት እየላከች ነው ተባለ

ኢትዮጵያ የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጠና ስምምነትን መስከረም 29 ቀን 2018 ዓ.ም በይፋ መጀመሯ ይታወሳል። ሀገሪቱ ምርቶቿን ወደ ሶስት የአፍሪካ ሀገራት በመላክ ላይ ነች የተባለ ሲሆን ምርቶቹ በኢትዮጵያ አየር መንገድ ካርጎ በኩል እየተላኩ እንደሆነም ተገልጿል። የንግድ እና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር ኮሚኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ወንድሙ ፍላቴ እንዳሉት ከተላኩት የመጀመሪያ የወጪ ንግድ ምርቶች መካከል ስጋ፣ አትክልትና ፍራፍሬ፣ ቡና እና ጥራጥሬ እህሎች ይገኙበታል። ኬንያ፣ ደቡብ አፍሪካ፣ ሶማሊያና ጅቡቲ ደግኖ የኢትዮጵያ ምርቶሽ የተላከባቸው ሀገራት እንደሆኑ ተጠቅሷል። ምርቶቹ በአብዛኛው የተጓጓዙት በኢትዮጵያ አየር መንገድ ካርጎ አማካኝነት ሲሆን፤ አየር መንገዱ ለነፃ ንግድ ቀጠናው ትግበራ ትልቁን ድርሻ እየተወጣ ነው ብለዋል አቶ ወንድሙ። የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጠና ስምምነትን…
Read More
ቋሚ ሲኖዶሱ በኦሮሚያ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች የተፈጸመውን የ25 ምዕመናን ግድያ አወገዘ

ቋሚ ሲኖዶሱ በኦሮሚያ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች የተፈጸመውን የ25 ምዕመናን ግድያ አወገዘ

በኦሮሚያ ክልል በምሥራቅ አርሲ ዞን አስተዳደር በጉና፣ በመርቲ፤ በሸርካ እና በሆሎንቆ ዋቢ ወረዳዎች ውስጥ በሚገኙ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን እምነት ተከታዮች ላይ ማንነታቸው ባልታወቀ ታጣቂዎች የተፈጸሙትን አሰቃቂ ግድያዎች የቤተክርሲቲያኒቷ ቋሚ ሲኖዶስ አውግዟል፡፡ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ በምሥራቅ አርሲ ሀገረ ስብከት ሕይወታቸውን ያጡ ወገኖችን አስመልክቶ መግለጫ አውጥቷል፡፡ በመግለጫውም ጥቅምት 14 ለ15 ቀን 2018 ዓ.ም በጉናና መርቲ ወረዳዎች 17 ክርስቲያኖች፣ ጥቅምት 17 ለ18 ቀን 2018 ዓ.ም. በሸርካ ወረዳ 3 ክርስቲያኖች እንዲሁም ጥቅምት 18 ለ19 ቀን 2018 ዓ.ም. በሆንቆሎ ዋቤ ወረዳ 5 ክርስቲያኖች በድምሩ በጥቅምት ወር 2018 ዓ.ም. ብቻ 25 ኦርቶዶክሳውያን በድንገት ማንነታቸው ባልታወቀ ታጣቂዎች በአሰቃቂ ሁኔታ መገደላቸውን አስታውቋል፡፡ ግድያውም…
Read More
የኢትዮጵያ እና ኤርትራ ጸብ ባንድ ጀምበር የመጣ እንዳልሆነ ጠቅላይ ሚንስትሩ ተናገሩ

የኢትዮጵያ እና ኤርትራ ጸብ ባንድ ጀምበር የመጣ እንዳልሆነ ጠቅላይ ሚንስትሩ ተናገሩ

ጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ በዛሬው ዕለት ከፓርላማ አባላት ጋር ባደረጉት ውይይት ላይ ከኤርትራ ጋር የተፈጠረው አለመግባባት በአንድ ጀምበር የመጣ ሳይሆን ቀስ በቀስ በሂደት መምጣቱን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ከስድስት ዓመት በፊት የባህር ሀይሏን እንዳቋቋመች የተናገሩት ጠቅላይ ሚንስትሩ ይህ ሀይል የተቋቋመው በሀገር ውስጥ ብቻ እንዲገታ በማሰብ አልነበረም አሰብ ወደብን ከኤርትራ እንደምንረከብ በማመን ነበር ብለዋል። "ከኤርትራ መንግሥት ጋር ተስማምተን ከዚህ ወደ አሰብ የሚወስደውን መንገድ ጠግነናል ፣እንከፍታለን ብለን ጠግነናል፣ መንገዱን ከጠገንን በኋላ ግን ችግር አለብን አሰብ ወደብ ተዳክሟል አሉን። አንዳንድ ሰው ከኤርትራ ጋር የገባንበት አለመግባባት በአንድ ምሽት የመጣ ይመስለዋል እንደዛ አይደለም ታሪኩን ስለማንናገር ነው" ብለዋል ጠቅላይ ሚንስትር አብይ። ወደ አሰብ መንገድ ጠግነን ከጨረስን በኃላ '…
Read More
በኢትዮጵያ የባንኮች የገንዘብ ዝውውር ቅናሽ ማሳየቱ ተገለጸ

በኢትዮጵያ የባንኮች የገንዘብ ዝውውር ቅናሽ ማሳየቱ ተገለጸ

በኢትዮጵያ ከ2013 ዓ.ም. ጀምሮ በባንክ የሚካሄድ አጠቃላይ የገንዘብ ዝውውር ቅናሽ ማሳየቱን የኢትዮጵያ ምጣኔ ሃብት ባለሙያዎች ማኅበር "ባካሄድኩት ጥናት አረጋግጫለሁ" ብሏል። በማኅበሩ ከፍተኛ የምጣኔ ሃብት ተመራማሪ ናስር የኑስ (ዶ/ር) እንደተናገሩት፤ በተለይ ከ2012 ዓ.ም. መጨረሻ ወራት አንስቶ፣ በይበልጥ ደግሞ ከ2013 ዓ.ም. ጀምሮ የገንዘብ ዝውውር (ትራንዛክሽን ባንኪንግ) አገልግሎት የሚጠቀሙ ደንበኞች ቁጥር እየቀነሰ ነው። ለዚህ የገንዘብ ዝውውር መቀነስ ዋነኛ ምክንያቶች ናቸው ያሏቸውን ጉዳዮች የጠቀሱት የምጣኔ ሃብት ተመራማሪው፤ የዜጎች የገቢ ማሽቆልቆል፣ አልፎ አልፎ የሚታዩ ግጭቶችና ጦርነቶች እልባት አለማግኘት፣ የሥራ አጥ ቁጥር መጨመር፣ እና የኢንተርኔት አገልግሎት ችግር እንደሆኑ ዘርዝረዋል። ተመራማሪው ይህንን እያሽቆለቆለ ያለውን የገንዘብ ዝውውር ለማነቃቃት ባንኮች ሊተገብሯቸው ይገባል ካሏቸው የመፍትሔ እርምጃዎች መካከል፤ ባንኮች ለገንዘብ ዝውውር…
Read More
ትዕግሥት አሰፋ እና ዮሚፍ ቀጄልቻ የዓመቱ ምርጥ አትሌት ዕጩ ሆኑ

ትዕግሥት አሰፋ እና ዮሚፍ ቀጄልቻ የዓመቱ ምርጥ አትሌት ዕጩ ሆኑ

የዓለም አትሌቲክስ በሁለቱም ፆታ የ2025 የዓመቱ የጎዳና ላይ ምርጥ አትሌት ዕጩዎችን ይፋ አድርጓል። በዚህም ኢትዮጵያ አትሌት ትዕግሥት አሰፋ እና ዮሚፍ ቀጄልቻን በዓመቱ በሁለቱም ፆታ ምርጥ ብቃት ካሳዩ አምስት አትሌቶች መካከል ተብለው እጩ ሆነዋል። በሴቶቹ አትሌት ትዕግሥት አሰፋ ከኬንያውያኑ አትሌቶች ፔሬስ ጄፕቺርቺር እና አግኔስ ንጌቲች፣ ለኔዘርላንድስ ከምትሮጠው ትውልደ ኢትዮጵያዊቷ አትሌት ሲፈን ሀሰን እና ከስፔናዊቷ ማሪያ ፔሬዝ ጋር ምርጥ አምስት ውስጥ መግባት ችላለች። በወንዶቹ ደግሞ አትሌት ዮሚፍ ቀጄልቻ ከብራዚላዊው አትሌት ካይኦ ቦንፊን፣ ካናዳዊው አትሌት ኢቫን ዱንፊ፣ ኬንያዊው አትሌት ሳባስቲያን ሳዌና ከታንዛኒያዊው አልፎንስ ሲምቡ ጋር ምርጥ አምስት መግባት ችሏል። በለንደን ማራቶን አሸናፊ የነበረችው አትሌት ትዕግሥት አሰፋ በውድድር ዓመቱ በተካሄደው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና 2ኛ…
Read More
በአማራ ክልል ያለው የጸጥታ ችግር በድርድር እንዲፈታ ፓርቲዎች ጥሪ አቀረቡ

በአማራ ክልል ያለው የጸጥታ ችግር በድርድር እንዲፈታ ፓርቲዎች ጥሪ አቀረቡ

በአማራ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች ያለው የፀጥታ ችግር በድርድር እንዲፈታ የፖለቲካ ፓርቲዎች አሳስበዋል። ችግሩን በሐይማኖት አባቶች እና በሽማግሌዎች ብቻ ለመፍታት ከመጣር ይልቅ፣ በድርድር እና በእውነተኛ አካታች ውይይት መፍታት እንደሚገባም የፓርቲዎቹ አመራሮች ጥሪ ማቅረባቸውን አሀዱ ሬዲዮ ዘግቧል። የአንድ ኢትዮጵያ ዲሞክራሲ ፓርቲ ሊቀመንበር አቶ ሲሳይ ደጉ፤ "መንግሥት እና አማራ ክልል የሚገኙ ታጣቂዎች ዋናው ሀገራዊ ምክክር ከመካሄዱ በፊት ያለው የጸጥታ ችግር በሰላም መፈታት አለባቸው" ብለዋል። አቶ ሲሳይ የፌዴራል መንግሥት "ታጣቂዎች ወደ ሰላማዊ መንገድ እንዲመጡ ጥሪ አቅርቤያለሁ" የሚለውን ቃሉን ተግባራዊ እንዲያደርግ፤ ጥረት እየተደረገ ከሆነም መንግሥት ለሕዝብ ይፋ እንዲያደርግ ጠይቀዋል። ይህንን ሀሳብ የሚጋሩት የኢትዮጵያ ሕዝብ አብዮታዊ ፓርቲ የፋይናንስ ንብረት አስተዳደር ሥራ አስፈጻሚ አቶ ሙሉጌታ ሐድጉ በበኩላቸው፤…
Read More
የቪዛ ጊዜያቸውን ያሳለፉ ከ36 ሺህ በላይ የውጭ ሀገር ዜጎች ተቀጡ

የቪዛ ጊዜያቸውን ያሳለፉ ከ36 ሺህ በላይ የውጭ ሀገር ዜጎች ተቀጡ

በኢትዮጵያ የተሰጣቸውን የቪዛ ጊዜ ያሳለፉ ከ36 ሺህ በላይ የውጭ ሀገር ዜጎች ተቀጥተው ወደ ሕጋዊ መስመር ተመልሰዋል አለ የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት፡፡ የአገልግሎቱ ዋና ዳይሬክተር ሰላማዊት ዳዊት እንዳሉት ወደ ኢትዮጵያ የሚመጡ የተለያዩ ሀገራት ዜጎች ሕግ አክብረው እንዲንቀሳቀሱ እየተሰራ ነው፡፡ በዘርፉ በተከናወኑ የሪፎርም ሥራዎች ሀገራዊ አቅም መጠናከሩን አመልክተዋል፡፡ ለአብነትም በአዲስ አበባ በተካሄዱ ዓለም አቀፍና አህጉር አቀፍ ጉባዔዎች የተሳተፉ የውጭ ሀገራት ዜጎች ያለምንም እንከን መስተናገዳቸውን ጠቅሰዋል። በቪዛ አገልግሎት ወደ 188 ሀገራት የመዳረሻ (ኦን አራይቫል ቪዛ) ተጠቃሚዎች ሆነዋል ያሉት ዋና ዳይሬክተሯ÷ ይህም የ24 ሰዓት የኤሌክትሮኒክስ ቪዛ አገልግሎት ያለው መሆኑን አመልክተዋል፡፡ ከፓስፖርት አገልግሎት ጋር በተያያዘ የተለያዩ የማሻሻያ ርምጃዎች መወሰዳቸውን እና በዚህም በሕገ ወጥ ሰንሰለት የተሰማሩ 26…
Read More
የ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ድምጽ መስጫ ቀን ግንቦት 24 እንዲሆን ቀረበ

የ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ድምጽ መስጫ ቀን ግንቦት 24 እንዲሆን ቀረበ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለሰባተኛ ጊዜ የሚካሄደውን ሀገር አቀፍ ምርጫ፤ በመጪው ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም ለማድረግ ምክረ ሃሳብ አቅርቧል። የምርጫ ውጤት ለህዝብ ማሳወቂያ ቀን ደግሞ ሰኔ 3 ቀን እንደሚሆንም ቦርዱ አስታውቋል። ሰባተኛው ሀገር አቀፍ ጠቅላላ ምርጫ ለማድረግ በዝግጅት ላይ የሚገኘው ብሔራዊው ምርጫ ቦርድ በምርጫው የጊዜ ሰሌዳ ዙሪያ ከፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር ውይይት አድርጓል። ከ60 በላይ የፖለቲካ ፓርቲዎች ተወካዮች በተሳተፉበት በዚህ ውይይት ላይ በምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ላይ የጦፈ ውይይት መደረጉ ተገልጿል። መገናኛ ብዙሃን ባልተገኙበት በዚህ የውይይት መድረክ ላይ፤ ምርጫ ቦርድ የሰባተኛውን ሀገር አቀፍ ምርጫ ዝርዝር የጊዜ ሰሌዳን ለፓርቲዎች ለውይይት አቅርቧል። ለውይይት በቀረበው የጊዜ ሰሌዳው መሰረትም ህዳር ወር ውስጥ በምርጫ መወዳደር የሚፈልጉ…
Read More
ኢትዮጵያ ከቻይና ያለባትን ዕዳ ወደ ዩዋን እንዲቀየር ጠየቀች

ኢትዮጵያ ከቻይና ያለባትን ዕዳ ወደ ዩዋን እንዲቀየር ጠየቀች

ኢትዮጵያ ለቻይና መንግሥት የምትከፍለውን ቢያንስ 5.38 ቢሊዮን ዶላር ዕዳ በከፊል ወደ ቻይና ገንዘብ (ዩዋን) ለመቀየር ከቤጂንግ ጋር ውይይት መጀመሯ ተዘግቧል። ይህ እርምጃ ቀደም ሲል ኬንያ ያደረገችውን በመከተል፣ ቻይና የገንዘብ ምንዛሪዋን ዓለም አቀፋዊ የማድረግ ጥረቷን የሚያጠናክር መሆኑ ተገልጿል። ብሉምበርግ እንደዘገበው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገዥ አቶ እዮብ ተካለኝ ባለፈው ወር ወደ ቤጂንግ ባደረጉት ጉብኝት ከቻይና ኤክስፖርት-ኢምፖርት ባንክ እና ከቻይና ሕዝብ ባንክ ጋር ለዚህ እምቅ የዕዳ ልውውጥ ውይይት መጀመራቸውን አስታውቀዋል። ገዥው ይህንን የገለጹት አርብ ጥቅምት 07 ቀን 2018 ዓ.ም. በዋሽንግተን ዲሲ በተካሄደው የዓለም አቀፍ የገንዘብ ተቋም (IMF) ዓመታዊ ስብሰባ ላይ በሰጡት ቃለ ምልልስ ነው። ሀገሪቷ ዕዳውን በዩዋን መክፈል የውጭ ምንዛሪ ክምችት ላይ ያለውን…
Read More