ዜና

በአዲስ አበባ 100 ሺህ ቤቶችን በአንድ ዓመት ውስጥ ለመገንባት ስምምነት ተፈረመ

በአዲስ አበባ 100 ሺህ ቤቶችን በአንድ ዓመት ውስጥ ለመገንባት ስምምነት ተፈረመ

የቤቶቹ ግንባታ በ68 የሪል ኢስቴት አልሚዎች እንደሚገነባ የተገለጸ ሲሆን መንግሥት መሬት በነጻ ለማቅረብ ተስማምቷል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በመንግሥትና በግል አጋርነት ፕሮጀክት አማካይነት በመረጣቸው ሪል ስቴት አልሚዎች፣ ከግማሽ ትሪሊዮን ብር በላይ ወጪ የመኖሪያ ቤቶች ግንባታ ሊካሄድ ነው ተብሏል። በዚህ ፕሮግራም ሥር እንዲሳተፉ 68 ሪል ስቴት አልሚዎችን የመረጠ ሲሆን፤ አልሚዎቹም በተቀመጠው 70/30 አጋርነት መሠረት ከከተማ አስተዳደሩ ጋር ተጣምረው ግንባታውን ለማካሄድ ውል መግባታቸውን ሪፖርተር ጋዜጣ ዘግቧል። ከእነዚህም አልሚዎች ውስጥ ሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ፣ ኦቪድ ግሩፕ፣ ፍሊንትስቶን ሆምስ፣ እንይ ኮንስትራክሽን፣ ጊፍት ሪል ስቴትና ሌሎችም ይገኙበታል። የከተማ አስተዳደሩ የቤቶቹን ግንባታ ለማካሄድ የሚያስፈልገውን መሬት ከሊዝ ነፃ ማቅረብና መሠረተ ልማቶችን የማሟላት ኃላፊነት አለበት ተብሏል። የሪል ስቴድ ድርጅቶች…
Read More
ኢትዮጵያ በቴሌግራም መተግበሪያ ላይ ዳግም እገዳ ጣለች

ኢትዮጵያ በቴሌግራም መተግበሪያ ላይ ዳግም እገዳ ጣለች

በኢትዮጵያ የቴሌግራም መተግበሪያ የማህበራዊ ትስስር ገጽ ከዛሬ ረቡዕ ሐምሌ 19 ቀን 2015ዓ.ም ጠዋት ጀምሮ እየሰራ አይደለም። ገደቡ የተጣለዉ ዛሬ ከሚጀመረዉ የ 2015 ዓ.ም የ 12ኛ ክፍል ፈተና ጋር በተያያዘ ሊሆን እንደሚችል ይገመታል። ይሁንና መንግሥት ለምን በቴሌግራም ላይ እገዳ እንደጣለ እስካሁን መረጃ ያልሰጠ ሲሆን መተግበሪያው በቪፒኤን እየሰራ ይገኛል። ከወራት በፊት በኦሮሚያ ክልል የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን አጋጥሟት የነበረዉን የመከፋፈል ድርጊትና የጳጳሳት ሹመነትን በሚመለከት በተለያዩ አካባቢዎች የተነሳዉን ተቋዉሞ ተከትሎ በማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ እግዱ ተጥሎ ለአምስት ወራት መቆየቱ ይታወሳል። በዚህም መሰረት እንደ ፌስቡክ ፣ ቲክቶክ ፣ ቴሌግራም ፣ ኢንስታግራም ፣ ዩቲዩብ እና ሌሎች የማህበራዊ መገናኛ ዘዴዎችን ሰዎች VPN ( virtual private network )…
Read More
ኢትዮጵያ ወደ ውጪ ሀገራት ከተላከ የአህያ ስጋ 300 ሺህ ዶላር ማግኘቷን ገለጸች

ኢትዮጵያ ወደ ውጪ ሀገራት ከተላከ የአህያ ስጋ 300 ሺህ ዶላር ማግኘቷን ገለጸች

ቻይና ዋነኛዋ የኢትዮጵያ አህያ ስጋ የተላከባት ሀገር ስትሆን ፍላጎቱ እያደገ እንደሆነም ተገልጿል። በተጠናቀቀው የ2015 በጀት ዓመት ኢትዮጵያ የአህያ ስጋን ወደ ሆንግኮንግ በመላክ 3 መቶ ሺህ ዶላር ገቢ ማግኘቷን የእንስሳት ልማት ኢንስትቲዩት አስታውቋል፡፡ በኢንስትቲዩቱ ምክትል ዋና  ዳይሬክተር የሆኑት ዶክተር ሳህሉ ሙሉ እንደተናገሩት፣ ከአህያ ስጋ ውጪ የአህያ ቆዳን እንደ ቻይና ያሉ ሃገራት ለመድሃኒትነት በስፋት ሲጠቀሙበት የሚስተዋል በመሆኑ የስጋ ምርቱን ወደ ሆንግኮንግ እንዲላክ ተደርጓል ብለዋል፡፡ ገቢው  የተገኘውም በተጠናቀቀው በጀት አመት 140 ቶን የአህያ ስጋ ምርትን ወደ ውጪ ገበያ በመላክ እንደሆነ ጨምረው ገልጸዋል፡፡ በበጀት አመቱ 600 ቶን የአህያ ስጋን ወደ ውጪ ለመላክ አስቀድሞ ታቅዶ እንደነበር ኢንስቲትዩቱ ገልጿል፡፡ በአህያ ስጋ የወጪ ንግድ  ዙሪያ የቄራ ድርጅቶች…
Read More
እስራኤል ሁለት ሺህ ቤተ እስራኤላዊያንን ከኢትዮጵያ ልትወስድ መሆኗን ገለጸች

እስራኤል ሁለት ሺህ ቤተ እስራኤላዊያንን ከኢትዮጵያ ልትወስድ መሆኗን ገለጸች

የእስራኤል ጠቅላይ ሚንስትር ቤንያሚን ኔታንያኹ ለመንግስታቸዉ ከኢትዮጵያዉያን ቤተ እስራኤላውያን ማህበረሰብ ጋር ያላቸዉን ግንኙነት ማጠናከር ባለባቸዉ ጉዳዮች ላይ ያቀረቡት እቅድ ጸድቋል። በዚህ እቅድ መሰረትም 2 ሺህ ቤተእስራኤላውያንን ወደ ቴልአቪቭ ለመዉሰድ ማቀዳቸዉን ጀረሰላም ፖስት ዘግቧል። እ.ኤ.አ በ 2015 የእስራኤል መንግስት 9 ሺህ የሚደርሱ ኢትዮጵያውያን እስራኤል መግባት የሚፈልጉ ቤተ እስራኤላውያንን ጥያቄ ከተቀበለ በኋላ ባገጠመዉ የበጀት እጥረት ማጓጓዝ ሳይችል መቅረቱ ተዘግቧል። በጠቅላይ ሚኒስትሩ ቀረበ የተባለዉ እቅድ ኢትዮጵያዊ ቤተ እስራኤላዊያንን ለማጓጓዝ 66 ሚሊዮን ዶላር በጀት ተይዞለታልም ተብሏል። የሀገሪቱ መንግስት በእስራል ከሚገኙ ከ 160 ሺህ በላይ ቤተ እስራኤላውያን ዜጎች ጋር ያለዉን ግንኙነት  በማጠናከር በተለይም ወደ ሀገሪቱ የጦር ሀይል ለማካተት እቅድ እንዳለዉ በዘገባው ላይ ተጠቅሷል። በተጨማሪም በእስራኤላውያን…
Read More
በጋምቤላ በተከሰተ የብሔር ግጭት ከ30 በላይ ሰዎች መገደላቸው ተገለጸ

በጋምቤላ በተከሰተ የብሔር ግጭት ከ30 በላይ ሰዎች መገደላቸው ተገለጸ

በጋምቤላ ክልል በአኙዋክ እና ኑዌር ብሔረሰቦች መካከል በተፈጠረዉ ግጭት እስካሁን ቁጥራቸዉ ከ30 በላይ የሆኑ ሰዎች ህይወት ማለፉን የክልሉ መንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ኡገቱ አዲንግ ተናግረዋል። አቶ ኡገቱ ፤ ግጭቱ ግንቦት 13 ላይ አኙዋ እና ሊየር በሰተኙ በሁለት መንደሮች መካከል የተነሳ መሆኑን ገልጸዋል ። ግጭቱ በኋላም ወደ ብሔር ግጭት እየሰፋ የመጣ መሆኑን የተናገሩት ሀላፊው ግጭቱ በተከሰተበት ወቅትም የክልሉ መንግስት ኮማንድ ፖስት በማቋቋም ከፌዴራል የጸጥታ አካላት ጋር ሁኔታዉን ለማረጋጋት እየሰሩ መሆኑን ጠቁመዋል። የሟቾች ቁጥር 30 ደርሷል ቢባልም በጸጥታ ግብረ ሀይሉ የተረጋገጠ አይደለም ብለዋል። ሆኖም በግጭቱ የተገደሉት ሰዎች ቁጥር ከዚህ ከፍ ሊል እንደሚችል ግን ግምታቸውን አስቀምጠዋል። በግጭቱ በኢታንግ ልዩ ወረዳ 4…
Read More
ሰላምዊት ዳዊት የኢምግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት ሀላፊ ሆነው ተሾሙ

ሰላምዊት ዳዊት የኢምግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት ሀላፊ ሆነው ተሾሙ

ጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ ሰላማዊት ዳዊትን የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ሀላፊ አድርገው ሾሙ። የኢሚግሬሽንና የዜግነት አገልግሎት ሶስት ከፍተኛ አመራሮች ከሀላፊነት መነሳታቸው ተገልጿል። ፓስፖርት እና መሰል የዜግነት አገልግሎቶችን ለመስጠት የተቋቋመው የኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት ተቋም ቅሬታዎች ሲቀርቡበት ቆይተዋል። ጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ (ዶ/ር) ላለፉት አንድ ዓመት ከመንፈቅ የኢምግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎትን በዋና ዳይሬክተርነት ሲመሩ የነበሩት አቶ ብሩህተስፋ ሙልጌታን፣ በምክትል ዳይሬክተርነት ሲያገለግሉ የነበሩት ፍራኦል ጣፋ እና ታምሩ ግንበቶን ከኅላፊነት አንስተዋል። የኢምግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት ህዝብ ግንኙነት እና ኮሙንኬሽን ሀላፊ ወይዘሮ ማስታዋል ገዳ ለአልዓይን እንዳሉት ወይዘሮ ሰላማዊት ዳዊት ከሰኔ 12 ቀን 2015 ዓም ጀምሮ ተቋሙን በዋና ዳይሬክተርነት እንዲመሩ መሾማቸውን የሚገልጽ ደብዳቤ ደርሶናል ብለዋል። እንዲሁም…
Read More
ድምጻዊ እጅጋየሁ ሽባባው እና የመቄዶኒያ መስራቹ የክብር ዶክትሬት ተሸለሙ

ድምጻዊ እጅጋየሁ ሽባባው እና የመቄዶኒያ መስራቹ የክብር ዶክትሬት ተሸለሙ

20 የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች በተለያዩ የትምህርት ዘርፎች ያሰለጠኗቸውን ተማሪዎች አስመርቀዋል። በመውጫ ፈተና ምክንያት የደበዘዘው የዘንድሮው የዩንቨርሲቲዎች ፈተና የተመራቂ ተማሪዎች ቁጥርም ቀንሷል፡፡ ተማሪዎቻቸውን ካስመረቁ ዩኒቨርስቲዎች መካከል አዲስ አበባ፣ ወለጋ፣ ደብረብርሃን፣ አርባምንጭ፣ ጅግጅጋ፣ ድሬዳዋ እና ሰመራ፣ ወልቂጤ እንዲሁም  እንጅባራ ዩኒቨርስቲዎች ዋነኞቹ ናቸው፡፡ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በተለያየ መርሐ ግብር ያስተማራቸውን 8 ሺህ 642 ተማሪዎችን ሲያስመርቅ ለመቄዶንያ የበጎ አድራጎት ድርጅት መስራቹ እና ለአርቲስት ደበበ እሸቱ የክብር ዶክትሬት ሰጥቷል፡፡ እንዲሁም እንጅባራ ዩኒቨርስቲ ለዝነኛዋ ሙዚቀኛ እጅጋየሁ ሽባባው የክብር ዶክትሬት ዲግሪ መስጠቱንም አስታውቋል፡፡ ድምጻዊቷ በህመም እና በስራ ምክንያት በአካል አለመገኘቷ የተገለጸ ሲሆን እናቷ በአካል ተገኝተው የክብር ድግሪውን ተቀብለዋል፡፡ ዩንቨርሲቲዎች ባልተለመደ መልኩ ባንድ ቀን ለማስመረቅ የተገደዱት ግቢዎቻቸውን ለ2015 የ12ኛ…
Read More
ኢትዮጵያ 12 ቢሊዮን ዶላር ብድር እንዲሰጣት ጠየቀች

ኢትዮጵያ 12 ቢሊዮን ዶላር ብድር እንዲሰጣት ጠየቀች

የኢትዮጵያ መንግስት ለሁለተኛው አገር በቀል የኢኮኖሚ ፕሮግራም ማስፈጸሚያ 12 ቢሊዮን ዶላር ብድር ጠይቋል፡፡ ብድሩ እና እርዳታው የተጠየቀው የዓለም የገንዘብ ድርጅት አይኤምኤፍ፣ ዓለም ባንክና ኢትዮጵያ ያለባትን የውጭ ዕዳ መልሶ ከማሸጋሸግ ለማግኘት እንደሆነ ተገልጿል፡፡ የጠቅላይ ሚኒስትሩ የኢኮኖሚ ጉዳዮች አማካሪ አቶ ተክለ ወልድ አጥናፉ ለሪፖርተር እንዳሉት ኢትዮጵያ አሁን ላይ ከአሜሪካ፣ ፈረንሣይና ሌሎች ሀገራት ጋር ያላት ግንኙነት መልካም መሆኑ ብድሩ ሊገኝ ይችላል ብለዋል፡፡ ኢትዮጵያ የብድር መክፈያ ጊዜ እንዲስተካከል ጠይቃለች ያሉት አማካሪው ብድሩ ድርድር ከተደረገበት በኋላ ይለቀቃል የሚል ተስፋ መኖሩንም ጠቅሰዋል፡፡ የአሜሪካ ኮንግረስ ኢትዮጵያ ላይ ጥሎት የነበረውን ገደብ እ.ኤ.አ. በጁላይ ወር መጨረሻ ላይ ያነሳል ተብሎ እንደሚጠበቅ፣ ይህም ገንዘቡን ለማግኘት ጥሩ እርምጃ ይሆናልም ተብሏል፡፡ 12 ቢሊዮን…
Read More
ኢትዮጵያ የቀድሞ ተዋጊዎችን መልሶ ለማቋቋም ግማሽ ቢሊዮን ዶላር ጠየቀች

ኢትዮጵያ የቀድሞ ተዋጊዎችን መልሶ ለማቋቋም ግማሽ ቢሊዮን ዶላር ጠየቀች

ኢትዮጵያ የቀድሞ ተዋጊዎችን መልሶ ለማቋቋም ግማሽ ቢሊዮን ዶላር እንደሚያስፈልጋት ገለጸች የቀድሞው ተዋጊዎችን የተሃድሶ ስልጠና ሰጥቶ ወደ ህብረተሰቡ ለመቀላቀል ከ554 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር በላይ እንደሚያስፈልግ የብሔራዊ ተሃድሶ ኮሚሽነር አምባሳደር ተሾመ ቶጋ ተናግረዋል፡፡ ኮሚሽነሩ ይህን የተናገሩት ኮሚሽኑ የቀድሞው ተዋጊዎችን መልሶ በዘላቂነት በማቋቋም ረገድ የመገናኛ ብዙሃን ሚናና በሌሎች ተያያዥ ጉዳዮች ዙሪያ ከመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች ጋር ባካሄደው ውይይት ላይ ነው፡፡ የኮሚሽኑ ጽ/ቤት ሃላፊ ገመዳ አለሚ በበኩላቸው ይህ  የገንዘብ መጠን በመነሻነት የታቀደ እንደነበረ የጠቀሱት ኮሚሽነሩ አሁን ላይ ግን ከተጠቀሰው ከፍ ማለቱን ተናግረዋል ። በኢትዮጵያ 372 ሺህ የቀድሞ ተዋጊዎች እንዳሉ የተሀድሶ ማዕከል እና የሀገር መከላከያ ሚንስቴር በጋራ ያጠኑት ጥናት ያስረዳል። የተመዘገበው አሐዝ ይህ ቢሆንም ቁጥር ሊያሻቅብ…
Read More
በሽብር ወንጀል የተከሰሱ ጋዜጠኞች የዋስትና ጥያቄያቸው ውድቆ ሆኖ በማረሚያ ቤት እንዲቆዩ ተወሰነ

በሽብር ወንጀል የተከሰሱ ጋዜጠኞች የዋስትና ጥያቄያቸው ውድቆ ሆኖ በማረሚያ ቤት እንዲቆዩ ተወሰነ

አራት የመገናኛ ብዙሃን ጋዜጠኞች እና ሌሎች 19 ተከሳሾች ያቀረቡት የዋስትና ጥያቄ በፍርድ ቤት ውድቅ ተደረጓል። በሽብር ወንጀል የተከሰሱ አራት የመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች እና ሌሎች 19 ተከሳሾች ያቀረቡት የዋስትና ጥያቄ፤ በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ውድቅ ተደረገ። የተከሳሾችን በቁጥጥር ስር መዋል በተመለከተ የጸጥታ እና ደህንነት የጋራ ግብረ ኃይል ያወጣውን መግለጫ በድረ ገጻቸው የጫኑ መገናኛ ብዙሃን ዘገባዎቻቸውን እንዲያወርዱም ፍርድ ቤቱ አዝዟል። ይህን ትዕዛዝ የሰጠው ሐምሌ 12 ቀን 2015 ዓ.ም የዋለው የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 3ኛ የጸረ ሽብር እና ህገ መንግስታዊ ችሎት ነው። ችሎቱ የዋስትና ጥያቄውን ውድቅ አድርጎ ትዕዛዞችን በሰጠበት ቅጽበት ተከሳሾች በጭብጨባ የታጀበ መፈክር አሰምተዋል። የተከሳሾቹ መፈክር እና ጭብጨባ፤ የችሎት ውሎ…
Read More