ዜና

የባቢሌ የዝሆኖች መጠለያ ከ200 ሄክታር በላይ መሬት ደን ወደመ

የባቢሌ የዝሆኖች መጠለያ ከ200 ሄክታር በላይ መሬት ደን ወደመ

በኦሮሚያ ክልል ምሥራቅ ሐረርጌ ዞን የሚገኘው የባቢሌ የዝሆኖች መጠለያ ለእርሻ ኢንቨስትመንት በመሰጠቱ ከ200 ሄክታር በላይ የፓርኩ መሬት ደን ሙሉ ለሙሉ መውደሙን የኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ጥበቃ ባለስልጣን ገልጿል፡፡ የኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ጥበቃ ባለስልጣን የብሔራዊ ፓርኮች አስተዳደር መሪ ሥራ አስፈጻሚ ዶክተር አዳነ ጸጋዬ፤ የባቢሌን የዝሆኖች መጠለያ ፓርክ በምሥራቅ ሐረርጌ ዞን በኩል ለእርሻ ኢንቨስትመንት ተሰጥቶ ፓርኩ እየታረሰ በመሆኑ፣ በፓርኩ የሚገኙ ዝሆኖች ለአደጋ ተጋልጠዋል ብለዋል፡፡ የባቢሌን የዝሆኖች መጠለያ በሶማሌ እና በኦሮሚያ ክልሎች ድንበር ላይ የሚገኝ ሲሆን "በኦሮሚያ ክልል በኩል ያለው የፓርኩ ክፍል ለኢንቨስትመንት በመሰጠቱ አሁንም ድረስ እየታረሰ ነው" ሲሉ ገልጸዋል። የፓርኩ መሬት ለኢንቨስትመንት የተሰጠው ፓርኮችን ለመጠበቅና ለማስተዳደር ኃላፊነት የተሰጠው የኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ጥበቃ ባለስልጣን…
Read More
የአፍሪካ ልማት ባንክ ለኢትዮጵያ የ104 ሚሊዮን ዶላር ድጋፍ አጸደቀ

የአፍሪካ ልማት ባንክ ለኢትዮጵያ የ104 ሚሊዮን ዶላር ድጋፍ አጸደቀ

የአፍሪካ ልማት ባንክ በምስራቅ ኢትዮጵያ የሃይል አቅርቦትን ለማሻሻል የሚያግዝ የ104 ሚሊዮን ዶላር ፈንድ ማጽደቁን ገልጿል። የባንኩ የዳይሬክተሮች ቦርድ ያጸደቀው የገንዘብ ድጋፍ 52 ሚሊዮን ዶላሩ ከአፍሪካ ልማት ፈንድ የተገኘ መሆኑም ተመላክቷል። ቀሪው የገንዘብ ድጋፍ ደግሞ የባንኩ የብድር አጋር ከሆነው በኮሪያ-አፍሪካ የኢነርጂ ኢንቨስትመንት ማዕቀፍ ስምምነት ከኮሪያ የኢኮኖሚ ልማት ትብብር ፈንድ የተገኘ እንደሆነ ተገልጿል። የባንኩ የኃይል ሥርዓት ልማት ዳይሬክተር ባቺ ባልዴህ፤ ፕሮጀክቱ በምሥራቅ ኢትዮጵያ ያለውን የኃይል ቋት አቅም በማሳደግ ታዳሽና አስተማማኝ የኤሌክትሪክ አቅርቦትን የሚያሳድግ ነው ብለዋል። መንግሥት በምሥራቅ ኢትዮጵያ የሚያደርጋቸውን የኃይል አቅርቦት ጥረቶች የሚያግዝ ሲሆን፤ አርብቶ አደሮች፣ አነስተኛ ማሳ ያላቸው አርሶ አደሮችና ሌሎች የማኅበረሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ እንደሚያደርግ ተገልጿል። ፕሮጀክቱ 157 ኪሎ ሜትር እርዝማኔ…
Read More
የታላቁ ህዳሴ ግድብ አምስት ተርባይኖች በቅርቡ ሀይል ማመንጨት እንደሚጀምሩ ተገለጸ

የታላቁ ህዳሴ ግድብ አምስት ተርባይኖች በቅርቡ ሀይል ማመንጨት እንደሚጀምሩ ተገለጸ

በ2016 በሕዳሴው ግድብ አምስት ተጨማሪ ዩኒቶችን ሥራ ለማስጀመር እየተሠራ መሆኑን፤ የታላቁ የኢትዮጵያ የሕዳሴ ግድብ ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር ክፍሌ ሆሮ አስታውቀዋል፡፡ የሕዳሴ ግድቡ አራተኛ ዙር የውኃ ሙሌት መጠናቀቁን ተከትሎ፤ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድን ጨምሮ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች በተገኙበት የሙሌቱ መጠናቀቅ በይፋ ተበስሯል፡፡ በሥፍራው ለተገኙ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች ማብራሪያ የሰጡት የታላቁ የኢትዮጵያ የሕዳሴ ግድብ ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር ክፍሌ ሆሮ፤ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ 93 በመቶ መጠናቀቁን መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ግድቡ፤ ግራ፣ ቀኝ እና መካከለኛ አካል እንዳለው የተናገሩት ኢንጂነር ክፍሌ፤ ግራና ቀኙ የግድቡ ክፍል ከ635 እስከ 645 ደረጃ እንደሚሆን ተናግረዋል፡፡ የግራና ቀኙን ክፍል ለማጠናቀቅ ከዘጠኝ እስከ አሥር ሜትር ድረስ ብቻ እንደሚያስፈልግም አስታውቀዋል፡፡…
Read More
ጋዜጠኛ የኋላሸት ዘሪሁን መታሰሩ ተገለጸ

ጋዜጠኛ የኋላሸት ዘሪሁን መታሰሩ ተገለጸ

የትርታ ኤፍ  ኤም መስራች ጋዜጠኛ የኋላሸት ዘሪሁን በፌደራል ፖሊሶች ተይዞ መወሰዱን ባለቤቱ ገልፃለች። ጋዜጠኛ የኋላሸት ዘሪሁን ዛሬ ምሳ ሰዓት ላይ ባልዳራስ ኮንዶሚኒየም ከሚገኘው መኖሪያ ቤቱ በፌደራል ፖሊስ አባላት ተይዞ  ሜክሲኮ የቀድሞው የፌደራል ጉዳዮች ሚኒስቴር ወደሚገኘው ጊዜያዊ ማቆያ ቦታ መወሰዱን ባለቤቷ ገልፃለች ። ባለቤቱ የታሰረበት ቦታ ሄዳ የጠየቀች ሲሆን በምን ምክንያት እንደታሰረ እንዳላወቀና ለጥያቄም እንዳልቀረበ አሳውቋታል ። ጋዜጠኛ የኋላሸት ትኩረቱን በኪነ ጥበባዊ ጉዳዮች ላይ ያደረገው ኪነ ብስራት የተሰኘ የሬድዮ ሾው ለዓመታት በብስራት ኤፍ ኤም 101.1 በማቅረብ ይታወቃል። ዓለም አቀፉ የጋዜጠኞች ጥበቃ ቡድን ወይም ሲፒጂ ከቀናት በፊት ባወጣው መግለጫ በኢትዮጵያ የጋዜጠኞች እስር መቀጠሉን እና የታሰሩት እንዲፈቱ ማሳሰቡ ይታወሳል።
Read More
የፌዴራል ቤቶች ኮርፓሬሽን ለዲያስፓራ ኢትዮጵያውያን ቤት መሸጥ ሊጀምር መሆኑን ገለጸ

የፌዴራል ቤቶች ኮርፓሬሽን ለዲያስፓራ ኢትዮጵያውያን ቤት መሸጥ ሊጀምር መሆኑን ገለጸ

ባለፉት አምስት ዓመታት በአዲስ ሀይል እና እቅድ ወደ ስራ መግባቱን የገለጸው የፌደራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በሃገር ውስጥ ካለው ነዋሪ ባሻገር በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያዊያን የቤት ባለቤት የሚሆኑበትን ኘሮጀክት ለመጀመር ዝግጅት እያደረኩ ነው ብሏል። ስለ ኘሮጀክቱ እና ስለተቋሙ ገለፃ ለማድረግም በኮርፓሬሽኑ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ረሻድ ከማል የተመራ ልዑክ ወደ ብሪታንያ በማምራት በዚያ ከሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ-ኢትዮጵያውያን የማህበረሰብ አመራሮች ጋር ተወያይቷል። በውይይቱ የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ-ኢትዮጵያውንን ተጠቃሚ ለማድረግ በአዲስ መልክ ያቀደውን የቤት ልማት ፕሮጀክት ስኬታማ እንዲሆን ከዲያስፖራው ማህበረሰብ ተጨማሪ ሀሳበችንና ተሞክሮዎችን መሰብሰቡ ተገልጻል። ከዚሁ ጎን ለጎን በዋና ስራ አስፈፃሚው የሚመራው የልዑካን ቡድኑ በለንደንና አካባቢው በሚገኙ ከሁለተኛ የዓለም ጦርነት…
Read More
የሕዳሴው ግድብ አራተኛ ዙር የውሀ ሙሌት ተጠናቀቀ

የሕዳሴው ግድብ አራተኛ ዙር የውሀ ሙሌት ተጠናቀቀ

የግድቡ አራተኛ እና ና የመጨረሻ ሙሌት መጠናቀቁን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ተናግረዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ  "የሕዳሴው ግድብን አራተኛና የመጨረሻ ሙሌት በተሳካ ሁኔታ መጠናቀቁን ሳበስር በታላቅ ደስታ ነው፤  ኢትዮጵያውያን ተባብረን በመሥራታችን ፈጣሪ ረድቶናል። " በማለት የግድቡ የመጨረሻ ሙሌት መጠናቀቁን አስታውቀዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ባሰፈሩት መልዕክት፤ "በገንዘባቸው፣ በዕውቀታቸው፣ በጉልበታቸውና በጸሎታቸው በስራው ውስጥ የተሳተፋችሁ ሁሉ  እንኳን ደስ አላችሁ፤ ይህ ኅብረታችን በሌሎች ጉዳዮቻችንም ሊደገም ይገባዋል" ብለዋል። ከ12 ዓመት በፊት የተጀመረው የታላቂ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ አጠቃላይ ግንባታው 91 በመቶ ደርሷል ተብሏብ። ኢትዮጵያዊያን በሚያዋጡት ገንዘብ እነ በመንግስት ወጪ እየተገነባ ያለው ይህ ግድብ በ5ሺህ 200 ሜጋ ዋት ሀይል በማመንጨት ከአፍሪካ ትልቁ ፕሮጀክት ነው። የህዳሴው…
Read More
ኢትዮ ቴሌኮም በመላው አዲስ አበባ የ5G ኔትወርክ አገልግሎቱን ይፋ አደረገ

ኢትዮ ቴሌኮም በመላው አዲስ አበባ የ5G ኔትወርክ አገልግሎቱን ይፋ አደረገ

ኢትዮ ቴሌኮም የአምስተኛው ትውልድ (5G) የሞባይል አገልግሎትን በአዲስ አበባ በወዳጅነት አደባባይ በተካሄደ መርሃ ግብር በይፋ አስጀምሯል። በመርሃ ግብሩም ተቋሙ ከዚህ ቀደም በቅድመ ገበያ ሙከራ ደረጃ በአዲስ አባባ እና አዳማ ከተሞች አስጀምሮት የነበረውን የ5G የሞባይል አገልግሎት፤ በአዲስ አበባ የተለያዩ አካባቢዎች በሚገኙ በ145 ጣቢያዎች ማስጀመሩን አብስሯል። ይህ የ5G የሞባይል ኔትዎርክ አገልግሎት እስከ 10 ጊጋ ባይት በሰከንድ የሚደርስ ፍጥነት እንዳለው የተገለጸ ሲሆን፤ ዳታ የማስተላለፍ መዘግየትን እጅግ በላቀ ኹኔታ በመቀነስ ወደ 1 ሚሊ ሰከንድ ያደርሳል ተብላል። የ5G አገልግሎት በተለይም በተመሳሳይ ወቅት መከናወን የሚፈልጉ እንደ የማምረቻ ፋብሪካዎች፣ ግብርና፣ ሕክምና ለመሳሰሉ ዘርፎች የላቀ ፋይዳ እንዳለውም ተገልጿል። የ5G አገልግሎት ሥራ ላይ መዋል የማህበረሰቡን ሕይወት የሚያቀሉ ዲጂታል መፍትሄዎችን በቀላሉ…
Read More
አሜሪካ በኢትዮጵያ ላይ ጥላው የነበረውን የኢኮኖሚ ማዕቀብ አራዘመች

አሜሪካ በኢትዮጵያ ላይ ጥላው የነበረውን የኢኮኖሚ ማዕቀብ አራዘመች

አሜሪካ ከሁለት ዓመት በፊት የተቀሰቃሰው የሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት የአሜሪካንን የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ይጎዳል በሚል ነበር ጦርነቱ እንዲቆም ጫና ስታደርግ የቆየችው፡፡ ይህ ጦርነት ከኢትዮጵያ በተጨማሪ ምስራቅ አፍሪካን ይጎዳል የምትለው አሜሪካ ጦርነቱ እንዲቆም የተለያዩ ጫናዎችን ያደረገች ሲሆን የሰብዓዊ መብት ጥሰት ተፈጽሟል በሚል የተለያዩ እርምጃዎችን ስትወስድ ቆይታለች፡፡ በዋሸንግተን ከተወሰዱ እርምጃዎች መካከል በኢትዮጵያ ላይ ብሔራዊ የአስቸኳይ ጊዜ ማዕቀብ የሚባል ሲሆን በፈረንጆቹ መስከረም 2021 ላይ ለሁለት ዓመት የሚቆይ ማዕቀብ ተጥሏል፡፡ ይህ ማዕቀብ ከአንድ ሳምንት በኋላ የሚጠናቀቅ ቢሆንም ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን ማዕቀቡ ለተጨማሪ አንድ ዓመት እንዲራዘም መፈረማቸውን አስታውቀዋል፡፡ አሜሪካ ማዕቀቡን ለአንድ ዓመት ያራዘመችው በኢትዮጵያ ያለው ሁኔታ አሁንም ከኢትዮጵያ በተጨማሪ ለምስራቅ አፍሪካ እና ለአሜሪካ የውጭ ጉዳዮች ፖሊሲ…
Read More
ኢትዮጵያ የመዳረሻ ቪዛን ከሚቀጥለው ሳምንት ጀምሮ መስጠት እንደምትጀምር ገለጸች

ኢትዮጵያ የመዳረሻ ቪዛን ከሚቀጥለው ሳምንት ጀምሮ መስጠት እንደምትጀምር ገለጸች

ኢትዮጵያ የመዳረሻ ቪዛ አገልግሎት ለውጭ ሀገራት ጎብኚዎች ከሁለት ዓመት በፊት መስጠት የጀመረች ቢሆንም በኮሮና ቫይረስ እና በሌሎች ምክንያቶች ተቋርጦ ቆይቷል፡፡ የጎብኚዎችን ቁጥር ከፍ እንደሚያደርግ የሚገለጸው የመዳረሻ ቮዛ አገልግሎት ከመስከረም 15 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ እንደሚሰጥ ተገልጿል፡፡ ይህ በዚህ እንዳለ ኢትዮጵያ 190 ሺህ ፓስፖርት ከውጪ ሀገር በማሳተም ወደ ሀገር ውስጥ ማስገባቷን ገልጻለች፡፡ የኢምግሬሽን እና ዝግጅት አገልግሎት ከሙስና ጋር በተያያዘ ሁሉንም ከፍተኛ አመራሮች ከሀላፊነት በማንሳት አዲስ አመራር ከአንድ ወር በፊት ተሾሞለታል። ባሳለፍነው ሀምሌ ወር ላይ ተቋሙን በሀላፊነት እንዲመሩ በጠቅላይ ሚኒስትር አቢይ አህመድ (ዶ/ር) የተሾሙት ወ/ሮ ሰላማዊት ዳዊት በጉዳዩ ዙሪያ መግለጫ ሰጥተዋል፡፡ ዋና ዳይሬክተሯ በመግለጫቸው 300 ሺህ ዜጎች ፓስፖርት ለማግኘት ተመዝግበው እየተጠባበቁ መሆኑን…
Read More
በአማራ ክልል በአንድ ቀን ብቻ ከ49 በላይ ንጹሃን ሰዎች መገደላቸው ተገለጸ

በአማራ ክልል በአንድ ቀን ብቻ ከ49 በላይ ንጹሃን ሰዎች መገደላቸው ተገለጸ

በአማራ ክልል ከትናንት በስቲያ ሰኞ ነሐሴ 29 ቀን 2015 የመንግሥት የጸጥታ አካላት በወሰዱት እርምጃ እንዲሁም በድሮን ጥቃት ከ49 በላይ ንጹሃን መገደላቸውን እናት ፓርቲ ባወጣው መግለጫ አስታውቋል። ፓርቲው በመግለጫው ሰኞ ነሐሴ 29 ቀን 2015 በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ማጀቴ ከተማ የመንግሥት ወታደሮች በወሰዱት እርምጃ 29 ንጹሃን ዜጎች በየመኖሪያ ቤታቸው በአሰቃቂ ሁኔታ ተገድለዋል ብሏል፡፡ "ከሟቾች ውስጥም ሕጻናት፣ ወጣቶች እና አረጋውያን እንዳሉበት ከመረጃ ምንጮቻችን አረጋግጠናል።" ያለው ፓርቲው  "በተመሳሳይ ነሐሴ 29 ቀን 2015 በምስራቅ ጎጃም ዞን ቢቡኝ ወረዳ፣ ሞሰባ ሽሜ አቦ ቀበሌ አዳራሽ ጎጥ ላይ መንግሥት በፈጸመው የድሮን ጥቃት ከ11 በላይ ንጹሐን ዜጎች ተጨፍጭፈዋል።" ብሏል። በዚሁ ቀን በምዕራብ ጎጃም ዞን ደጋ ዳሞት ወረዳ…
Read More