ኢኮኖሚ

የሕዳሴው ግድብ አራተኛ ዙር የውሀ ሙሌት ተጠናቀቀ

የሕዳሴው ግድብ አራተኛ ዙር የውሀ ሙሌት ተጠናቀቀ

የግድቡ አራተኛ እና ና የመጨረሻ ሙሌት መጠናቀቁን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ተናግረዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ  "የሕዳሴው ግድብን አራተኛና የመጨረሻ ሙሌት በተሳካ ሁኔታ መጠናቀቁን ሳበስር በታላቅ ደስታ ነው፤  ኢትዮጵያውያን ተባብረን በመሥራታችን ፈጣሪ ረድቶናል። " በማለት የግድቡ የመጨረሻ ሙሌት መጠናቀቁን አስታውቀዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ባሰፈሩት መልዕክት፤ "በገንዘባቸው፣ በዕውቀታቸው፣ በጉልበታቸውና በጸሎታቸው በስራው ውስጥ የተሳተፋችሁ ሁሉ  እንኳን ደስ አላችሁ፤ ይህ ኅብረታችን በሌሎች ጉዳዮቻችንም ሊደገም ይገባዋል" ብለዋል። ከ12 ዓመት በፊት የተጀመረው የታላቂ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ አጠቃላይ ግንባታው 91 በመቶ ደርሷል ተብሏብ። ኢትዮጵያዊያን በሚያዋጡት ገንዘብ እነ በመንግስት ወጪ እየተገነባ ያለው ይህ ግድብ በ5ሺህ 200 ሜጋ ዋት ሀይል በማመንጨት ከአፍሪካ ትልቁ ፕሮጀክት ነው። የህዳሴው…
Read More
አሜሪካ በኢትዮጵያ ላይ ጥላው የነበረውን የኢኮኖሚ ማዕቀብ አራዘመች

አሜሪካ በኢትዮጵያ ላይ ጥላው የነበረውን የኢኮኖሚ ማዕቀብ አራዘመች

አሜሪካ ከሁለት ዓመት በፊት የተቀሰቃሰው የሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት የአሜሪካንን የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ይጎዳል በሚል ነበር ጦርነቱ እንዲቆም ጫና ስታደርግ የቆየችው፡፡ ይህ ጦርነት ከኢትዮጵያ በተጨማሪ ምስራቅ አፍሪካን ይጎዳል የምትለው አሜሪካ ጦርነቱ እንዲቆም የተለያዩ ጫናዎችን ያደረገች ሲሆን የሰብዓዊ መብት ጥሰት ተፈጽሟል በሚል የተለያዩ እርምጃዎችን ስትወስድ ቆይታለች፡፡ በዋሸንግተን ከተወሰዱ እርምጃዎች መካከል በኢትዮጵያ ላይ ብሔራዊ የአስቸኳይ ጊዜ ማዕቀብ የሚባል ሲሆን በፈረንጆቹ መስከረም 2021 ላይ ለሁለት ዓመት የሚቆይ ማዕቀብ ተጥሏል፡፡ ይህ ማዕቀብ ከአንድ ሳምንት በኋላ የሚጠናቀቅ ቢሆንም ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን ማዕቀቡ ለተጨማሪ አንድ ዓመት እንዲራዘም መፈረማቸውን አስታውቀዋል፡፡ አሜሪካ ማዕቀቡን ለአንድ ዓመት ያራዘመችው በኢትዮጵያ ያለው ሁኔታ አሁንም ከኢትዮጵያ በተጨማሪ ለምስራቅ አፍሪካ እና ለአሜሪካ የውጭ ጉዳዮች ፖሊሲ…
Read More
ኢትዮጵያ የመዳረሻ ቪዛን ከሚቀጥለው ሳምንት ጀምሮ መስጠት እንደምትጀምር ገለጸች

ኢትዮጵያ የመዳረሻ ቪዛን ከሚቀጥለው ሳምንት ጀምሮ መስጠት እንደምትጀምር ገለጸች

ኢትዮጵያ የመዳረሻ ቪዛ አገልግሎት ለውጭ ሀገራት ጎብኚዎች ከሁለት ዓመት በፊት መስጠት የጀመረች ቢሆንም በኮሮና ቫይረስ እና በሌሎች ምክንያቶች ተቋርጦ ቆይቷል፡፡ የጎብኚዎችን ቁጥር ከፍ እንደሚያደርግ የሚገለጸው የመዳረሻ ቮዛ አገልግሎት ከመስከረም 15 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ እንደሚሰጥ ተገልጿል፡፡ ይህ በዚህ እንዳለ ኢትዮጵያ 190 ሺህ ፓስፖርት ከውጪ ሀገር በማሳተም ወደ ሀገር ውስጥ ማስገባቷን ገልጻለች፡፡ የኢምግሬሽን እና ዝግጅት አገልግሎት ከሙስና ጋር በተያያዘ ሁሉንም ከፍተኛ አመራሮች ከሀላፊነት በማንሳት አዲስ አመራር ከአንድ ወር በፊት ተሾሞለታል። ባሳለፍነው ሀምሌ ወር ላይ ተቋሙን በሀላፊነት እንዲመሩ በጠቅላይ ሚኒስትር አቢይ አህመድ (ዶ/ር) የተሾሙት ወ/ሮ ሰላማዊት ዳዊት በጉዳዩ ዙሪያ መግለጫ ሰጥተዋል፡፡ ዋና ዳይሬክተሯ በመግለጫቸው 300 ሺህ ዜጎች ፓስፖርት ለማግኘት ተመዝግበው እየተጠባበቁ መሆኑን…
Read More
ሸራተን ሆቴል የድምጻዊ ሬማ አዲስ ዓመት ዋዜማ ኮንሰርትን ሰረዘ

ሸራተን ሆቴል የድምጻዊ ሬማ አዲስ ዓመት ዋዜማ ኮንሰርትን ሰረዘ

የ2016 አዲስ ዓመትን አስመልክቶ በሸራተን አዲስ ሆቴል የሙዚቃ ድግስ መዘጋጀቱን የሚገልጹ ማስታወቂያዎች ሲተላለፉ ሰንብተዋል፡፡ በዚህ የአዲስ ዓመት ዋዜማ ላይ የሙዚቃ ስራዎቻቸውን የሚያቀርቡ ድምጻዊያን የማስታወቂያው አንድ አካል የነበሩ ሲሆን ናይጀሪያዊው ዲቫይን ኢኩቦር ወይም በቅጽል ስሙ ሪማ በመባል የሚታወቀው ድምጻዊ ከሌሎች ኢትዮጵያዊያን ድምጻዊያን ጋር በመድረኩ ላይ እንደሚዘፍኑ ተገልጾም ነበር፡፡ ይሁንና ድምጻዊ ሬማ ከክርስትና ሀይማኖት ጋር በተያያዘ ያልተገባ ነገር አድርጓል በሚል ይህን የአዲስ ዓመት ዋዜማ የሙዚቃ ድግስ ላይ ላለመገኘት በማህበራዊ የትስስር ገጾች ላይ ቅስቀሳ ሲደረግ ሰንብቷል፡፡ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያንም በይፋ የቤተ ክርስቲያን በዓላት ሲደርሱ ከሥርዓቷ እና ከአስተምሮዋ ውጪ በ ሆነ መልኩ የተለያዩ አካላት የዳንኪራ ጥሪ በማዘጋጀት የሚያደርጉት እንቅስቃሴ አግባብነት የሌለው መሆኑን…
Read More
አርቲስቶች እና ስፖንሰሮች የአዲስ ዓመት ዋዜማ ሙዚቃ ኮንሰርቶችን ሰረዙ

አርቲስቶች እና ስፖንሰሮች የአዲስ ዓመት ዋዜማ ሙዚቃ ኮንሰርቶችን ሰረዙ

ኢትዮጵያ የ2016 አዲስ ዓመትን ከአምስት ቀናት በኋላ የምታከብር ሲሆን በበዓሉ ዋዜማ የሙዚቃ ኮንሰርቶች ተዘጋጅተዋል። የአዲስ ዓመት ዋዜማ ዕለት ከሚዘጋጁ የሙዚቃ ድግሶች መካከል በአዲስ አበባ ሸራተን ሆቴል የተዘጋጀው አንዱ ነበር። በዚህ የሙዚቃ ኮንሰርት ላይ የውጭ ሀገራት እና ኢትዮጵያዊያን ሙዚቀኞች ስራዎቻቸውን እንደሚያቀርቡ ማስታወቂያዎች በሚዲያዎች በመተላለፍ ላይ ናቸው። ናይጀሪያዊው ዲቫይን ኢኩቦር ወይም በቅጽል ስሙ ሪማ በመባል የሚታወቀው ድምጻዊ ፣ ከሀገር ውስጥ ደግሞ ልጅ ሚካኤል፣ ኩኩ ሰብስቤ እና ሌሎችን ድምጻዊያን በዚህ የአዲስ ዓመት ኮንሰርት ላይ የሙዚቃ ስራቸውን እንደሚያቀርቡ ተገልጾ ነበር። ይሁንና ድምጻዊ ሬማ የክርስትና እምነት ላይ ከዚህ በፊት አሹፏል በሚል የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን አማኞች በዚህ ኮንሰርት ላይ እንዳይገኙ መልዕክት ማስተላለፏን ተከትሎ በርካቶች…
Read More
በኢትዮጵያ የውጭ ሀገራት ገንዘቦችን በማተም ወንጀል የተጠረጠሩ ቻይናዊያን በቁጥጥር ስር ዋሉ

በኢትዮጵያ የውጭ ሀገራት ገንዘቦችን በማተም ወንጀል የተጠረጠሩ ቻይናዊያን በቁጥጥር ስር ዋሉ

በርካታ መጠን ያላቸው የውጭ ሀገራት ገንዘቦችን በማተምና ጥቁር ገበያን በማስፋፋት ወንጀል የተጠረጠሩ ግለሰቦች ፍርድ ቤት ቀረቡ። ተጠርጣሪዎቹ በፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ ተረኛ ጊዜ ቀጠሮ ችሎት ቀርበው ጉዳያቸው ታይቷል። በኢትዮጵያ መዲና አዲስ አበባ ቻይናዊያን ባለሀብቶች ንብረት የሆነው ፀሃይ ሪል ስቴት በዚህ ወንጀል እጁ እንዳለበት ፖሊስ ገልጿል። ፖሊስ የሪል ኢስቴቱ ዋና ስራ አስኪያጅ ኪያ ዦንግን ጨምሮ ዘጠኝ የውጭ ሀገራት ዜጎችን በቁጥጥር ስር ማዋሉን አስታውቋል። ፖሊስ በህገወጥ የገንዘብ ዝውውር ወንጀል ጠርጥሮ በቁጥጥር ስር ካዋላቸው የውጭ ሀገራት ዜጎች ውስጥ ሶስት ኢትዮጵውያን ተጠርጣሪዎችም ተይዘዋል። ፖሊስ ሁሉንም ተጠርጣሪዎችን ፍርድ ቤት አቅርቦ ተጨማሪ ምርመራዎችን ለማድረግ የ14 ቀናት ጊዜ ቀጠሮ እንዲሰጠው ፍርድ ቤቱን ጠይቋል። ፖሊስ…
Read More
የመጀመሪያው የአፍሪካ የአየር ንብረት ጉባኤ በናይሮቢ መካሄድ ጀመረ

የመጀመሪያው የአፍሪካ የአየር ንብረት ጉባኤ በናይሮቢ መካሄድ ጀመረ

ከድርቅ ጀምሮ እስከ በርሃማነት በተደቀነባት የአፍሪካ አህጉር የወደፊት እጣ ፋንታ ላይ የሚመክር የአየር ንብረት ጉባኤ በናይሮቢ መካሄድ ጀምሯል። በኬንያ አስተናጋጅነት የሚካሄደው ጉባኤ ከዛሬ ጀምሮ ለሶስት ቀናት ይካሄዳልብተብሏል። በጉባኤው ላይ ከ20 ቡላይ የአፍሪካ መሪዎች፣ የበርካታ ሀገራት ሚንስትሮች፣ ልዑኮችና የአየር ንብረት ተሟጋቾች ይሳተፋሉ። በአህጉሪቱ እንደ ኢትዮጵያ፣ ሶማሊያና ኬንያ ባሉ ሀገራት ከ40 ዓመታት ወዲህ የከፋ የተባለ ድርቅ ተከስቷል። በዚህም በአፍሪካ ቀንድ እና በሌሎች የአፍሪካ ሀገራት የምግብ ዋስትና ቀውስ የተከሰተ ሲሆን፤ 10 ሚሊዮን የሚሆኑ እንስሳት ሞተዋል። የአፍሪካ ልማት ባንክ እንደሚለው እየጨመረ ከመጣው የአየር ንብረት ለውጥ ጋር በተያያዘ በሚከሰቱ አደጋዎች ሀገራት በየዓመቱ ከሰባት እስከ 15 ቢሊዮን ዶላር የሚገመት ሀብታቸውን ያጣሉ። የአየር ንብረት ለውጥን መከላከል ካልተቻለ…
Read More
እስራኤል ሁከት የፈጠሩ ኤርትራዊያንን ለማባረር ወሰነች

እስራኤል ሁከት የፈጠሩ ኤርትራዊያንን ለማባረር ወሰነች

የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ በቴላቪቭ በሃይለኛ ግጭት ውስጥ የተሳተፉ ኤርትራውያን በአስቸኳይ እንዲባረሩ እንደሚፈልጉ ገልፀዋል። የሀገሪቱን አፍሪካውያን ስደተኞች በሙሉ ለማስወገድ እቅድ ማውጣታቸውን አስታውቀዋል። ይህንን አስተያየት ጠቅላይ ሚኒስትሩ የሰጡት በደቡባዊ ቴል አቪቭ በኤርትራ ተቀናቃኝ ቡድኖች መካከል በነበረ ደም አፋሳሽ ግጭት በርካታ ሰዎች ላይ ጉዳት ከደረሰ  ከአንድ ቀን በኋላ ነበር። ኔታንያሁ የተከሰተውን ሁከት ተከትሎ በትላንትናው እለት በተጠራው ልዩ የሚኒስትሮች ስብሰባ ላይ “በሁከት ፈጣሪዎች ላይ ከባድ እርምጃዎችን እንፈልጋለን ፣ የተሳተፉትን ወዲያውኑ ወደ መጡበት መመለስ እንፈልጋለን” ብለዋል ። ሚኒስትሮቹ “ሌሎች ህገወጥ ሰርጎ ገቦችን ለማስወገድ” እቅድ እንዲያቀርቡላቸው የጠየቁ ሲሆን ጠቅላይ ፍርድ ቤቱ ስደተኞቹን ለቀው እንዲወጡ ለማስገደድ የታቀዱ አንዳንድ እርምጃዎችን መተላለፉን በንግግራቸው አስታውቀዋል። በአለም አቀፍ ህግ…
Read More
በአሶሳ ዞን የወርቅ ማዕድን ማውጫ ተደርምሶ የስድስት ሰዎች ህይወት አለፈ

በአሶሳ ዞን የወርቅ ማዕድን ማውጫ ተደርምሶ የስድስት ሰዎች ህይወት አለፈ

በአሶሳ ዞን በመንጌ ወረዳ ሸጎል ቀበሌ  አሚር ካምፕ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ የወርቅ ማዕድን ማውጫ ተደርምሶ የስድስት ሰዎች ህይወት ማለፉን የወረዳው ፖሊስ ገልጿል። ነሃሴ 24 ቀን 2015 ዓ.ም ከቀኑ 7 ሰዓት ገደማ በአካባቢው ለወርቅ ማዕድን ማውጣት ስራ ጉድጓድ በመቆፈር ላይ ከነበሩ ዘጠኝ ግለሰቦች መካከል የስድስት ሰዎች ህይወት ማለፉን የመንጌ ወረዳ ፖሊስ ጽህፈት ቤት አዛዥ ረዳት ኢንስፔክተር አሳድቅ አብዱልፈታህ ተናግረዋል። ቀሪ ሶስት ሰዎች ደግሞ በአደጋው ቀላል እና ከባድ ጉዳት ደርሶባቸዋል የተባለ ሲሆን ተጎጂዎች በመንጌ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል እና በአሶሳ አጠቃላይ ሆስፒታል የህክምና እርዳታ እየተደረገላቸው ይገኛል ብለዋል። በወቅቱ ግለሰቦችን በህይወት ለመታደግ በሰውና በመኪና የታገዘ ጥረት ቢደረግም ቦታው አስቸጋሪ ከመሆኑ የተነሳ መታደግ እንዳልተቻለ ተናግረዋል።…
Read More
ኢትዮጵያ የሲንጋፖር ኩባንያን ወደ ሀገሯ እንዲመጣ ጋበዘች

ኢትዮጵያ የሲንጋፖር ኩባንያን ወደ ሀገሯ እንዲመጣ ጋበዘች

የሲንጋፖር የወደብ ባለስልጣን በኢትዮጵያ በሎጀስቲክስ ኢንቨስትመንት እንዲሰማራ ጥሪ ቀረበ ዓለም አቀፍ የእስያ ኩባንያዎችን ወደ ኢትዮጵያ እንዲመጡ እና ኢንቨስት እንዲያደርጉ ለማሳመን የኢትዮጵያ ከፍተኛ ባለስልጣናት ሲንጋፖርን በመጎብኘት ላይ ናቸው፡፡ የኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር ሌሊሴ ነሜ ከኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈፃሚ አክሊሉ ታደሰ ጋር በመሆን ሲንጋፖር የሚገኘውን የሲንጋፖር የወደብ ባለስልጣን ጎብኝተዋል። ሁለቱ የኢንቨስትመንት አመራሮች ከሲንጋፖር ወደብ ባለስልጣን ኃላፊዎች ጋር ውይይት አድርገዋል። በውይይቱም የሲንጋፖር የወደብ ባለስልጣን በኢትዮጵያ በሎጀስቲክስ ኢንቨስትመንት እንዲሰማራ ጠይቀዋል። የኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር ሌሊሴ ነሜ፣ ኢትዮጵያ በዘርፉ ያላትን ከፍተኛ ፍላጎት ገልፀው ባለስልጣኑ በኢትዮጵያ በኢንቨስትመንት የሚሰማራበትንና ልምድ የሚያካፍልበት መንገድ እንዲኖር ጥሪ አቅርበዋል። የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈፃሚ አክሊሉ ታደሰ በበኩላቸው ፈጣን…
Read More