ኢኮኖሚ

ዳሸን ባንክ ከሁለት የአውሮፓ ባንኮች 40 ሚሊዮን ዶላር ብድር አገኘ

ዳሸን ባንክ ከሁለት የአውሮፓ ባንኮች 40 ሚሊዮን ዶላር ብድር አገኘ

ዳሸን ባንክ ከእንግሊዝ እና ኔዘርላንድ ባንኮች 40 ሚሊዮን ዶላር ብድር አገኘ የእንግሊዝ ዓለም አቀፍ ኢንቨስትመንት (ቢ አይ አይ) እና የኔዘርላንድ የሥራ ፈጠራና ልማት ባንክ የሆነው (ኤፍ ኤም ኦ) እያንዳንዳቸው 20 ሚሊየን ዶላር በድምሩ 40 ሚሊየን ዶላር ብድር ለዳሸን ባንክ ማቅረባቸውን ይፋ አድርገዋል፡፡ የብድር አቅርቦቱ ኢትዮጵያ ለውጪ ገበያ የምታቀርበውን የግብርና ምርት ለማሳደግ እና በእጅጉ አስፈላጊ የሆነውን የውጪ ምንዛሬ አቅርቦት ለማሻሻል እንደሚያስችል ተመላክቷል፡፡ ቢ አይ አይ እና ኤፍኤምኦ ለዳሸን ባንክ ያቀረቡት ገንዘብ በኢትዮጵያ 80 በመቶ የህብረተሰብ ክፍል በተሰማራበት፣ ለጠቅላላ የአገር ውስጥ ምርት 39 በመቶ ድርሻ ላለው እና ለወጪ ንግዱ 90 በመቶ አስተዋጽኦ ለሚያበረክተው የግብርና ዘርፍ ከፍተኛ እገዛ እንደሚኖረውም ታምኖበታል፡፡ የቀረበው ብድር ባንኩ…
Read More
የዓለም ባንክ ለኢትዮ-ጅቡቲ መንገድ 730 ሚሊዮን ዶላር ሰጠ

የዓለም ባንክ ለኢትዮ-ጅቡቲ መንገድ 730 ሚሊዮን ዶላር ሰጠ

የገንዘብ ሚኒስቴርና የዓለም ባንክ ለአፍሪካ ቀጣናዊ የኢኮኖሚ ኮሪደር ፕሮጀክት (በኢትዮ-ጅቡቲ ኮሪደር ፕሮጀክት) የ730 ሚሊዮን ዶላር የድጋፍ ስምምነት መፈራረማቸው ይፋ ተደርጓል። ፕሮጀክቱ የኢትዮጵያን 90 በመቶ የባህር ንግድን የሚይዘው ስትራቴጂካዊው ከአዲስ አበባ-ጅቡቲ ኮሪደር ጋር በተሳሰረ መልኩ የኢትዮጵያን የሎጅስቲክስና የትስስር አቅም እንደሚያጎለብት ተጠቁሟል። በስምምነቱ መሰረት ለሜኦሶ-ድሬዳዋ መንገድ ግንባታ የፋይናንስ ድጋፍ የሚደረግ ሲሆን፤ ግንባታው የትራንስፖርት አቅምና ብቃት የሚጨምር መሆኑን የገንዘብ ሚኒስቴር አስታውቋል። መንገዱ በሚገነባባቸው አካባቢዎች የሚገኙ ዜጎች የጤና፣ ውሃና ትምህርት አገልግሎት ተደራሽነት ጨምሮ ሌሎች መሰረተ ልማቶች ድጋፍ እንደሚደረግም ተመላክቷል። ፕሮጀክቱ የአፍሪካ ቀንድ ኢኒሺዬቲቭ አካልና የቀጣናዊ ትብብር ማዕቀፍ እንደሆነ ያመለከተው ሚኒስቴሩ፤ ማዕቀፉ አካባቢውን በመሰረተ ልማት የማስተሳሰር ፋይዳም እንዳለው ተጠቅሷል። ስምምነቱን የተፈራረሙትም የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ…
Read More
አዲስ አበባ ቀጣዩን የህዳሴው ግድብ የሶስትዮሽ ድርድር እንድታካሂድ ተመረጠች

አዲስ አበባ ቀጣዩን የህዳሴው ግድብ የሶስትዮሽ ድርድር እንድታካሂድ ተመረጠች

የህዳሴው ግድብ የቴክኒክ ባለሙያዎች የሶስትዮሽ ድርድር ባለፉት ሁለት ቀናት በግብጽ ካይሮ መካሄዱን የውጭ ጉዳይ ሚንስቴር አስታውቋል። ኢትዮጵያ በድንበር ተሻጋሪው አባይ ወንዝ ላይ እየገነባችው ያለው ታላቁ የህዳሴ ግድብ የሶስትዮሽ ድርድር በተለያዩ ምክንያቶች መቋረጡ ይታወሳል። ኢትዮጵያ፣ ግብጽ እና ሱዳን በአፍሪካ ህብረት አደራዳሪነት የሶስትዮሽ ድርድር  ሲያካሂዱ ቆይተዋል። በሱዳን እና በኢትዮጵያ የተከሰተው የፖለቲካ አለመረጋጋት ለሶስትዮሽ ድርድር አለመቀጠል እና የግብጽ ተለዋዋጭ አቋም ማሳየት ለድርድሩ አለመሳካት ዋነኞቹ ምክንያቶች ነበሩ። ከአንድ ወር በፊት በግብጽ ካይሮ በሱዳን ለተከሰተው ጦርነት እልባት ለመፈለግ በሚል በተካሄደው የጎረቤት ሀገራት መድረክ ላይ ለመሳተፍ ወደ ስፍራው ያቀኑት ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ (ዶ/ር) እግረ መንገዳቸውን ከፕሬዝዳንት አብዱልፈታህ  አልሲሲ ጋር መክረዋል። ሁለቱ መሪዎች ከተወያዩባቸው ጉዳዮች መካከልም…
Read More
የህዳሴው ግድብ የሶስትዮሽ ድርድር በግብጽ ተጀመረ

የህዳሴው ግድብ የሶስትዮሽ ድርድር በግብጽ ተጀመረ

ኢትዮጵያ በድንበር ተሻጋሪው አባይ ወንዝ ላይ እየገነባችው ያለው ታላቁ የህዳሴ ግድብ የሶስትዮሽ ድርድር በተለያዩ ምክንያቶች መቋረጡ ይታወሳል። በአፍሪካ ህብረት አደራዳሪነት ሲካሄድ የቆየው ይህ የሶስትዮሽ ድርድር በኢትዮጵያ ፣ ግብጽ እና ሱዳን መካከል ሲካሄድ ቆይቷል። በሱዳን እና በኢትዮጵያ የተከሰተው የፖለቲካ አለመረጋጋት ለሶስትዮሽ ድርድር አለመቀጠል እና የግብጽ ተለዋዋጭ አቋም ማሳየት ለድርድሩ አለመሳካት ዋነኞቹ ምክንያቶች ነበሩ። ከአንድ ወር በፊት በግብጽ ካይሮ በሱዳን ለተከሰተውን ጦርነት እልባት ለመፈለግ በሚል በተካሄደው የጎረቤት ሀገራት መድረክ ላይ ለመሳተፍ ወደ ስፍራው ያቀኑት ጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ (ዶ/ር) እግረ መንገዳቸውን ከፕሬዝዳንት አብዱል ፋታህ አልሲሲ ጋር መክረዋል። ሁለቱ መሪዎች ከተወያዩባቸው ጉዳዮች መካከልም የህዳሴው ግድብ ጉዳይ ዋነኛው ሲሆን በሶስት ወራት ውስጥ ዳግም ድርድር…
Read More
ከኬንያ ላሙ ወደብ ሞያሌ- አዲስ አበባ የባቡር መስመር ሊገነባ እንደሆነ ተገለጸ

ከኬንያ ላሙ ወደብ ሞያሌ- አዲስ አበባ የባቡር መስመር ሊገነባ እንደሆነ ተገለጸ

ኬንያ ከኢትዮጵያ ጋር የሚያገናኛትን የባቡር መስመር በ14 ቢሊዮን ዶላር ልትዘረጋ መሆኑን አስታውቃለች፡፡ ኬንያ የምትዘረጋው ይህ ፈጣን የባቡር መስመር በኤሌክትሪክ የሚሰራ ሲሆን፤ መነሻውን ከህንድ ውቅያኖስ ላሙ ወደብ በማድረግ ኢትዮጵያን እና ደቡብ ሱዳንን እንደሚያገናኝ ብሉምበርግ ዘግቧል። በዓይነቱ ልዩ ነው የተባለው ይህ የባቡር መስመር በፈረንጆቹ 2025 ሥራ እንደሚጀመር እና 3 ሺሕ ከሎ ሜትር እንደሚረዝም ታውቋል፡፡ የባቡር መስመሩ መነሻውን ከህንድ ውቅያኖስ አድርጎ፣ በኬንያዋ ማዕከላዊ ከተማ ኦሲዮሎን በኩል፣ ናይሮቢን እና አዲስ አበባን በማገናኘት የመጨረሻም መዳረሻውን ደቡብ ሱዳን ጁባ እንደሚያደርግ ተነግሯል፡፡ ይህ ፈጣን የባቡር መስመር “ኢትዮጵያ በአሰብ እና ምጽዋ እንዲሁም ጅቡቲ ወደቦች ላይ ያላትን ጥገኝነት የሚቀንስ ነው” የተባለ ሲሆን፤ ሌሎች በርካታ ማህበራዊ፣ ፖለቲካዊ እና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳዎች…
Read More
አሸዋ ቴክኖሎጂ  ተጨማሪ የአክስዮን ሽያጭ ጀመረ

አሸዋ ቴክኖሎጂ ተጨማሪ የአክስዮን ሽያጭ ጀመረ

አክስዮን ገዢዎች  በ500 ሺ ብር  አክስዮን በስድስት አመት ውስጥ ከስድስት ሚልየን ብር በላይ እንደሚያገኙ ተገልጿል። አሸዋ ቴክኖሎጂ በሰው ሃብት አስተዳደር ፣ በሂሳብ መዝገብ አያያዝ  እና የቢዝነስ  ክንውኖችን ማቀላጠፊያ ሶፍትዌሮችን በማበልጸግ ወደ ስራ የገባ አገር በቀል ድርጅት ነው። የድርጅቱ ዋና ስራ አስፈጻሚ ዳንኤል በቀለ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ግለሰቦች እና ድርጅቶች አክስዮን  ገዝተው ትርፍ የሚጋሩበትን ለሶስት ወራት የሚቆይ የአክስዮን ሽያጭ መጀመሩን ተናግረዋል። የአንድ አክስዮን ዋጋ 2 ሺህ 500 ብር እየሸጠ ያለው አሸዋ ቴክኖሎጂ  ትንሹ አክስዮን 500 ሺህ ብር ሲሆን  ትልቁ አክስዮን ደግሞ 100 ሚልየን ብር እንደሆነ በጋዜጣዊ መግለጫው ላይ ተጠቅሷል። የአክስዮን ገዢዎች የገዙትን አክስዮን መጠን 50 በመቶውን ቅድሚያ መክፈል ይጠበቅባቸዋል የተባለ ሲሆን ቀሪ የአክስዮን ድርሻዎችን ደግሞ…
Read More
የብሪክስ መሪዎች ዓመታዊ ጉባኤ በደቡብ አፍሪካ መካሄድ ጀመረ

የብሪክስ መሪዎች ዓመታዊ ጉባኤ በደቡብ አፍሪካ መካሄድ ጀመረ

ከ15 ዓመት በፊት በብራዚል፣ ሩሲያ፣ሕንድ፣ ቻይና እና ደቡብ አፍሪካ የተመሰረተው ብሪክስ የዘንድሮውን ጉባኤ በጆሀንስበርግ በማካሄድ ላይ ይገኛል፡፡ በዚህ የመሪዎች ጉባኤ ላይ የቻይና ፕሬዝዳንት ሺ ፒንግ፣ የሕንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ፣ የብራዚል ፕሬዝዳንት ሉላ ዳ ሲልቫ እና የደቡብ አፍሪካ ፕሬዝዳንት ሲሪል ራማፎዛ ተገኝተዋል፡፡ ሩሲያ በውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ሰርጊ ላቭሮቭ የተወከለች ሲሆን ፕሬዝዳንት ፑቲን በበይነ መረብ ታግዘው ንግግር አድርገዋል፡፡ የጉባአው አዘጋጅ ደቡብ አፍሪካ ለ60 ሀገራት ግብዣ ያቀረቡ ሲሆን ሁሉም የአፍሪካ ሀገራት መሪዎች በጉባኤው ላይ እንዲገኙ መጋበዛቸውን ተናግረዋል፡፡ ኢትዮጵያን ጨምሮ ከ40 በላይ የዓለማችን ሀገራት የብሪክስ አባል ለመሆን ጥያቄ አቅርበዋል፡፡ ሳውዲ አረቢያ፣ ኢራን፣ የተባበሩት አረብ አምሬት፣ ግብጽ፣ አልጀሪያ እና ሌሎችም ሀገራት ብሪክስን ለመቀላቀል በይፋ…
Read More
በአማራ ክልል ከ50 በላይ ወረዳዎች ከመንግስት ቁጥጥር ውጪ መሆናቸው ተገለጸ

በአማራ ክልል ከ50 በላይ ወረዳዎች ከመንግስት ቁጥጥር ውጪ መሆናቸው ተገለጸ

በአማራ ክልል ባለዉ ጦርነት ምክንያት ክልሉ ከመንግሥት መዋቅር ውጪ ናቸው የተባሉ ወረዳዎች ይፋ ሆነዋል። መንግስት ከቁጥጥር ውጪ የሆኑ ወረዳዎች እና ከተማ አስተዳድር የባንክ ሂሳቦችን እንዳይንቀሳቀሱ እገዳ ጥሏል። ከሰሜን ሸዋ ወረዳዎች ውስጥ ሚዳ ወረሞ፣ መርሃቤቴ፣ አለም ከተማ ፣እነዋሪ፣ መንዝ ቀያ፣ መንዝ ላሎ፣ መንዝ፣ ማማ፣ መንዝ ሞላሌ ከተማ አስተዳድር፣ መንዝ ጌራ፣ ሲያደብር እና ዋዩ፣ እንሳሮ ፣ሞረትና ጅሩ ወረዳዎች ከመንግስት ቁጥጥር ውጪ ናቸው ተብሏል። ከሰሜን ወሎ ወረዳዎች ደግሞ ግዳን ወረዳ ፣እስታይሽ፣ ቡግና እና ሙጃ ወረዳዎች እንዲሁም ከደቡብ ወሎ ደፍሞ ወግዲ ወረዳ፣ ከለላ፣ መካነሰላም ፣ቦረና ፣ አማራ ሳይንት እና ዋድላ ደላንታ ወረዳዎች ከመንግስት ቁጥጥር ውጪ ናቸው የተባለ ሲሆን የመንግስት ተቋማት የባንክ ሂሳብ እንዳይንቀሳቀሱ እገዳ…
Read More
ኢትዮጵያ ከሀገር ውስጥ ጎብኚዎች 61 ቢሊዮን ብር ገቢ ማግኘቷ ተገለጸ

ኢትዮጵያ ከሀገር ውስጥ ጎብኚዎች 61 ቢሊዮን ብር ገቢ ማግኘቷ ተገለጸ

በ2015 በጀት ዓመት ከሀገር ውስጥ ጎብኚዎች 61 ነጥብ 1 ቢሊየን ብር ገቢ መገኘቱን የቱሪዝም ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡ የሚኒስቴሩ የኮሙኒኬሽንና የሕዝብ ግንኙነት ስራ አስፈፃሚ አለማየሁ ጌታቸው እንደገለጹት በተጠናቀቀው በጀት ዓመት የቱሪዝም ዘርፉን ለማነቃቃት በርካታ ስራዎች ተከናውነዋል፡፡ በተለይም አዳዲስ የቱሪስት መዳረሻዎችን ከማልማት እንዲሁም ነባሮችን ከማደስ እና ከመጠገን አንጻር ውጤታማ ስራዎች መሰራታቸውን አንስተዋል፡፡ የጮቄ ተራራ እና ወንጪ የኢኮ ቱሪዝም መዳረሻዎች በዓለም ቱሪዝም ድርጅት እውቅና እንዲያገኙ ማድረግ መቻሉንም አስታውሰዋል። በተለያዩ አካባቢዎች ተጨማሪ የኢኮ ቱሪዝም መዳረሻ ሊሆኑ የሚችሉ ቦታዎችን በጥናት የመለየት እና መረጃ የማሰባሰብ ስራ መከናወኑን ጠቅሰዋል፡፡ በበጀት ዓመቱም በርካታ ቁጥር ካላቸው የሀገር ውስጥ ጎብኚዎች 61 ነጥብ 1 ቢሊየን ብር በላይ ገቢ መገኘቱን ነው አቶ አለማየሁ…
Read More
ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ የአውሮፕላን ጥገና ፈቃድ ሰጠች

ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ የአውሮፕላን ጥገና ፈቃድ ሰጠች

የኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽን ባለስልጣን ለመጀመሪያ ጊዜ የአውሮፕላን ጥገና ፈቃድ ሰጥቷል፡፡ ባለስልጣኑ ዋን ኤም. አር.ኦ (One M.R.O) ለተሰኘ የግል ተቋም በታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ የሆነውን አውሮፕላን ጥገና ፈቃድ ሰጥቷል፡፡ በ2013 ዓ.ም የቢዝነስ ፈቃድ አውጥቶ የተቋቋመው ዋን ኤም. አር.ኦ የጥገና ፈቃድ ሰርትፊኬት ለማግኘት የበቃው ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ያዘጋጃቸውን አምስት ዓለም አቀፍ መስፈርቶች አሟልቷል በሚል ነው፡፡ ለተቋሙ የተሰጠው የጥገና ፈቃድ ቦይነግ 737 ክላሲክና ቦይንግ 737 ኔክስት ጄኔሬሽን የተባሉ ዘመናዊ አውሮፕላኖችን መጠገን ያስችለዋል ተብሏል፡፡ ዋን ኤም.አር ኦ. የጥራት ማረጋገጫና ደህንነት ማናጀር አቶ አንዱአለም ስለሺ ፤ ድርጅታቸው በአሁን ሰዓት ናይጄሪያ ላይ መሰረት አድርጎ በምዕራብ አፍሪካ ለሚገኙ የግል ኦፐሬተሮች የጥገና አገልግሎት እየሰጠ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ድርጅታቸው በቀጣይም በኢትዮጵያ…
Read More