አካባቢ ጥበቃ

የባቢሌ የዝሆኖች መጠለያ ከ200 ሄክታር በላይ መሬት ደን ወደመ

የባቢሌ የዝሆኖች መጠለያ ከ200 ሄክታር በላይ መሬት ደን ወደመ

በኦሮሚያ ክልል ምሥራቅ ሐረርጌ ዞን የሚገኘው የባቢሌ የዝሆኖች መጠለያ ለእርሻ ኢንቨስትመንት በመሰጠቱ ከ200 ሄክታር በላይ የፓርኩ መሬት ደን ሙሉ ለሙሉ መውደሙን የኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ጥበቃ ባለስልጣን ገልጿል፡፡ የኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ጥበቃ ባለስልጣን የብሔራዊ ፓርኮች አስተዳደር መሪ ሥራ አስፈጻሚ ዶክተር አዳነ ጸጋዬ፤ የባቢሌን የዝሆኖች መጠለያ ፓርክ በምሥራቅ ሐረርጌ ዞን በኩል ለእርሻ ኢንቨስትመንት ተሰጥቶ ፓርኩ እየታረሰ በመሆኑ፣ በፓርኩ የሚገኙ ዝሆኖች ለአደጋ ተጋልጠዋል ብለዋል፡፡ የባቢሌን የዝሆኖች መጠለያ በሶማሌ እና በኦሮሚያ ክልሎች ድንበር ላይ የሚገኝ ሲሆን "በኦሮሚያ ክልል በኩል ያለው የፓርኩ ክፍል ለኢንቨስትመንት በመሰጠቱ አሁንም ድረስ እየታረሰ ነው" ሲሉ ገልጸዋል። የፓርኩ መሬት ለኢንቨስትመንት የተሰጠው ፓርኮችን ለመጠበቅና ለማስተዳደር ኃላፊነት የተሰጠው የኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ጥበቃ ባለስልጣን…
Read More
የታላቁ ህዳሴ ግድብ አምስት ተርባይኖች በቅርቡ ሀይል ማመንጨት እንደሚጀምሩ ተገለጸ

የታላቁ ህዳሴ ግድብ አምስት ተርባይኖች በቅርቡ ሀይል ማመንጨት እንደሚጀምሩ ተገለጸ

በ2016 በሕዳሴው ግድብ አምስት ተጨማሪ ዩኒቶችን ሥራ ለማስጀመር እየተሠራ መሆኑን፤ የታላቁ የኢትዮጵያ የሕዳሴ ግድብ ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር ክፍሌ ሆሮ አስታውቀዋል፡፡ የሕዳሴ ግድቡ አራተኛ ዙር የውኃ ሙሌት መጠናቀቁን ተከትሎ፤ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድን ጨምሮ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች በተገኙበት የሙሌቱ መጠናቀቅ በይፋ ተበስሯል፡፡ በሥፍራው ለተገኙ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች ማብራሪያ የሰጡት የታላቁ የኢትዮጵያ የሕዳሴ ግድብ ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር ክፍሌ ሆሮ፤ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ 93 በመቶ መጠናቀቁን መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ግድቡ፤ ግራ፣ ቀኝ እና መካከለኛ አካል እንዳለው የተናገሩት ኢንጂነር ክፍሌ፤ ግራና ቀኙ የግድቡ ክፍል ከ635 እስከ 645 ደረጃ እንደሚሆን ተናግረዋል፡፡ የግራና ቀኙን ክፍል ለማጠናቀቅ ከዘጠኝ እስከ አሥር ሜትር ድረስ ብቻ እንደሚያስፈልግም አስታውቀዋል፡፡…
Read More
የሕዳሴው ግድብ አራተኛ ዙር የውሀ ሙሌት ተጠናቀቀ

የሕዳሴው ግድብ አራተኛ ዙር የውሀ ሙሌት ተጠናቀቀ

የግድቡ አራተኛ እና ና የመጨረሻ ሙሌት መጠናቀቁን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ተናግረዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ  "የሕዳሴው ግድብን አራተኛና የመጨረሻ ሙሌት በተሳካ ሁኔታ መጠናቀቁን ሳበስር በታላቅ ደስታ ነው፤  ኢትዮጵያውያን ተባብረን በመሥራታችን ፈጣሪ ረድቶናል። " በማለት የግድቡ የመጨረሻ ሙሌት መጠናቀቁን አስታውቀዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ባሰፈሩት መልዕክት፤ "በገንዘባቸው፣ በዕውቀታቸው፣ በጉልበታቸውና በጸሎታቸው በስራው ውስጥ የተሳተፋችሁ ሁሉ  እንኳን ደስ አላችሁ፤ ይህ ኅብረታችን በሌሎች ጉዳዮቻችንም ሊደገም ይገባዋል" ብለዋል። ከ12 ዓመት በፊት የተጀመረው የታላቂ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ አጠቃላይ ግንባታው 91 በመቶ ደርሷል ተብሏብ። ኢትዮጵያዊያን በሚያዋጡት ገንዘብ እነ በመንግስት ወጪ እየተገነባ ያለው ይህ ግድብ በ5ሺህ 200 ሜጋ ዋት ሀይል በማመንጨት ከአፍሪካ ትልቁ ፕሮጀክት ነው። የህዳሴው…
Read More
ኢትዮ ቴሌኮም በመላው አዲስ አበባ የ5G ኔትወርክ አገልግሎቱን ይፋ አደረገ

ኢትዮ ቴሌኮም በመላው አዲስ አበባ የ5G ኔትወርክ አገልግሎቱን ይፋ አደረገ

ኢትዮ ቴሌኮም የአምስተኛው ትውልድ (5G) የሞባይል አገልግሎትን በአዲስ አበባ በወዳጅነት አደባባይ በተካሄደ መርሃ ግብር በይፋ አስጀምሯል። በመርሃ ግብሩም ተቋሙ ከዚህ ቀደም በቅድመ ገበያ ሙከራ ደረጃ በአዲስ አባባ እና አዳማ ከተሞች አስጀምሮት የነበረውን የ5G የሞባይል አገልግሎት፤ በአዲስ አበባ የተለያዩ አካባቢዎች በሚገኙ በ145 ጣቢያዎች ማስጀመሩን አብስሯል። ይህ የ5G የሞባይል ኔትዎርክ አገልግሎት እስከ 10 ጊጋ ባይት በሰከንድ የሚደርስ ፍጥነት እንዳለው የተገለጸ ሲሆን፤ ዳታ የማስተላለፍ መዘግየትን እጅግ በላቀ ኹኔታ በመቀነስ ወደ 1 ሚሊ ሰከንድ ያደርሳል ተብላል። የ5G አገልግሎት በተለይም በተመሳሳይ ወቅት መከናወን የሚፈልጉ እንደ የማምረቻ ፋብሪካዎች፣ ግብርና፣ ሕክምና ለመሳሰሉ ዘርፎች የላቀ ፋይዳ እንዳለውም ተገልጿል። የ5G አገልግሎት ሥራ ላይ መዋል የማህበረሰቡን ሕይወት የሚያቀሉ ዲጂታል መፍትሄዎችን በቀላሉ…
Read More
የመጀመሪያው የአፍሪካ የአየር ንብረት ጉባኤ በናይሮቢ መካሄድ ጀመረ

የመጀመሪያው የአፍሪካ የአየር ንብረት ጉባኤ በናይሮቢ መካሄድ ጀመረ

ከድርቅ ጀምሮ እስከ በርሃማነት በተደቀነባት የአፍሪካ አህጉር የወደፊት እጣ ፋንታ ላይ የሚመክር የአየር ንብረት ጉባኤ በናይሮቢ መካሄድ ጀምሯል። በኬንያ አስተናጋጅነት የሚካሄደው ጉባኤ ከዛሬ ጀምሮ ለሶስት ቀናት ይካሄዳልብተብሏል። በጉባኤው ላይ ከ20 ቡላይ የአፍሪካ መሪዎች፣ የበርካታ ሀገራት ሚንስትሮች፣ ልዑኮችና የአየር ንብረት ተሟጋቾች ይሳተፋሉ። በአህጉሪቱ እንደ ኢትዮጵያ፣ ሶማሊያና ኬንያ ባሉ ሀገራት ከ40 ዓመታት ወዲህ የከፋ የተባለ ድርቅ ተከስቷል። በዚህም በአፍሪካ ቀንድ እና በሌሎች የአፍሪካ ሀገራት የምግብ ዋስትና ቀውስ የተከሰተ ሲሆን፤ 10 ሚሊዮን የሚሆኑ እንስሳት ሞተዋል። የአፍሪካ ልማት ባንክ እንደሚለው እየጨመረ ከመጣው የአየር ንብረት ለውጥ ጋር በተያያዘ በሚከሰቱ አደጋዎች ሀገራት በየዓመቱ ከሰባት እስከ 15 ቢሊዮን ዶላር የሚገመት ሀብታቸውን ያጣሉ። የአየር ንብረት ለውጥን መከላከል ካልተቻለ…
Read More
ኢትዮጵያ ከሀገር ውስጥ ጎብኚዎች 61 ቢሊዮን ብር ገቢ ማግኘቷ ተገለጸ

ኢትዮጵያ ከሀገር ውስጥ ጎብኚዎች 61 ቢሊዮን ብር ገቢ ማግኘቷ ተገለጸ

በ2015 በጀት ዓመት ከሀገር ውስጥ ጎብኚዎች 61 ነጥብ 1 ቢሊየን ብር ገቢ መገኘቱን የቱሪዝም ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡ የሚኒስቴሩ የኮሙኒኬሽንና የሕዝብ ግንኙነት ስራ አስፈፃሚ አለማየሁ ጌታቸው እንደገለጹት በተጠናቀቀው በጀት ዓመት የቱሪዝም ዘርፉን ለማነቃቃት በርካታ ስራዎች ተከናውነዋል፡፡ በተለይም አዳዲስ የቱሪስት መዳረሻዎችን ከማልማት እንዲሁም ነባሮችን ከማደስ እና ከመጠገን አንጻር ውጤታማ ስራዎች መሰራታቸውን አንስተዋል፡፡ የጮቄ ተራራ እና ወንጪ የኢኮ ቱሪዝም መዳረሻዎች በዓለም ቱሪዝም ድርጅት እውቅና እንዲያገኙ ማድረግ መቻሉንም አስታውሰዋል። በተለያዩ አካባቢዎች ተጨማሪ የኢኮ ቱሪዝም መዳረሻ ሊሆኑ የሚችሉ ቦታዎችን በጥናት የመለየት እና መረጃ የማሰባሰብ ስራ መከናወኑን ጠቅሰዋል፡፡ በበጀት ዓመቱም በርካታ ቁጥር ካላቸው የሀገር ውስጥ ጎብኚዎች 61 ነጥብ 1 ቢሊየን ብር በላይ ገቢ መገኘቱን ነው አቶ አለማየሁ…
Read More
የአፍሪካ ምግብ ዋስትና በአየር ንብረት ለውጥ ምክንያት ፈተና እንደገጠመው ተገለጸ

የአፍሪካ ምግብ ዋስትና በአየር ንብረት ለውጥ ምክንያት ፈተና እንደገጠመው ተገለጸ

19ኛው የአፍሪካ አካባቢ ጥበቃ ሚንስትሮች ጉባኤ የአፍሪካን ችግሮች ለመፍታት እድሎችን መጠቀም እና ትብብርን ማጎልበት" በሚል ሀሳብ በአዲስ አቡባ ተካሂዷል። በዚህ ጉባኤ ላይ አፍሪካ አካባቢ ጥበቃ ሚንስትሮች፣ የዘንድሮው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዓመታዊ የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ አዘጋጅ ሀገር ፕሬዝዳንት የሆኑት ዶክተር ሱልጣን አልጃቢር ተገኝተዋል። እንዲሁም የአካባቢ ጥበቃ ተቆርቋሪዎች፣ ተመራማሪዎች እና ተቋማት መሪዎች እንደተገኙ ተገልጿል። የኢትዮጵያ ምክትል ጠቅላይ ሚንስትር እና ውጪ ጉዳይ ሚንስትር ደመቀ መኮንን ባደረጉት የመክፈቻ ንግግር የአየር ንብረት ለውጥ የአፍሪካን የምግብ ዋስትና እየፈተነ ነው ብለዋል። አቶ ደመቀ አክለውም ኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥ ጉዳትን ለመከላከል እና ዘላቂ የኢኮኖሚ እድገት ለማስመዝገብ አረንጓዴ አሻራ ስትራቴጂ ነድፋ እየተገበረች መሆኗንም ጠቅሰዋል። የኮፕ28 አለም አቀፍ አየር…
Read More
ኢትዮጵያ ከቡና የምታገኘው ገቢ የ90 ሚሊዮን ዶላር ቅናሽ አሳየ

ኢትዮጵያ ከቡና የምታገኘው ገቢ የ90 ሚሊዮን ዶላር ቅናሽ አሳየ

ኢትዮጵያ ወደ ውጭ ሀገራት ከተላከ ቡና 1 ነጥብ 3 ቢሊዮን ዶላር ገቢ አግኝታለች። ኢትዮጵያ ለዓለም ገበያ የምታቀርበው የቡና ምርት መጠን ከዓመት ዓመት ማሽቆልቆሉን የኢትዮጵያ ቡና ላኪዎች ማህበር ገልጿል፡፡ የማህበሩ ዋና ሥራ አስኪያጅ ግዛት ወርቁ ኢትዮጵያ በ2014 ዓ. ም ለዓለም ገበያ ያቀረበችው የቡና መጠን 302 ሺሕ ቶን ነበር። በዘንድሮው ማለትም በ2015 ዓመት ግን 240 ሺሕ ቶን ብቻ ቡና ለዓለም ገበያ ማቅረቧን የኢትዮጵያ ቡና ላኪዎች ማህበር አስታውቋል። ወደ ውጪ ሀገራት የተላከው ቡና ከባለፈው ዓመት ለዓለም ገበያ ከቀረበው የቡና ምርት ጋር ሲንጻጸር በ62 ሺሕ ቶን ቅናሽ አሳይቷል ተብላል። ሥራ አስኪያጁ አክለውም፤ ኢትዮጵያ በዘንድሮው ዓመት ለዓለም ገበያ ካቀረበችው ቡና 1 ነጥብ 33 ቢሊዮን ዶላር…
Read More
ኢትዮጵያ በአንድ ቀን 567 ሚሊዮን ችግኞችን ተከለች

ኢትዮጵያ በአንድ ቀን 567 ሚሊዮን ችግኞችን ተከለች

ኢትዮጵያ በአንድ ቀን 567 ሚሊዮን ችግኞችን ተከለች ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ "በአንድ ቀን 567 ሚሊዮን ችግኞች ተተክሏል" ብለዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ በዛሬው እለት 567 ሚሊዮን ችግኞች መተከላቸውን ተናግረዋል። በአንድ ቀን 500ሺ ችግኝ የመትከል ዘመቻ አማካኝነት በሀገሪቱ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ችግኝ ሲተክሉ የሚያሳዩ ፎቶዎች እና ቪዲዮዎች ተለቀዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ የችግኝ ተከላው" ለኢትዮጵያ ትልቅ ስኬት" ነው ሲሉ ተናግረዋል። ኢትዮጵያ በዚህ አመት ብቻ ከካርቦን ሽያጭ 52 ሚሊዮን ዶላር ማግኘቷን የተናገሩት ጠቅላይ ሚኒስትሩ የችግኝ ተከላው ስራ በዚሁ ከቀጠለ ከካርቦን ሽያጭ የምታገኘው ገቢ በእጥፍ እንደሚጨምር ገልጸዋል። ይሁንና በአንድ ጀምበር ተተከለ የተባለው የችግኝ መጠን በትክክል ስለመተከሉ በገለልታኛ አካል አልተረጋገጠም።
Read More
ኢትዮጵያ እና ግብጽ በህዳሴ ግድቡ ዙሪያ በአራት ወራት ውስጥ ችግራቸውን ለመፍታት ተስማሙ

ኢትዮጵያ እና ግብጽ በህዳሴ ግድቡ ዙሪያ በአራት ወራት ውስጥ ችግራቸውን ለመፍታት ተስማሙ

ግብጽ በሱዳን ያለውን ጦርነት ለማስቆም ያለመ ውይይት የጎረቤት ሀገራት መሪዎችን መጋበዟ ይታወሳል። ኢትዮጵያን ጨምሮ የሱዳን ጎረቤት ሀገራት በመድረኩ ላይ ለመሳተፍ ወደ ካይሮ ያመሩ ሲሆን ጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ (ዶ/ር) ከውይይቱ በተጓዳኝ ከፕሬዝዳንት አብዱል ፋታህ አልሲሲ ጋር መወያየታቸው ተገልጿል። የሁለቱ ሀገራት መሪዎች በህዳሴ ግድቡ ዙሪያ መወያየታቸው ሲገለጽ የግድቡ ውሀ አሞላል ደግሞ የመሪዎቹ ዋነኛ መወያያ እንደሆነ ተገልጿል። በዚህ መሰረትም ኢትዮጵያ በግድቡ ውሀ አሞላል ዙሪያ ግብጽን እና ሱዳንን የመጉዳት ፍላጎት የላትም የተባለ ሲሆን በዚሁ ጉዳይ ዙሪያ ተጨማሪ ውይይቶችን ለማድረግ ስለመስማማታቸውም ተገልጿል። ኢትዮጵያ ፣ ግብጽ እና ሱዳንም በህዳሴው ግድብ ውሀ አሞላል እና ሌሎች ተያያዥ ጉዳዮች ዙሪያ ያለባቸውን አለመግባባት በአራት ወራት ውስጥ በሚያደርጉት ውይይት ወደ…
Read More