አካባቢ ጥበቃ

ኢትዮጵያ ለኤሌክትሪክ መኪኖች አዲስ መመሪያ አዘጋጀች

ኢትዮጵያ ለኤሌክትሪክ መኪኖች አዲስ መመሪያ አዘጋጀች

ለኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች ሃይል መሙያ ማሽን (ቻርጀር) መትከል የሚፈቅድ መመሪያ ጸደቀ መመሪያው በመንገዶች ግራና ቀኝ በየ50 ኪሎሜትር ልዩነት የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎችን መሙላት የሚችል ፈጣን ቻርጀር ጣቢያ ማቋቋም ይፈቅዳል፡፡ ይሁንና የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች ሃይል ማቅረብ የሚፈልጉ ተቋማት ከነዳጅ እና ኢነርጂ ባለስልጣን ፈቃድ በመውሰድ እንዳለባቸው መመሪያ ይገልጻል። በተለያዩ ተቋማት የሚተከሉ የኤሌክትሪክ ሃይል መሙያዎች ከባለስልጣኑ ፈቃድ ማግኘት እንደሚጠበቅባቸው ይደነግጋል፡፡ ነገር ግን በግል በቤት ውስጥ ከሚተከሉ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ ሃይል መሙሊያ ማሽኖች ፈቃድ መጠየቅ የማይጠበቅባቸው መሆኑን ያመላከተው የተቋሙ መረጃ ከዚህ ውጭ ግን ማናቸውም የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ ሃይል ሙሌት የሚሰጡ ማሽኖች መትከል የሚቻለው ከባለስልጣኑ ፈቃድ ሲያገኝ ብቻ መሆኑንም አመላክቷል። መመሪያው ለህዝብ በሽያጭ የኤሌክትሪክ ሃይል ሙሊት አገልግሎት የሚሰጡ ታሪፋቸው በባለስልጣኑ ሲጸድቅላቸው…
Read More
በኢትዮጵያ ባጋጠመው የመሬት መንቀጥቀጥ አደጋ 80 ሺህ ዜጎች እንደሚፈናቀሉ ተገለጸ

በኢትዮጵያ ባጋጠመው የመሬት መንቀጥቀጥ አደጋ 80 ሺህ ዜጎች እንደሚፈናቀሉ ተገለጸ

በኢትዮጵያ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የመሬት መንቀጥቀጥ አደጋዎች እየተደጋገሙ ሲሆን እስካሁን መኖሪያ ቤቶች ላይ የተወሰኑ ጉዳቶችን ከማድረስ የዘለለ ከባድ ጉዳት አላደረሱም፡፡ ባለፉት ሁለት ሳምንት ውስጥ ብቻ ከ30 ጊዜ በላይ በአፋር ክልል አዋሽ ከተማ አቅራቢያ የመሬት መንቀጥቀጥ አደጋዎች ያጋጠሙ ሲሆን በትናንትናው ዕለት ከ60 ዓመት በኋላ ከፍተኛ የጠባለ የመሬት መንቀጥቀጥ አደጋ አጋጥሟል፡፡ የአሜሪካ ጂኦሎጂካል ሰርቬይ ሪፖርት እንደገለጸው ከሆነ በሬክተር ስኬል 5 ነጥብ 8 የተመዘገበ የመሬት መንቀጥቀጥ አደጋ አጋጥሟል፡፡ በዚህ አደጋ ምክንያት በአፋር ክልል ባሉ መኖሪያ ቤቶች እና የመንግስት ተቋማት ላይ አነስተኛ ጉዳት ያጋጠመ ሲሆን ንዝረቱ አዲ አበባ ድረስ ተሰምቷል፡፡ የመንግስት ኮሚኒኬሽን አገልግሎት ባወጣው ማስታወቂያ የርዕደ መሬቱ ማዕከል ከሆኑ 12 ቀበሌዎች 80 ሺህ ዜጎችን ሊፈጠር…
Read More
በኢትዮጵያ ባንድ ቀን ውስጥ ከ14 ጊዜ በላይ የመሬት መንቀጥቀጥ አደጋ ተከሰተ

በኢትዮጵያ ባንድ ቀን ውስጥ ከ14 ጊዜ በላይ የመሬት መንቀጥቀጥ አደጋ ተከሰተ

በኢትዮጵያ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የመሬት መንቀጥቀጥ አደጋዎች እየተደጋገሙ ሲሆን እስካሁን መኖሪያ ቤቶች ላይ የተወሰኑ ጉዳቶችን ከማድረስ የዘለለ ከባድ ጉዳት አላደረሱም፡፡ አደጋው እያጋጠመ ያለው በአፋር ክልል አዋሽ ልዩ ስሙ ፈንታሌ አካባቢ እንደሆነ የአሜሪካ ጂኦሎጂካል ሰርቬይ ሪፖርት ያስረዳል፡፡ በአዋሽ ፈንታሌ እየተከሰተ ባለዉ ተደጋጋሚ ርዕደ መሬት ምክንያት ነዋሪዎች ከመኖሪያ ቤታቸው እየለቀቁ ሲሆን እስካሁን ከ2,500 በላይ ሰዎች ተፈናቅለዋል፡፡ ንዝረቱ አዲስ አበባ ድረስ በተሰማው የመሬት መንቀጥቀጥ አደጋዎች እስካሁን ከፍተኛው 5 በሬክተር ስኬል 5 የሆነ የመሬት መንቀጥቀጥ ነው። በአደጋው ከ100 በላይ ቤቶች ጉዳት የደረሰባቸዉ ሲሆን፤ 2 ሺሕ 560 ሰዎች መፈናቀላቸውን እና እንሰሳት መሞታቸውን የአዋሽ ፈንታሌ ወረዳ አስተዳደር አቶ አደም ባሂ ተናግረዋል። አስተዳዳሪው አክለውም በቀን ውስጥ እስከ…
Read More
በደን አጠባበቅ ላይ የተሻለ የፈጠራ ስራ ያቀረቡ ወጣቶች ተሸለሙ

በደን አጠባበቅ ላይ የተሻለ የፈጠራ ስራ ያቀረቡ ወጣቶች ተሸለሙ

ውድድሩ የኢትዮጵያ አየር ንብረት ለውጥ ትብብር፣ኢንፉሌንሰርስ እና ቬንደንስ የተሰኙ ተቋማት በጋራ አዘጋጅተውታል፡፡ ሶስቱ በአየር ንብረት ለውጥ ላይ የሚሰሩት ተቋማት ከሁለት ወራት በፊት ወጣቶች በደን አጠባበቅ ዙሪያ በኢሴይ ራይቲንግ፣ ኢንፎ ግራፊ እና ቪዲዮ የታገዘ ስራዎቻቸውን እንዲያቀርቡ ጥሪ አቅርበው ነበር፡፡ የኢንፉሌንሰርስ ኤክስኪዩቲቭ ዳይሬክተር ናሆም ፈቃዱ እንዳሉት በተደረገው ማስታወቂያ መሰረት 80 ወጣቶች በውድድሩ ላይ እንደተሳተፉ ተናግረዋል፡፡ ከሁሉም ተወዳዳሪዎች ውስጥ ከአንድ እስከ ሶስተኛ ደረጃ የወጡ ወጣት አሸናፊዎች  ከ10 ሺህ እስከ 20 ሺህ ብር ሽልማት ተሸልመዋል፡፡ ወጣት ናሆም እንዳሉት ተቋማቸው ኢንፉሌንሰርስ ሁሉም ሰው ለአካባቢ ጥበቃ የራሱን ድርሻ እንዲወጣ በሚል መቋቋሙን ተናግረዋል፡፡ ለአካባቢ ጥበቃ የራሳቸውን አስተዋጽኦ ማበርከት ለሚፈልጉ ሰዎች ነው የተቋቋመው፣የአየር ንብረት ለውጥ የባሰ ጉዳት የሚያደርሰው…
Read More
በኢትዮጵያ የአንበሳ እንስሳት የመጥፋት አደጋ ተደቅኖበታል ተባለ

በኢትዮጵያ የአንበሳ እንስሳት የመጥፋት አደጋ ተደቅኖበታል ተባለ

በኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ጥበቃ ባለስልጣን  የአንበሳ እና የስጋ በል እንስሳት ተመራማሪ የሆኑት አቶ ካህሳይ ገብረ-ተንሳይ  አሁን ላይ በኢትዮጵያ ያሉት አንበሶች ቁጥር ከ1 ሺ እንደማይበልጥ ተናግረዋል። በሃገሪቱ አሁን ላይ አንበሶች ያሉበት  ሁኔታ ለማወቅ ጥናት  ማድረጋቸውን የገለፁልን ተመራማሪው በአዋሽ  እና በመካከለኛው አዋሽ  በተደረገው ጥናት መሰረት ያለው ሁኔታ  ተስፋ ሰጪ ቢሆንም   አሁንም ግን ሁሉም ርብርብ ካላደረገ  አንበሶቹን ልናጣ እንችላለን ብለዋል፡፡ ተመራማሪው እንደሚሉትም ህገወጥ የነዋሪዎች ሰፈራ፣ የደን ጭፍጨፋ መኖር፣ የእርሻ ስራ እና  ግጦሽ  መበራከት አንበሶቹ  የሚፈልጉትን ምግብ እንዳያገኙና በምግብ ሰንሰለት ውስጥ ችግር እንዲፈጠር ብሎም ለህገወጥ አደን  በስፋት ተጋላጭ እንዲሆኑ አድርጓቸዋል ብለዋል። ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ  የባህል መድኃኒት ቀማሚዎች  ፊታቸውን ወደ አንበሳ አጥንት ማዞራቸው እንስሳቶቹን ለህገወጥ…
Read More
ኢትዮጵያ የፕላስቲክ ምርቶች መጠቀምን የሚከለክል ህግ አዘጋጀች

ኢትዮጵያ የፕላስቲክ ምርቶች መጠቀምን የሚከለክል ህግ አዘጋጀች

ኢትዮጵያ ለአንድ ጊዜ ግልጋሎት የሚውሉ የፕላስቲክ ምርቶች ሀገር ውስጥ እንዳይገቡ የሚከለክል ህግ አዘጋጀች፡፡ በጠቅላይ ሚኒስትሩ የሚመራው የሚኒስትሮች ምክር ቤት የፕላስቲክ ምርቶች አጠቃቀም ላይ ገደብ የሚጥል ረቂ ህግ ላይ ተወያይቷል፡፡ ምክር ቤቱ ባሳለፍነው ሳምንት ለአንድ ጊዜ ግልጋሎት የሚውሉ የፕላስቲክ ምርቶች ወደ ሀገር ውስጥ እንዳይገቡ የሚከለክል ረቂቅ አዋጅን አዘጋጅቷል፡፡ ረቂቅ አዋጁ ለዝርዝር እይታ እና ተጨማሪ ግብዓት ታክሎበት እንዲጸድቅ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ተመርቷል። ረቂቅ አዋጁ የሀገሪቱን የደረቅ ቆሻሻ አሰባሰብ፣ ማጓጓዝ፣ ክምችት፣ መልሶ አጠቃቀም፣ መልሶ ኡደት እና አወጋገድ ሥርዓት ማስያዝ ላይ ያተኮረ እንደሆነ የጠቅላይ ሚኒስቴር ጽህፈት ቤት አስታውቋል፡፡ የኢትዮጵያ የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ሌሊሴ ነሜ በበኩላቸው ለሀገሪቱ ፓርላማ የተመራው ይህ ረቂቅ አዋጅ፤…
Read More
የኢትዮጵያ ብርቅዬ የዱር እንስሳ የሆነው ዋልያ የመጥፋት አደጋ ተደቅኖበታል ተባለ

የኢትዮጵያ ብርቅዬ የዱር እንስሳ የሆነው ዋልያ የመጥፋት አደጋ ተደቅኖበታል ተባለ

በኢትዮጵያ ካሉ የዱር እንስሳት መጠለያዎች ውስጥ አንዱ በሆነው በ ሰሜን ተራሮች ብሄራዊ ፓርክ ውስጥ ከ900 በላይ ዋልያዎች የነበሩ ሲሆን አሁን ላይ ቁጥራቸው ወደ 300 ዝቅ ብሏል፡፡ በሰሜን ተራሮች ብሄራዊ ፓርክ መኖሪያቸውን ያደረጉና ከዚህ ቀደም ቁጥራቸው ከ900 በላይ የነበሩ ዋልያዎች ወደ 306 ዝቅ ማለታቸውን የፓርኩ ፅህፈት ቤት አስታውቋል:: የፓርኩ ፅህፈት ቤት ሀላፊ አቶ ማሩ ቢያድግልኝ እንደተናገሩት በክልሉ በነበረው የፀጥታ ችግር በተሰማው የተኩስ ድምፅ በፓርኩ ውስጥ የነበሩ ብርቅዬ እንስሳቶች በመረበሻቸው በአሁኑ ሰአት ቁጥራቸው ቀንሷል ብለዋል:: አለመረጋጋቱን ተከትሎ በዋና ዋና የዱር እንስሳቶች መናሃሪያ ቦታዎች ላይ የጦር መሳሪያዎች የነበሩ በመሆናቸው በርካታ የዱር እንስሳቶች ከአካባቢዉ መራቃቸውን  የገለፁት ኃላፊው ከእነዚህም መካከል ዋልያዎች ተጠቃሽ ናቸው ሲሉ ተናግረዋል። በሚመለከተው አካል በኩል…
Read More
ግብጽ በአባይ ወንዝ ላይ አዋጭነታቸው ያልተረጋገጡ ፕሮጀክቶችን እንዳትገነባ ኢትዮጵያ ጠየቀች

ግብጽ በአባይ ወንዝ ላይ አዋጭነታቸው ያልተረጋገጡ ፕሮጀክቶችን እንዳትገነባ ኢትዮጵያ ጠየቀች

ኢትዮጵያ በጸጥታው ምክር ቤት በግብጽ ለቀረበባት ክስ ምላሽ ሰጥታለች ከአንድ ሳምንት በፊት ኢትዮጵያ በታላቁ ህዳሴ ግድብ አምስተኛው ዙር ውሃ ሙሌት ማከናወኗ እና ተጨማሪ ተርባይኖች ሀይል ማመንጨት መጀመራቸውን ይፋ ማድረጓ ይታወሳል፡፡ ይህን ተከትሎም ግብጽ ኢትዮጵያ በግድቡ ለይ የተናጠል እርምጃ ወስዳለች በሚል ለተባበሩት መንግስታት ድርጅት የጸጥታው ምክር ቤት ክስ አስገብታለች፡፡ በግብጽ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የተፈረመው ይህ ደብዳቤ ኢትዮጵያ በፈረንጆቹ 2015 የተፈረመውን የመርህ ስምምነት ጥሳለች፣ ድርጊቱም ለአካባቢው ሀገራት አለመረጋጋት የሚሆን ነው፣ ግብጽ ብሔራዊ ጥቅሟን ለማስጠበቅ በተመድ ቻርተር አማካኝነት እርምጃ ትወስዳለች ሲልም ያትታል፡፡ ኢትዮጵያ በግብጽ ለቀረበባት ክስ በይፋ ባሳለፍነው ቅዳሜ ለተመድ ይፋዊ ምላሽ መስጠቷን አል ዐይን ከታማኝ ምንጮች አረጋግጧል፡፡ አል ዐይን የተመለከተው ይህ ደብዳቤ…
Read More
ግብጽ በድጋሚ ኢትዮጵያን በጸጥታው ምክር ቤት ላይ ከሰሰች

ግብጽ በድጋሚ ኢትዮጵያን በጸጥታው ምክር ቤት ላይ ከሰሰች

በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ ዙሪያ ተቃውሞ አለኝ የምትለው ግብጽ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የጸጥታው ምክር ቤት ላይ ከሳለች፡፡ ግብጽ በዛሬው ዕለት ለጸጽታው ምክር ቤት በጻፈችው ደብዳቤ ላይ እንደገለጸችው ኢትዮጵያ በታላቁ ሕዳሴ ግድብ ላይ ለአምስተኛ ዓመት ውሃ ሙሌት አከናውናለች ይላል፡፡ በግብጽ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ ስደተኞች እና ግብጻዊያን አርበኞች እንደተጻፈ የተገለጸው ይህ ደብዳቤ ኢትዮጵያ የግብጻዊያንን ጥቅም በሚጻረር መልኩ የውሃ ሙሌት እያካሄደች ነው ብሏል፡፡ በሀገሪቱ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ባድር አብደል አቲ የተፈረመው ይህ የተመድ ደብዳቤ ኢትዮጵያ፣ግብጽ እና ሱዳን በፈረንጆቹ 2015 ላይ የተፈራረሙትን ስምምነት በመጣስ የግድቡ ውሃ ሙሌት በተናጠል ተከናውኗል፣ ይህም የታችኛው ተፋሰስ ሀገራትን ጥቅም የሚጎዳ እንደሆነ ተጠቅሷል፡፡ ከሰሞኑ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ የግድቡን…
Read More
ኢትዮጵያ ከአንድ ወር በኋላ ለታንዛኒያ የኤሌክትሪክ ሀይል መሸጥ እንደምትጀምር ገለጸች

ኢትዮጵያ ከአንድ ወር በኋላ ለታንዛኒያ የኤሌክትሪክ ሀይል መሸጥ እንደምትጀምር ገለጸች

የታላቁ ሕዳሴ ግድብ ሀይል የማመንጨት አቅም በዕጥፍ ጨምሯል ተብሏል ኢትዮጵያ ከታላቁ የህዳሴ ግድብ የምታመነጨውን የኤሌክትሪክ ኃይል መጠን ከእጥፍ በላይ ማሳደጓን አስታወቀች። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሀይል ሥራ አስፈጻሚ አሸብር ባልቻ በሰጡት መግለጫ በቅርቡ ሁለት ተጨማሪ ተርባይኖች አገልግሎት በመጀመራቸዉ ከግድቡ የሚመረተዉ የኤሌክትሪክ ኃይል መጠን ወደ 1 ሺሕ 550 ሜጋዋት ከፍ ብሏል። ከዚሕ ቀደም ሥራ የጀመሩት ሁለት ተርባይኖች እያንዳዳቸዉ 375 ሜጋዋት የኤሌክትሪክ ኃይል ሲያመነጩ ቆይተዋል፡፡ ሰሞኑን የተመረቁት ሁለት ተጨማሪ ተርባይኖች ደግሞ እያንዳዳቸዉ 400 ሜጋዋት ኃይል እንደሚያመነጩ ተገልጿል፡፡ ኢትዮጵያ ከግብፅና ሱዳን ጋር የሚያወዛግባትን ግዙፍ የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ግድብ በአባይ ወንዝ ላይ መገንባት የጀመረችዉ ከመጋቢት 2003 ዓ.ም ጀምሮ ነበር። ይህ የአፍሪካ ትልቁ ግድብ በ2014 ዓ.ም ላይ…
Read More