08
Apr
ኢትዮ ቴሌኮም በአዲስ አበባ ከተማ ከመገናኛ ወደ ቦሌ በሚወስደው አውራ ጎዳና ላይ እጅግ ፈጣን ያለውን የኤሌክትሪክ መኪና ባትሪ መሙያ ሁለተኛውን ጣቢያ በይፋ ሥራ አስጀምሬያለሁ ብሏል። ኩባንያው ከዚህ ቀደም ከቦሌ ወደ መገናኛ በሚወስደው አውራ ጎዳና ላይ 16 መኪኖችን በአንድ ጊዜ ማስተናገድ የሚችል የኤሌክትሪክ መኪና መሙያዎችን የያዘ ጣቢያ ገንብቼ ወደ ስራ አስገብቻለሁ ማለቱ ይታወሳል፡፡ በዚህም ከየካቲት 4 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ ለ14 ሺህ 280 የኤሌክትሪክ መኪኖች አገልግሎት መስጠት ችሏል ተብሏል። ለዚህም 376,574.72 ኪሎዋት የኤሌክትሪክ ኃይል ጥቅም ላይ ውሏል የተባለ ሲሆን በተጨማሪም 521,074.23 ኪሎግራም ካርቦንዳይ ኦክሳይድ ወደ ከባቢ አየር እንዳይለቀቅ መከላከል የተቻለ ሲሆን፣ ይህም ከ2,622 በላይ ዛፎችን ከመትከል ጋር እንደሚነጻጸር ተገልጿል። በምራፍ ሁለት…