አካባቢ ጥበቃ

ኢትዮ ቴሌኮም ሁለተኛውን የኤሌክትሪክ መኪና ባትሪ መሙያ ጣቢያ አስመረቀ

ኢትዮ ቴሌኮም ሁለተኛውን የኤሌክትሪክ መኪና ባትሪ መሙያ ጣቢያ አስመረቀ

ኢትዮ ቴሌኮም በአዲስ አበባ ከተማ ከመገናኛ ወደ ቦሌ  በሚወስደው አውራ ጎዳና ላይ እጅግ ፈጣን ያለውን የኤሌክትሪክ መኪና ባትሪ መሙያ ሁለተኛውን ጣቢያ በይፋ ሥራ አስጀምሬያለሁ ብሏል። ኩባንያው ከዚህ ቀደም ከቦሌ ወደ መገናኛ በሚወስደው አውራ ጎዳና ላይ 16 መኪኖችን በአንድ ጊዜ ማስተናገድ የሚችል የኤሌክትሪክ መኪና መሙያዎችን የያዘ ጣቢያ ገንብቼ ወደ ስራ አስገብቻለሁ ማለቱ ይታወሳል፡፡ በዚህም ከየካቲት 4 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ ለ14 ሺህ 280 የኤሌክትሪክ መኪኖች አገልግሎት መስጠት ችሏል ተብሏል። ለዚህም 376,574.72 ኪሎዋት የኤሌክትሪክ ኃይል ጥቅም ላይ ውሏል የተባለ ሲሆን በተጨማሪም 521,074.23 ኪሎግራም ካርቦንዳይ ኦክሳይድ ወደ ከባቢ አየር እንዳይለቀቅ መከላከል የተቻለ ሲሆን፣ ይህም ከ2,622 በላይ ዛፎችን ከመትከል ጋር እንደሚነጻጸር ተገልጿል። በምራፍ ሁለት…
Read More
ታላቁ የህዳሴ ግድብ በቀጣዮቹ ስድስት ወራት ውስጥ ይጠናቃል ተባለ

ታላቁ የህዳሴ ግድብ በቀጣዮቹ ስድስት ወራት ውስጥ ይጠናቃል ተባለ

ከ15 ዓመት በፊት በቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ግንባታው የተጀመረው ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴው ግድብ በያዝነው ዓመት እንደሚጠናቀቅ ተገልጿል፡፡ ጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ (ዶ/ር) ከህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽ በመስጠት ላይ ናቸው። ጠቅላይ ሚንስትሩ ከህዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት አባላት ለተነሳው ጥያቄ ምላሽ በሰጡበት ውቅት እንዳሉት ህዳሴ ግድብን ከ6 ወር በኋላ እንመርቃለን ብለዋል፡፡ መንግስት ከህዳሴ ግድብ ጋር በተያያዘ ከግብፅ መንግስት ጋር በተለይም ከደህንነት መስሪያ ቤት ጋር ህዳሴን በተመለከተ ውይይት አድርገናል የተለያዩ ሃሳቦችም በህዳሴ ግድብ ዙሪያ አቅርበናል ብለዋል፡፡ መንግስት በህዳሴ ግድብ ጋር በተያያዘ ከግብፅ ጋር ለመነጋገርና ለመወያየት ዝግጁ ነው ሲሉ ጠቅሰዋል:: የግድቡ ግንባታ ከተጀመረ 15 ዓመታት ሊሞሉት አንድ ሳምንት ብቻ ቀርቶታል።…
Read More
የህዳሴው ግድብን ለማጠናቀቅ 80 ቢሊዮን ብር ያስፈልጋል ተባለ

የህዳሴው ግድብን ለማጠናቀቅ 80 ቢሊዮን ብር ያስፈልጋል ተባለ

የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን ቀሪ ስራዎች ለማጠናቀቅ 80 ቢሊዮን ብር እንደሚያስፈልገው ተገልጿል፡፡ ከ14 ዓመት በፊት ለግንባታው መሰረት ድንጋይ ሲጣል 80 ቢሊዮን ብር ያስፈልገዋል ተብሎ የተጀመረው የታላቁ ህዳሴ ግድብ፤ ግንባታው 97.6 በመቶ እንደደረሰና ጥቂት የማጠናቀቂያ ስራዎች ብቻ እንደቀሩት  የታላቁ ህዳሴ ግድብ ማስተባበሪያ የፕሮጀክት ፅህፈት ቤት ተናግሯል፡፡ ህዝቡ እስካሁን ከ20 ቢሊዮን ብር በላይ ለግእቡ ግንባታ በበጎ ፈቃደኝነት ያዋጣ ሲሆን በዚህ ዓመት 1.6 ቢሊዮን ብር ለመሰብሰብ አቅዶ እየሰራ እንደሆነ ተገልጿል፡፡ የዚህ አካል የሆነና ባንኮችን፣ ኢንሹራንስ ተቋማትንና የብድርና ቁጠባ ተቋማትን ያሳተፈ የገቢ ማሰባሰቢያ መርሃ ግብር ባሳለፍነው ዓርብ አካሂዷል፡፡ በመርሃ ግብሩ 110 ሚሊዮን ብር ለመሰብሰብ የታሰበ ቢሆንም በወቅቱ ከተቋማቱ መሰብሰብ የተቻለው 25.9 ሚሊዮን ብር ብቻ…
Read More
ኢትዮጵያ ለኤሌክትሪክ መኪኖች አዲስ መመሪያ አዘጋጀች

ኢትዮጵያ ለኤሌክትሪክ መኪኖች አዲስ መመሪያ አዘጋጀች

ለኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች ሃይል መሙያ ማሽን (ቻርጀር) መትከል የሚፈቅድ መመሪያ ጸደቀ መመሪያው በመንገዶች ግራና ቀኝ በየ50 ኪሎሜትር ልዩነት የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎችን መሙላት የሚችል ፈጣን ቻርጀር ጣቢያ ማቋቋም ይፈቅዳል፡፡ ይሁንና የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች ሃይል ማቅረብ የሚፈልጉ ተቋማት ከነዳጅ እና ኢነርጂ ባለስልጣን ፈቃድ በመውሰድ እንዳለባቸው መመሪያ ይገልጻል። በተለያዩ ተቋማት የሚተከሉ የኤሌክትሪክ ሃይል መሙያዎች ከባለስልጣኑ ፈቃድ ማግኘት እንደሚጠበቅባቸው ይደነግጋል፡፡ ነገር ግን በግል በቤት ውስጥ ከሚተከሉ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ ሃይል መሙሊያ ማሽኖች ፈቃድ መጠየቅ የማይጠበቅባቸው መሆኑን ያመላከተው የተቋሙ መረጃ ከዚህ ውጭ ግን ማናቸውም የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ ሃይል ሙሌት የሚሰጡ ማሽኖች መትከል የሚቻለው ከባለስልጣኑ ፈቃድ ሲያገኝ ብቻ መሆኑንም አመላክቷል። መመሪያው ለህዝብ በሽያጭ የኤሌክትሪክ ሃይል ሙሊት አገልግሎት የሚሰጡ ታሪፋቸው በባለስልጣኑ ሲጸድቅላቸው…
Read More
በኢትዮጵያ ባጋጠመው የመሬት መንቀጥቀጥ አደጋ 80 ሺህ ዜጎች እንደሚፈናቀሉ ተገለጸ

በኢትዮጵያ ባጋጠመው የመሬት መንቀጥቀጥ አደጋ 80 ሺህ ዜጎች እንደሚፈናቀሉ ተገለጸ

በኢትዮጵያ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የመሬት መንቀጥቀጥ አደጋዎች እየተደጋገሙ ሲሆን እስካሁን መኖሪያ ቤቶች ላይ የተወሰኑ ጉዳቶችን ከማድረስ የዘለለ ከባድ ጉዳት አላደረሱም፡፡ ባለፉት ሁለት ሳምንት ውስጥ ብቻ ከ30 ጊዜ በላይ በአፋር ክልል አዋሽ ከተማ አቅራቢያ የመሬት መንቀጥቀጥ አደጋዎች ያጋጠሙ ሲሆን በትናንትናው ዕለት ከ60 ዓመት በኋላ ከፍተኛ የጠባለ የመሬት መንቀጥቀጥ አደጋ አጋጥሟል፡፡ የአሜሪካ ጂኦሎጂካል ሰርቬይ ሪፖርት እንደገለጸው ከሆነ በሬክተር ስኬል 5 ነጥብ 8 የተመዘገበ የመሬት መንቀጥቀጥ አደጋ አጋጥሟል፡፡ በዚህ አደጋ ምክንያት በአፋር ክልል ባሉ መኖሪያ ቤቶች እና የመንግስት ተቋማት ላይ አነስተኛ ጉዳት ያጋጠመ ሲሆን ንዝረቱ አዲ አበባ ድረስ ተሰምቷል፡፡ የመንግስት ኮሚኒኬሽን አገልግሎት ባወጣው ማስታወቂያ የርዕደ መሬቱ ማዕከል ከሆኑ 12 ቀበሌዎች 80 ሺህ ዜጎችን ሊፈጠር…
Read More
በኢትዮጵያ ባንድ ቀን ውስጥ ከ14 ጊዜ በላይ የመሬት መንቀጥቀጥ አደጋ ተከሰተ

በኢትዮጵያ ባንድ ቀን ውስጥ ከ14 ጊዜ በላይ የመሬት መንቀጥቀጥ አደጋ ተከሰተ

በኢትዮጵያ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የመሬት መንቀጥቀጥ አደጋዎች እየተደጋገሙ ሲሆን እስካሁን መኖሪያ ቤቶች ላይ የተወሰኑ ጉዳቶችን ከማድረስ የዘለለ ከባድ ጉዳት አላደረሱም፡፡ አደጋው እያጋጠመ ያለው በአፋር ክልል አዋሽ ልዩ ስሙ ፈንታሌ አካባቢ እንደሆነ የአሜሪካ ጂኦሎጂካል ሰርቬይ ሪፖርት ያስረዳል፡፡ በአዋሽ ፈንታሌ እየተከሰተ ባለዉ ተደጋጋሚ ርዕደ መሬት ምክንያት ነዋሪዎች ከመኖሪያ ቤታቸው እየለቀቁ ሲሆን እስካሁን ከ2,500 በላይ ሰዎች ተፈናቅለዋል፡፡ ንዝረቱ አዲስ አበባ ድረስ በተሰማው የመሬት መንቀጥቀጥ አደጋዎች እስካሁን ከፍተኛው 5 በሬክተር ስኬል 5 የሆነ የመሬት መንቀጥቀጥ ነው። በአደጋው ከ100 በላይ ቤቶች ጉዳት የደረሰባቸዉ ሲሆን፤ 2 ሺሕ 560 ሰዎች መፈናቀላቸውን እና እንሰሳት መሞታቸውን የአዋሽ ፈንታሌ ወረዳ አስተዳደር አቶ አደም ባሂ ተናግረዋል። አስተዳዳሪው አክለውም በቀን ውስጥ እስከ…
Read More
በደን አጠባበቅ ላይ የተሻለ የፈጠራ ስራ ያቀረቡ ወጣቶች ተሸለሙ

በደን አጠባበቅ ላይ የተሻለ የፈጠራ ስራ ያቀረቡ ወጣቶች ተሸለሙ

ውድድሩ የኢትዮጵያ አየር ንብረት ለውጥ ትብብር፣ኢንፉሌንሰርስ እና ቬንደንስ የተሰኙ ተቋማት በጋራ አዘጋጅተውታል፡፡ ሶስቱ በአየር ንብረት ለውጥ ላይ የሚሰሩት ተቋማት ከሁለት ወራት በፊት ወጣቶች በደን አጠባበቅ ዙሪያ በኢሴይ ራይቲንግ፣ ኢንፎ ግራፊ እና ቪዲዮ የታገዘ ስራዎቻቸውን እንዲያቀርቡ ጥሪ አቅርበው ነበር፡፡ የኢንፉሌንሰርስ ኤክስኪዩቲቭ ዳይሬክተር ናሆም ፈቃዱ እንዳሉት በተደረገው ማስታወቂያ መሰረት 80 ወጣቶች በውድድሩ ላይ እንደተሳተፉ ተናግረዋል፡፡ ከሁሉም ተወዳዳሪዎች ውስጥ ከአንድ እስከ ሶስተኛ ደረጃ የወጡ ወጣት አሸናፊዎች  ከ10 ሺህ እስከ 20 ሺህ ብር ሽልማት ተሸልመዋል፡፡ ወጣት ናሆም እንዳሉት ተቋማቸው ኢንፉሌንሰርስ ሁሉም ሰው ለአካባቢ ጥበቃ የራሱን ድርሻ እንዲወጣ በሚል መቋቋሙን ተናግረዋል፡፡ ለአካባቢ ጥበቃ የራሳቸውን አስተዋጽኦ ማበርከት ለሚፈልጉ ሰዎች ነው የተቋቋመው፣የአየር ንብረት ለውጥ የባሰ ጉዳት የሚያደርሰው…
Read More
በኢትዮጵያ የአንበሳ እንስሳት የመጥፋት አደጋ ተደቅኖበታል ተባለ

በኢትዮጵያ የአንበሳ እንስሳት የመጥፋት አደጋ ተደቅኖበታል ተባለ

በኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ጥበቃ ባለስልጣን  የአንበሳ እና የስጋ በል እንስሳት ተመራማሪ የሆኑት አቶ ካህሳይ ገብረ-ተንሳይ  አሁን ላይ በኢትዮጵያ ያሉት አንበሶች ቁጥር ከ1 ሺ እንደማይበልጥ ተናግረዋል። በሃገሪቱ አሁን ላይ አንበሶች ያሉበት  ሁኔታ ለማወቅ ጥናት  ማድረጋቸውን የገለፁልን ተመራማሪው በአዋሽ  እና በመካከለኛው አዋሽ  በተደረገው ጥናት መሰረት ያለው ሁኔታ  ተስፋ ሰጪ ቢሆንም   አሁንም ግን ሁሉም ርብርብ ካላደረገ  አንበሶቹን ልናጣ እንችላለን ብለዋል፡፡ ተመራማሪው እንደሚሉትም ህገወጥ የነዋሪዎች ሰፈራ፣ የደን ጭፍጨፋ መኖር፣ የእርሻ ስራ እና  ግጦሽ  መበራከት አንበሶቹ  የሚፈልጉትን ምግብ እንዳያገኙና በምግብ ሰንሰለት ውስጥ ችግር እንዲፈጠር ብሎም ለህገወጥ አደን  በስፋት ተጋላጭ እንዲሆኑ አድርጓቸዋል ብለዋል። ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ  የባህል መድኃኒት ቀማሚዎች  ፊታቸውን ወደ አንበሳ አጥንት ማዞራቸው እንስሳቶቹን ለህገወጥ…
Read More
ኢትዮጵያ የፕላስቲክ ምርቶች መጠቀምን የሚከለክል ህግ አዘጋጀች

ኢትዮጵያ የፕላስቲክ ምርቶች መጠቀምን የሚከለክል ህግ አዘጋጀች

ኢትዮጵያ ለአንድ ጊዜ ግልጋሎት የሚውሉ የፕላስቲክ ምርቶች ሀገር ውስጥ እንዳይገቡ የሚከለክል ህግ አዘጋጀች፡፡ በጠቅላይ ሚኒስትሩ የሚመራው የሚኒስትሮች ምክር ቤት የፕላስቲክ ምርቶች አጠቃቀም ላይ ገደብ የሚጥል ረቂ ህግ ላይ ተወያይቷል፡፡ ምክር ቤቱ ባሳለፍነው ሳምንት ለአንድ ጊዜ ግልጋሎት የሚውሉ የፕላስቲክ ምርቶች ወደ ሀገር ውስጥ እንዳይገቡ የሚከለክል ረቂቅ አዋጅን አዘጋጅቷል፡፡ ረቂቅ አዋጁ ለዝርዝር እይታ እና ተጨማሪ ግብዓት ታክሎበት እንዲጸድቅ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ተመርቷል። ረቂቅ አዋጁ የሀገሪቱን የደረቅ ቆሻሻ አሰባሰብ፣ ማጓጓዝ፣ ክምችት፣ መልሶ አጠቃቀም፣ መልሶ ኡደት እና አወጋገድ ሥርዓት ማስያዝ ላይ ያተኮረ እንደሆነ የጠቅላይ ሚኒስቴር ጽህፈት ቤት አስታውቋል፡፡ የኢትዮጵያ የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ሌሊሴ ነሜ በበኩላቸው ለሀገሪቱ ፓርላማ የተመራው ይህ ረቂቅ አዋጅ፤…
Read More
የኢትዮጵያ ብርቅዬ የዱር እንስሳ የሆነው ዋልያ የመጥፋት አደጋ ተደቅኖበታል ተባለ

የኢትዮጵያ ብርቅዬ የዱር እንስሳ የሆነው ዋልያ የመጥፋት አደጋ ተደቅኖበታል ተባለ

በኢትዮጵያ ካሉ የዱር እንስሳት መጠለያዎች ውስጥ አንዱ በሆነው በ ሰሜን ተራሮች ብሄራዊ ፓርክ ውስጥ ከ900 በላይ ዋልያዎች የነበሩ ሲሆን አሁን ላይ ቁጥራቸው ወደ 300 ዝቅ ብሏል፡፡ በሰሜን ተራሮች ብሄራዊ ፓርክ መኖሪያቸውን ያደረጉና ከዚህ ቀደም ቁጥራቸው ከ900 በላይ የነበሩ ዋልያዎች ወደ 306 ዝቅ ማለታቸውን የፓርኩ ፅህፈት ቤት አስታውቋል:: የፓርኩ ፅህፈት ቤት ሀላፊ አቶ ማሩ ቢያድግልኝ እንደተናገሩት በክልሉ በነበረው የፀጥታ ችግር በተሰማው የተኩስ ድምፅ በፓርኩ ውስጥ የነበሩ ብርቅዬ እንስሳቶች በመረበሻቸው በአሁኑ ሰአት ቁጥራቸው ቀንሷል ብለዋል:: አለመረጋጋቱን ተከትሎ በዋና ዋና የዱር እንስሳቶች መናሃሪያ ቦታዎች ላይ የጦር መሳሪያዎች የነበሩ በመሆናቸው በርካታ የዱር እንስሳቶች ከአካባቢዉ መራቃቸውን  የገለፁት ኃላፊው ከእነዚህም መካከል ዋልያዎች ተጠቃሽ ናቸው ሲሉ ተናግረዋል። በሚመለከተው አካል በኩል…
Read More