መነሻ ገፅ

“የኢትዮጵያ የረቂቅ ሙዚቃ እናት” እማሆይ ፅጌማርያም ገብሩ አረፉ

“የኢትዮጵያ የረቂቅ ሙዚቃ እናት” እማሆይ ፅጌማርያም ገብሩ አረፉ

ፒያኖን በድንቅ ብቃት ስለሚጫወቱ “የፒያኖዋ እናት” የሚል ስያሜን ያገኙት እማሆይ ፅጌማርያም በ100 አመታቸው ነው ያረፉትእማሆይ ጽጌማርያም ከ150 በላይ የረቂቅ ሙዚቃ ድርሰቶችን የጻፉ ሲሆን፥ ሦስት አልበሞችን በሲዲ እና በሸክላ ላይ ማሳተማቸውም ይታወሳል በኢትዮጵያ ቀዳሚዋ የቫዮሊን እና ፒያኖ አቀናባሪ እማሆይ ፅጌማርያም ገብሩ በ100 ዓመታቸው አርፈዋል።እማሆይ ፅጌማርያም ከአባታቸው ከአቶ ገብሩ ደስታ እና እናታቸው ወይዘሮ ካሣዬ የለምቱ በ1915 ዓ.ም በአዲስ አበባ ውስጥ ነው የተወለዱት። እማሆይ ጽጌማርያም ገብሩ በልጅነታቸው ለትምህርት በሄዱባት ስዊዘርላንድ ፒያኖን በደንብ ተምረዋል። ከትምህርት መልስም በ19 አመታቸው ወደ ወሎ ግሸን ማርያም ገዳም በመሄድ በ21 አመታቸው ምንኩስናን መቀበላቸውን የኢቢሲ ዘገባ ያሳያል። ወላጆቻቸው ያወጡላቸው ስም የውብዳር ሲሆን ምንኩስናን ከተቀበሉ በኋላ መጠሪያቸው ወደ እማሆይ ፅጌማርያም ተቀይሯል።…
Read More
በአርባምንጭ ዙሪያ ጫሞ ሀይቅ ላይ በተፈጠረ  ማዕበል የስምንት ሰዎች ህይወት አለፈ

በአርባምንጭ ዙሪያ ጫሞ ሀይቅ ላይ በተፈጠረ ማዕበል የስምንት ሰዎች ህይወት አለፈ

በደቡብ ክልል ጫሞ ሐይቅ ላይ በጀልባ ሲጓዙ የነበሩ 8 ሰዎች ባጋጠማቸው የማዕበል አደጋ ምክንያት ሰጥመው ህይወታቸው አለፈ። " ኢትዮጵያ ኢንሳይደር " የአማሮ ልዩ ወረዳ ኮሚዩኒኬሽን ዋቢ አድርጎ እንደዘገበው አደጋው የደረሰው ትላንት ቅዳሜ ከሰዓት ለኃላ ነው። ባለሞተር ጀልባው የአማሮ ልዩ ወረዳ አልፋጮ ቀበሌ ነዋሪዎችን አሳፍሮ ወደ አርባ ምንጭ በመጓዝ ላይ እያለ በጫሞ ሐይቅ ላይ በነበረው ማዕበል የመስጠም አደጋው አጋጥማል። በአደጋው የጀልባውን ሹፌር ጨምሮ ስምንት ሰዎች ህይወታቸው አልፏል። አደጋው መከሰቱ እንደታወቀ የተጎጂዎችን ህይወት ለማትረፍ ጥረት ቢደረግም በጫሞ ሐይቅ ላይ በነበረው ከፍተኛ ማዕበል ምክንያት አልተሳካም። ከአደጋው መድረስ በኋላ ከአርባ ምንጭ ከተማ በመጡ ዋናተኞች ጭምር ሕይወት ለማዳን ቢሞከርም በሰዓቱ የነበረው ማዕበል አላስቻለም ተብሏል። በጫሞ…
Read More
የኢትዮጵያ ፖለቲካ ፓርቲዎች የህወሀትን ከሽብር መዝገብ መሰረዝን ተቃወሙ

የኢትዮጵያ ፖለቲካ ፓርቲዎች የህወሀትን ከሽብር መዝገብ መሰረዝን ተቃወሙ

የትግራይ ህዝብ ነጻነት ግንባት (ህወሀት) በትግራይ ክልል ያለውን የሀገር መከላከያ ሰሜን እዝ ላይ ጥቃት መክፈቱን ተከትሎ ነበር በሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት የተጀመረው። ለሁለት ዓመት የዘለቀው ይህ ጦርነት ከ800 ሺህ በላይ ዜጎችን እና ከ20 ቢሊዮን ዶላር በላይ ዋጋ የንብረት ውድመት አድርሷል። በፌደራል መንግሥት እና ህወሀት መካከል የተደረገው ይህ ጦርነት ባሳለፍነው ህዳር በአፍሪካ ህብረት አደራዳሪነት በደቡብ አፍሪካ የሰላም ስምምነት ተፈርሟል። ይህን ስምምነት ተከትሎም ጦርነቱ የቆመ ሲሆን በትግራይ ክልል ጊዜያዊ መንግሥት በመመስረት ላይ ይገኛል። እንዲሁም ህወሀት በግንቦት 2021 ላይ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በሽብርተኝነት ተፈርጆ ነበር። ይህ ህግ አውጪ ምክር ቤት ባሳለፍነው ሳምንት ህወሀትን ከሽብር መዝገብ ላይ ሰርዟል። የኢትዮጵያ ማህበራዊ ፍትህ ፓርቲ እና የአማራ…
Read More
የትግራይ አህጉረ ስብከት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ስርዓትን እንዲያከብር ቋሚ ሲኖዶስ ጠየቀ

የትግራይ አህጉረ ስብከት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ስርዓትን እንዲያከብር ቋሚ ሲኖዶስ ጠየቀ

የትግራይ አህጉረ ስብከት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ስርዓትን እንዲያከብር ቋሚ ሲኖዶስ ጠየቀ። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ ከሰሞኑ በትግራይ አህጉረ ስብከት በተሰጠ መግለጫ ዙሪያ ምላሽ ሰጥታለች። ቤተ ክርስቲያኗ በመግለጫዋ እንዳለችው በጦርነቱ ምክንያት በቤተ ክርስቲያኒቱ የበላይ መዋቅርና በትግራይ ክልል አህጉረ ስብከት መካከል አስተዳደራዊና መዋቅራዊ ግንኙነት ተቋርጦ መቆየቱን ገልጻለች። ይህንንም ተከትሎ በጦርነቱ ምክንያት ሁሉም የባንክ ተቋማት ሥራቸውን በማቆማቸው በየጊዜው እንደሌሎች አህጉረ ስብከት ለትግራይ አህጉረ ስብከት ይላክ የነበረው በጀት መላክ አልተቻለም ተብሏል፡፡ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ቀጣይ እርምጃ ምንድን ነው? ቤተክርስቲያኗ ተፈጥሮ የነበረውን ችግር በቀኖናው መሰረት መፈታቱን ገለጸችምንም እንኳን በባንክ መዘጋት ለአገልጋይ ሠራተኞች በጀት መላክ ባይቻልም የደመወዝ መክፈያ የባንክ…
Read More
ሊዮኔል ሜሲ በእግር ኳስ ህይወቱ 800ኛ ጎሉን አስቆጠረ

ሊዮኔል ሜሲ በእግር ኳስ ህይወቱ 800ኛ ጎሉን አስቆጠረ

አርጀንቲናዊው የዓለም ኮኮብ ሊዮኔል ሜሲ በእግር ኳስ ህይወቱ 800ኛ ጎሉን ከመረብ አገናኝቷል። በኳታር አዘጋጅነት የተካሄደው የዓለም ዋንጫን ያሸነፈው የአርጀንቲና ብሔራዊ ቡድን አምበል ሊዮኔል ሜሲ በህይወት ዘመኑ ያስቆጠራቸውን ጎሎች ወደ 800 ከፍ አድርጓል። የሰባት ጊዜ የባሎንዶር አሸናፊው ሜሲ ሀገሩ አርጀንቲና ከፓናማ ጋር የወዳጅነት ጨዋታ ተጫውታ 2ለ0 አሸንፋለች። የአርጀንቲናን የማሸነፊያ ጎሎች ቲያጎ አልማዳ በ11ኛው ደቂቃ እንዲሁም ሊዮኔል ሜሲ ደግሞ በ89ኛው ደቂቃ አስቆጥራል። ሊዮኔል ሜሲ ለአርጀንቲና ብሔራዊ ቡድን ተሰልፎ ያስቆጠራቸውን ጎሎች ወደ 99 ከፍ ሲያደርግ በቀጣይ የማጣሪያ ጨዋታቆች 100ኛ ግቡን እንደሚያስቆጥር ይጠበቃል። የቀድሞው የባርሴሎና እግር ኳስ ክለብ ተጫዋች ሊዮኔል ሜሲ ለባርሳ 672 እንዲሁም አሁን እየተጫወተበት ላለው ፒኤስጂ ደግሞ 29 ጎሎችን አስቆጥሯል። ሊዮኔል ሜሲ…
Read More
ኢትዮ ቴሌኮም ቴሌብር ሱፐር አፕ የተሰኘ አገልግሎት መስጫውን ይፋ አደረገ

ኢትዮ ቴሌኮም ቴሌብር ሱፐር አፕ የተሰኘ አገልግሎት መስጫውን ይፋ አደረገ

ኢትዮ ቴሌኮም ከዚህ በፊት የተለያዩ አገልግሎቶችን ይሰጥበት የነበረውን "ቴሌ ብር" መተግበሪያ አዘምኗል። ዛሬ ይፋ ያደረገው ይህ የደንበኞች አገልግሎት ከዚህ በፊት በአገልግሎት ላይ ከነበሩት ሶስት ተጨማሪ አገልግሎቶችን መስጠት ያስችላል። አዲሶቹ አገልግሎቶች የታቀደ ክፍያ፣ ለቡድን ገንዘብ መላክ እና የእድል ጨዋታዎችን ማከናወን የሚያስችሉ ናቸው። የታቀደ ክፍያ አገልግሎት ደንበኞች የገንዘብ እና አየር ሰዓት ለመላክ እንዲሁም ወርሀዊ የአገልግሎት ክፍያዎችን በቀኑ ለመክፈል ቀድመው ማቀድ የሚያስችል እንደሆነ ተቋሙ አስታውቋል። ሁለተኛው እና ዛሬ ይፋ የተደረገው የቴሌ ብር ተጨማሪ አገልግሎት ከአንድ በላይ ለሆኑ ተቀባዮች አስቀድመው በሚሞሉት መስፈርት መሰረት በአንዴ መላክ ያስችላልም ተብሏል። ሶስተኛው አዲስ አገልግሎት ደግሞ የእድል ጨዋታ የሚባል ሲሆን አጠቃቀምን መሰረት ያደረገ የአጓጊ ሽልማቶች ባለቤት የሚያደርግ እንደሆነ በፕሮግራሙ…
Read More
ሳፋሪ ኮም ከብሔራዊ ባንክ የሞባይል ገንዘብ ዝውውር ፈቃድ እንደሚሰጠው ገለጸ

ሳፋሪ ኮም ከብሔራዊ ባንክ የሞባይል ገንዘብ ዝውውር ፈቃድ እንደሚሰጠው ገለጸ

ብሔራዊ ባንክ ለሳፋሪኮም የሞባይል ገንዘብ ዝውውር በቅርቡ ፈቃድ እንደሚሰጥ አስታውቋል በኢትዮጵያ የመጀመሪያውን የግል የቴሌኮም አገልግሎት ፈቃድ ላገኘው ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ የሞባይል ገንዘብ ዝውውር አገልግሎት እንዲሰጥ የሚያስችለውን ፈቃድ በቅርቡ እንደሚሰጥ ብሔራዊ ባንክ ገልጿል። የብሔራዊ ባንክ ገዥ አቶ ማሞ ምህረቱ መጋቢት እንዳሉት መንግስት የፋይናንስ ዘርፉን ለማዘመንና ለማጠናከር  የተለያዩ እርምጃዎችን እየወሰደ ነው። ከባንክ ውጭ የሆኑ የቴሌኮሙኒኬሽን ኩባንያዎችን፣ ፊንቴክና የክፍያ ኤጀንቶችን የመሳሰሉ ተቋማት በክፍያ አገልግሎት ዘርፉ እንዲሳተፉ መደረጉንም ጠቅሰዋል። ባንክ ገዢው አቶ ማሞ አክለውም በአገሪቱ የመጀመሪያው የግል የቴሌኮም አገልግሎት አቅራቢነት ፈቃድ አግኝቶ ሥራ የጀመረው ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ የሞባይል ገንዘብ አገልግሎት እንዲሰጥ የሚያስችለውን ፍቃድ በቅርቡ እንደሚያገኝ ተናግረዋል። ይህም ዋና መቀጨውን በኬንያ ያደረገው ሳፋሪኮም በስፋት የሚታወቅበትን የኤም-ፔሳ የሞባይል…
Read More
የ ታላቁ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ 90 በመቶ ተጠናቀቀ

የ ታላቁ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ 90 በመቶ ተጠናቀቀ

የሕዳሴ ግድብ ግንባታ 90 በመቶ ተጠናቀቀ የታላቁ ሕዳሴ ግድብ ማስተባበሪያ ፕሮጀክት ጽህፈት ቤት  እንዳስታወቀው የታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ 90 በመቶ ተጠናቋል። የሕዳሴ ግድብ መሠረተ ድንጋይ የተጣለበት 12ኛ ዓመትን አስመልክቶ ጽህፈት ቤቱ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቷል። ግድቡ በሚቀጥለው ዓመት ተጠናቆ ሙሉ ለሙሉ ወደ ስራ የሚገባ ሲሆን 5200 ሜጋ ዋት ሀይል ያመነጫል። በ5 ቢሊዮን ዶላር ወጪ እየተገነባ ያለው ይህ የአፍሪካ ግዙፍ ግድብ ወጪው በኢትዮጵያውያን እና በመንግስት በመሸፈን ላይ ይገኛል። የግድቡ ሁለት ቱርባይኖች አሁን ላይ 700 ሜጋ ዋት ሀይል በማመንጨት ላይ ሲሆን የግድቡ አራተኛ ዙር ውሀ ሙሌት በመጪው ክረምት ወራት እንደሚካሄድ ተገልጿል። ግብጽ ኢትዮጵያ በተናጥል በግድቡ ላይ የምትወስደው እርምጃ ታሪካዊ የውሀ ድርሻዬን ይጎዳል በሚል…
Read More
ሱዳን ለኢትዮጵያ ከ10 ሚሊዮን ዶላር በላይ የኤሌክትሪክ ክፍያ አለመፈጸሟ ተገለጸ

ሱዳን ለኢትዮጵያ ከ10 ሚሊዮን ዶላር በላይ የኤሌክትሪክ ክፍያ አለመፈጸሟ ተገለጸ

ሱዳን ለኢትዮጵያ መክፈል ያለባትን የኤሌክትሪክ ክፍያ ባለመክፈሏ መንግሥት ጣልቃ እንዲገባ ተጠይቋል። ሱዳን ከኢትዮጵያ ለምትጠቀመው የኤሌክትሪክ ኃይል ፍጆታ በየወሩ ሙሉ ለሙሉ መክፈል ቢኖርባትም ካለፈው ዓመት ጀምሮ ክፍያዋን በማቆረጧ፣ ተከፍሎ ያላለቀና መጠኑ ያልተገለጸ በርካታ ሒሳብ እንዳለባት ተገልጿል። ኢትዮጵያ ለሦስት የጎረቤት አገሮች የኤሌክትሪክ ኃይል ትልካለች። ሀገሮቹም አንደኛው ወር ሲጠናቀቅ የሚቀጥለው ወር ላይ ሆነው ባለፈው ወር ለተላከው የኤሌክትሪክ ኃይል ፍጆታ ክፍያ ይፈጽማሉ። ሱዳንም በእንዲህ ዓይነት አሠራር መክፈል የነበረባትን ቢሆንም ክፍያ አየቆራረጡ በመሆኑ ሙሉ ለሙሉ ክፍያቸውን ጨርሰው እየከፈሉና እያጠናቀቁ አይደለም ሲሉ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሕዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር አቶ ሞገስ መኮንን ተናግረዋል። "የአንድ ወር ሙሉ የሚከፈልበት፣ ሌላው ሙሉውን የማይከፈልበት፣ አልያም ደግሞ በከፊል ከሌሎች ክፍያዎች ጋር እያደረጉ…
Read More
ህወሓት ከሽብርተኛ ድርጅት ዝርዝር ውስጥ ተሰረዘ

ህወሓት ከሽብርተኛ ድርጅት ዝርዝር ውስጥ ተሰረዘ

ሕወሀት በሽብርተኝነት ከተፈረጀ ከ22 ወራት በኋላ ውሳኔው ተሽሯል የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሕዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) ከሽብርተኛ ድርጅት እንዲሠረዝ በአብላጫ ድምጽ ወስኗል። ምክር ቤቱ ዛሬ ባሄደው ልዩ ስብሰባ ህወሓትን ከሽብርተኛ መዝገብ ለማንሳት በቀረበለት የውሳኔ ሀሳብ ላይ ከተወያየ በኋላ በአብላጫ ድምፅ አፅድቋል። ለሰሜኑ ጦርነት ሰላማዊ መፍትሄ ለመስጠት በአፍሪካ ህብረት አደራዳሪነት ጥቅምት 24 ቀን 2015 ዓ.ም በደቡብ አፍሪካ ፕሪቶሪያ በኢትዮጵያ መንግስትና በህወሓት መካከል የሰላም ስምምነት መፈረሙ ይታወሳል። በተፈረመው የሰላም ስምምነት መሰረትም በፌደራል መንግስት እና በህወሓት በኩል ስራዎች ሲከናወኑ ቆይተዋል። ስምምነቱ የፌደራል መንግስት በትግራይ ክልል መሰረታዊ አገልግሎቶች እንዲጀመሩ እና የሰብዓዊ እርዳታ ለተጎጂዎች እንዲቀርብ አድርጓል። ህወሓትም ታጣቂዎቹን ወደ ካምፕ በመሰብሰብ ከባድ የጦር መሳሪያዎችን…
Read More