Blog

የቫሌንሲያ ማራቶን ውድድር በኢትዮጵያዊያን የበላይነት ተጠናቀቀ

የቫሌንሲያ ማራቶን ውድድር በኢትዮጵያዊያን የበላይነት ተጠናቀቀ

በስፔኗ ቫሌንሲያ የተካሄደው የማራቶን ውድድር በኢትዮጵያዊያን የበላይነት ተጠናቀቀ፡፡ ኢትዮጵያዊያን በተደጋጋሚ የሚነግሱባት የስፔኗ ቫሌንሲያ ዛሬም ኢትዮጵያዊያን ተመሳሳይ ድሎችን አግኝተውባታል፡፡ በዚው ውድድር በሁለቱም ጾታዎች ኢትዮጵያዊያን አትሌቶች በአንደኝነት አጠናቀዋል፡፡ በሴቶች የማራቶን ውድድር ኢትዮጵያዊያን ከአንደኛ እስከ 3ኛ ያለውን ደረጃ በበላይነት ሲያሸንፉ አትሌት ውርቅነሸ ደገፈ፣ አልማዝ አያና እና ህይወት ገብረኪዳን ከ1ኛ እስከ 3ኛ ያለውን ደረጃ ይዘው ጠናቀዋል፡፡ በዚህ የወንዶች የማራቶን ውድድር ላይ አትሌት ሲሳይ ለማ አንደኛ፣ ኬንያዊው አትሌት አሌክሳንደር ሙቲሶ ሁለተኛ እንዲሁም ዳዊት ወልዴ እና ቀነኒሳ በቀለ ሶተኛ እና አራተኛ ሆነው አጠናቀዋል፡፡ አትሌት ሲሳይ ለማ ርቀቱን 2:01:48 በሆነ ሰአት ማጠናቀቅ የቻለ ሲሆን የቦታውን ክብረወሰን ማሻሻል ሲችል ተጠብቆ የነበረው አትሌት ቀነኒሳ በቀለ አራተኛ ሆኖ ማጠናቀቅ ችሏል፡፡…
Read More
አሜሪካ የኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄ እንደሚሰጋት ገለጸች

አሜሪካ የኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄ እንደሚሰጋት ገለጸች

የአሜሪካ የታችኛው ምክር ቤት ኮንግረስ የውጭ ጉዳይ ኮሚቴ የአፍሪካ ጉዳዮች ንኡስ ኮሚቴ፣  ‘”በኢትዮጵያ ተስፋ ወይንስ ስጋት፣ የአሜሪካ ፖሊሲ ሁኔታ’’ ላይ ትላንት ምሸት ምስክርነት ሰምቷል፡፡ የኮሚቴው አባላት ለአሜሪካ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ ማይክ ሐመር፣ ስለ ባህር በር በጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ስለተነሳው ጥያቄ የአሜሪካን አቋም ጠይቀዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አሕመድ “የወደብ ጉዳይ ለኢትዮጵያ የህልውና ጉዳይ ነው” ብለው መናገራቸው በቀጠናው ካሉ አገራት አልፎ ለአሜሪካ ስጋት እንደሆነ ማይክ ሐመር ተናግረዋል። ይሁን እንጂ የጠቅላይ ሚኒስትሩ የባህር በር ፍላጎት በኃይል ተፈጻሚ እንደማይሆን በይፋ እንዲሁም በግል ማረጋገጫ እንደሰጧቸው አመልክተዋል። ጥያቄው በምስራቅ አፍሪካ ሀገራት ስጋት እንደፈጠረ የጠቆሙት ማይክ ሐመር፣ የኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄ በሰላማዊ መንገድ የሚቀጠል ከሆነ…
Read More
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ በሚሰጠው የብድር ወለድ ላይ ማሻሻያ አደረገ

የኢትዮጵያ ልማት ባንክ በሚሰጠው የብድር ወለድ ላይ ማሻሻያ አደረገ

ባንኩ በግብርና ስራዎች ለተሰማሩ ተበዳሪዎች የብድር ወለድ መጠኑን ከ11 በመቶ ወደ 7 በመቶ ዝቅ ማድረጉን አስታውቋል። ባንኩ በኢትዮጵያ የግብርና ስራዎችን ለማበረታታት በሚል ለተበዳሪዎች በሚሰጠው ብድር ላይ ያስከፍል በነበረው ወለድ ምጣኔ ላይ ማሻሻያ ማድረጉን ገልጿል። የብድር ወለድ ቅናሽ የተደረገው ያ ያልታረሰን የመሬት ሀብት ወደ ስራ ለማስገባት፤ ባለሀብቶች፣ አርሶ አደሮች እና አርብቶ አደሮች የበለጠ እንዲበረታቱ ለማድረግ በማሰብ እንደሆነ አስታውቋል። በዚህም መሰረት በአነስተኛ፣ መካከለኛና የኮርፖሬት ፕሮጀክት ብድር ለሚጠይቁ ይጠበቅ የነበረው የ11.5 በመቶ የማበደሪያ የወለድ ተመን ወደ 7 በመቶ ዝቅ አድርጓል ብሏል። ልማት ባንክ የሀገር ውስጥ ምርቶችን ለማሳደግ እና ከውጭ ተመርተው ወደ ሀገር ውስጥ የሚገቡ ምርቶችን በሀገር ውስጥ ለመተካት በሚል የተቋቋመ የመንግስት የልማት ድርጅት…
Read More
ጦርነቶች እንዲቆሙ በማደራደር የሚታወቁት ዲፕሎማት በ100 ዓመታቸው ህይወታቸው አለፈ

ጦርነቶች እንዲቆሙ በማደራደር የሚታወቁት ዲፕሎማት በ100 ዓመታቸው ህይወታቸው አለፈ

የቀድሞው የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር እና የኖቤል የሰላም ሽልማት አሸናፊ ሄንሪ ኪሲንገር   በመቶ አመታቸው  አረፉ ታዋቂው ዲፕሎማት እና ተፅዕኖ ፈጣሪ የውጭ ፖሊሲ አሳቢ በኮነቲከት በሚገኘው መኖሪያ ቤታቸው ትናንት ለሊት መሞታቸውን የአማካሪ ድርጅታቸው ኪሲንገር አሶሺየትስ በመግለጫው ገልጿል። በፈረንጆቹ በ1969 የፕሬዝዳንት ሪቻርድ ኒክሰን ከፍተኛ የብሄራዊ ደህንነት አማካሪ ከመሆናቸው በፊት በሃርቫርድ ዩኒቨርሲቲ የዶክትሬት ዲግሪ አግኝተው አለም አቀፍ ግንኙነቶችን አስተምረዋል። የፕሬዚዳንት ጄራልድ ፎርድ የመንግስት ፀሀፊም ሆነው አገልግለዋል። ጎበዝ ተደራዳሪ ተብለው የተወደሱ ሲሆን በ1970ዎቹ አሜሪካ ከሶቪየት ኅብረት ጋር ያለውን ግንኙነት እንድትሻሻል  ኪስንገር ትልቅ ሚና ነበራቸው። አሜሪካ  ከቻይና ጋር ያላትን ግንኙነት የተሻለ ለማድረግ መንገድ ጠርገዋል። እ.ኤ.አ. በ 1973 ኪሲንገር የፓሪስ የሰላም ስምምነትን በማሳካታቸው  ከዲፕሎማት ለዱክ ቶ…
Read More
አትሌት ቀነኒሳ በቀለ በቫሌንሺያ ማራቶን እንደሚሳተፍ ገለጸ

አትሌት ቀነኒሳ በቀለ በቫሌንሺያ ማራቶን እንደሚሳተፍ ገለጸ

አትሌት ቀነኒሳ በቀለ ሕዳር 23 ቀን 2016 ዓ.ም በሚካሄደው የቫሌንሺያ ማራቶን እንደሚሳተፍ አስታውቋል፡፡ አትሌቱ በፌስቡክ ገጹ እንዳለው "ከብዙ ጊዜ ጉዳት በኋላ በቫሌንሺያ ማራቶን እሳተፋለሁ" ብሏል። "ከብዙ ጉዳት በኋላ ወደ ውድድር በመመለሴ ደስተኛ ነኝ" ያለው አትሌት ቀነኒሳ አኤኤንቲኤ የተሰኘው ኩባንያ ስፖንሰሬ ነው፣ ላደረገልኝ ድጋፍ አመሰግናለሁ " ሲልም ገልጿል። ውድድሩ የፊታችን ሕዳር 23 ቀን 2016 ዓ.ም በስፔኗ ቫሌንሲያ እንደሚካሄድ ተገልጿል። አትሌት ቀነኒሳ በአምስት እና አስር ሺህ ውድድሮች ላይ ለዓመታት ሳይረታ የቆየ ውጤታማ አትሌት ሆኖ ቆይቷል። በሁለቱም ርቀቶች የዓለም ሪከርዶችን ለ16 ዓመታት ይዞ የቆየው አትሌት ቀነኒሳ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ደግሞ ፊቱን ወደ ማራቶን ውድድር አዙሯል። የማራቶን ውድድርን ከሁለት ሰዓት በታች ይገባል ተብሎ ከሚጠበቁት…
Read More
በአዲስ አበባ 100 ሺህ ሰዎች የሚሳተፉበት ሰላማዊ ሰልፍ ተጠራ

በአዲስ አበባ 100 ሺህ ሰዎች የሚሳተፉበት ሰላማዊ ሰልፍ ተጠራ

የኢትዮጰያ ህዝቦች አብዮታዊ ፓርቲ እንደገለጸው መነሻውን አራት ኪሎ ያደረገ ሰላማዊ ሰልፍ ለማድረግ የሚጠይቅ ደብዳቤ ለከንቲባ ቢሮ ማስገባቱን ገልጿል፡፡ ሰላማዊ ሰልፉ "ጦርነት ይቁም! ሠላም ይስፈን፣ መከላከያ ሰራዊቱ ባስቸኳይ ወደ ካምፕ ይግባ!" በሚል መሪ ቃል እንደሚካሄድ ተገልጿል፡፡ በኢትዮጵያ የተለያዩ አካባቢዎች የሚካሄደውን ደም አፋሳሽ ጦርነት ለማስቆም በሚል የተዘጋጀው ይህ ሰላማዊ ህዳር 30 ቀን 2016 ዓ. ም በሀገሪቱ ዋና ከተማ አዲስ አበባ ይካሄዳል ተብሏል፡፡ የሰላማዊ ሰልፉ አስተባባሪዎች ደብዳቤውን ጦርነት እንዲቆም፣ መከላከያ ሠራዊቱ ከዘመተባቸው ክልሎች ወጥቶ ወደ ጦር ካምፑ እንዲመለስና ፖለቲካዊ ውይይቶች እንዲከፈቱ በሰልፉ ላይ እንጠይቃለንም ብለዋል፡፡ የኢትዮጰያ ህዝቦች አብዮታዊ ፓርቲ /ኢህአፓ/ እና ሌሎች ዜጎች አስተባባሪነት የተጠራው ይህ ሰላማዊ ሰልፍ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ ጽህፈት…
Read More
የፈረንሳዩ ኩባንያ የኢትዮ ቴሌኮምን ድርሻ ለመግዛት የጀመረውን ጥረት እቅድ ሰረዘ

የፈረንሳዩ ኩባንያ የኢትዮ ቴሌኮምን ድርሻ ለመግዛት የጀመረውን ጥረት እቅድ ሰረዘ

ኦሬንጅ የተሰኘው የፈረንሳይ የቴሌኮም ኩባንያ ከኢትዮቴሌኮም 45 በመቶ አካባቢ ድርሻ ለመግዛት ዕቅድ የነበረው ቢሆንም ኃሳባችንን በፍጥነት ለመተግበር እና ውጤት ለማግኘት የሚያስችል ሁኔታ ባለመኖሩ ራሴን አግልያለሁ ብሏል። ኢትዮጵያ ከመንግስታዊው ኢትዮቴሌኮም እና በቅርቡ ገበያውን ከተቀላቀለው ከሳፋሪኮም በተጨማሪ ሦስተኛ የቴሌኮም አገልግሎት አቅራቢ ስራ እንዲጀምር ፈቃድ ለመስጠት ገበያውን እየገመገመ የቆየች ሲሆን በቅርቡ የገበያው ሁኔታ የታሰበውን ያህል አመርቂ ባለመሆኑ ሐደቱ ተቋርጧል ማለቷ ይታወሳል። ከዚህ ጎን ለጎን ከኢትዮቴሌኮም ከግማሽ ያነሰ ድርሻ ለመሸጥም እየጣረች ሲሆን ኦሬንጅ ድርሻ ለመግዛት ፍላጎት ካሳዩት ዓለምአቀፍ ግዙፍ ኩባንያዎች መካከል አንዱ ነበር። ኩባንያው ሞባይል ለዎርልድ ላይቭ እንደገለፀው ከ2021 ጀምሮ የነበረውን ፍላጎት አሁን መግታቱን ይፋ አድርጓል። ኦሬንጅ ግሩፕ በጉዳዩ ላይ ትንተና ከሠራ በኋላ “ስትራቴጂያችንን…
Read More
በጦርነት በተጎዳችው ትግራይ የ6 ቢሊዮን ብር ብረት ማምረቻ ፋብሪካ ሊገነባ እንደሆነ ተገለጸ

በጦርነት በተጎዳችው ትግራይ የ6 ቢሊዮን ብር ብረት ማምረቻ ፋብሪካ ሊገነባ እንደሆነ ተገለጸ

በ6 ቢሊዮን ብር ወጪ በኢትዮጵያ እና ቻይና ባለሃብቶች ትብብር የብረታ-ብረት ማምረቻ ኢንዱስትሪ በመቐሌ ከተማ ሊገነባ ነው። በአስር ወራት ውስጥ የሚገነባው ይህ ኢንዱስትሪ የስራ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ዛሬ ይፋ ተደርጓል። በዚህ ወቅት የትግራይ ክልል ግዜያዊ አስተዳደር ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጌታቸው ረዳ፤ የሌጀንድ ብረታብረት ኢንዱስትሪ ሃላፈነቱ የተወሰነ የግል ማህበር ለበርካታ ወጣቶች የስራ ዕድል የሚፈጥር በመሆኑ አስፈጊው ድጋፍ ይደረግለታል ብለዋል። ሌሎች በግልና በማህበር የተደራጁ ባለሃብቶችም የዚህን የልማት ፕሮጀክት አርአያ ተከትለው በማልማት  ራሳቸውንና ሀገራቸውን እንዲጠቅሙ መልእክት አስተላልፈዋል። የብረታብረት ማምረቻው 75 በመቶ በኢትዮጵያዊው ባለሃብት ኢንጅነር ያሬድ ተስፋይ የተሸፈነ ሲሆን ቀሪው 25 በመቶ ደግሞ በቻይናዊው ባለሃብት ሚስተር ሊ ዮን መሸፈኑን የፕሮጀክቱ አስተባባሪ አቶ ሳምሶም ገብረመድህን ገልጸዋል።…
Read More
ኢትዮጵያ 28 የመስኖ ግድቦችን በመገንባት ላይ መሆኗን ገለጸች

ኢትዮጵያ 28 የመስኖ ግድቦችን በመገንባት ላይ መሆኗን ገለጸች

የመስኖ እና ቆላማ አካባቢ ሚኒስቴር እንደገለጸው ኢትዮጵያ 28 የመስኖ ፕሮጀክቶችን በመገንባት ላይ መሆኑን አስታውቋል፡፡ በግንባታ ላይ ካሉት የመስኖ ግድቦች ውስጥም 13ቱን በተያዘው የ2016 ዓመት በከፊል ለማጠናቀቅ ጥረት እየተደረገ መሆኑንም ሚኒስቴሩ ገልጿል፡፡ በዚህ ዓመት እንዲጠናቀቁ በሚል እየተገነቡ ላሉ ግድቦችም 8 ነጥብ 03 ቢሊዮን ብር መመደቡ ተመልክቷል፡፡ የመስኖ እና ቆላማ አካባቢ ሚኒስቴር የሕዝብ ግንኙነት እና ኮሙኒኬሽን ሥራ አስፈጻሚ አቶ ብዙነህ ቶልቻ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጀት እንደገለጹት በአሁኑ ጊዜ በሀገሪቱ 28 የመስኖ ልማት ፕሮጀክቶች ግንባታቸው በመከናወን ላይ ነው፡፡ 13 የመስኖ ፕሮጀክቶች በከፊል ሲጠናቀቁ 2 ሺህ 450 ሄክታር መሬት ማልማት የሚያስችሉ እንደሆኑም ሃለፊው ተናግረዋል፡፡ እየተገነቡ ካሉት ግድቦች በተጨማሪም 27 አዲስ የመስኖ ግድቦችን ለመገንባት የጥናትና ዲዛይን…
Read More
የኢትዮጵያ ባለሥልጣናት ስለባህር በር አስተያየት ሲሰጡ እንዲጠነቀቁ ተጠየቀ

የኢትዮጵያ ባለሥልጣናት ስለባህር በር አስተያየት ሲሰጡ እንዲጠነቀቁ ተጠየቀ

ባለስልጣናት ስለ ባህር በር ጉዳይ የሚሰጡት መግለጫ የተጠናና ጥንቃቄ የተሞላበት መሆን እንዳለበት ምሁራን አሳስበዋል፡፡ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በኢትዮጵያ የባህር በር ዙሪያ የምሁራን ውይይት መድረክ አዘጋጅቶ ነበር፡፡ በዚህ የምሁራን መድረክ ላይ ጥናት ያቀረቡና ውይይት ያደረጉ ምሁራን፣ መንግሥት ስለባህር በር የሚሰጣቸው መረጃዎች የጎረቤት አገሮችን የማያሠጉና ጥንቃቄ የተሞላባቸው እንዲሆኑ አሳስበዋል፡፡ ‹‹ፍትሐዊ የወደብ አጠቃቀም ለአፍሪካ ቀንድ ዘላቂ ሰላምና ልማት›› በሚል ርዕስ በተስተናገደው በዚህ ዓውደ ጥናት ላይ፣ ኢትዮጵያ በሰላማዊ መንገድ የባህር በር ባለቤት መሆን ስለምትችልባቸው አማራጮች ሰፊ ምሁራዊ ውይይት ተካሂዷል፡፡ በጥናት መድረኩ ላይ ለኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄን በማስመለስ ታሪካዊ ድል ያስመዘገቡ ያለፈው ትውልድ ምርጥ ተሞክሮ ታሪካዊ ድል እንደነበር ተገልጿል፡፡ በሰላማዊ መንገድ ኤርትራን በፌዴሬሽን ከኢትዮጵያ ጋር…
Read More