23
Nov
የአፍሪካዊቷ ጋና ህግ አውጪ ምክር ቤት አባል የሆኑት አይዛክ አዶንጎ ከአንድ ዓመት በፊት የሀገሪቱ ምክትል ፕሬዝዳንትን ከማንችስተሩ ተከላካይ ተጫዋች ሀሪ ማጓየር ጋር ተመሳሳይ እንደሆኑ ተናግረው ነበር፡፡ የፓርላማ አባሉ በወቅቱ “የሀገሪቱ ምክትል ፕሬዝዳንት እንደ ማጓየር በራሱ ላይ ግብ የሚያስቆጥር፣ ጠንካራ የስራ አጋሮቹን መትቶ የሚጥል እና እንዲቀጡ ለዳኛ አቤት የሚል ነው” ሲሉ ተናግረው ነበር፡፡ ግለሰቡ ይህን ንግግር ያደረጉበት ተንቀሳቃሽ ምስል በተለያዩ ማህበራዊ የትስስር ገጾች ላይ ለብዙ ሰዎች መድረስ ችሏል፡፡ እኝህ የህግ አውጪ አባል “ስለ ማጓየር ከዚህ በፊት የተናገርኩት አስተያየት ስህተት ነበር፣ ማጓየርን ይቅርታ መጠየቅ እፈልጋለሁ ተጫዋቹ አሁን ላይ ምርጥ ተከላካይ መሆኑን አስመስክሯል” ሲሉ ተናግረዋል፡፡ ይሁንና ለጋና ምክትል ፕሬዝዳንትን ግን ይቅርታ አልጠይቅም ያሉት…